ይህ ጽሑፍ ለቤተ ክርስቲያን ምእመናን ከእግዚአብሔር ቃል ጠቃሚ እውነቶችን ከሚያስተላልፉ ተከታታይ እትሞች ውስጥ አንዱ ነው። እነዚህ በራሪ ጽሑፎች የቀረቡት ከአማርኛ ውጭ በሌሎች ቋንቋዎች አፋቸውን የፈቱ ሰዎች በሚረዱበት መንገድ ቀለል ተደርገው ነው። ምእመኖቿ የእግዚአብሔርን ቃል በትክክል እስካልተገነዘቡ ድረስ የትኛዋም ቤተ ክርስቲያን ልትጠነክር አትችልም። መንፈስ ቅዱስ እነዚህን በራሪ ጽሑፎች ተጠቅሞ የእግዚአብሔር ሕዝብ የማይለወጡትን የእግዚአብሔር እውነቶች እንዲረዱ እንዲያግዝ ጸሎታችን ነው። ይህንን በራሪ ጽሑፍ በሚገባ ለመጠቀም፥ የተጠቀሱትን ጥቅሶች አውጥተህ ልታነብ ይገባል።
“የጌታ እራት”፣ በቲም ፌሎስ ተጽፎ፣ ተሾመ ነጋሽ የተተረጎመ እና በኤስ አይ ኤም የታተመ ነው፡፡ አስቀድመን ስለ እነዚህ ቅዱሳን ትጋት እና የክርስቶስን ቤተ ክርስቲያን ለማገልገል ለከፈሉት ዋጋ ምስጋናችን እናቀርባለን፡፡ በመቀጠል ጽሁፉን ኮፒ እና ፕሪንት በማድረግ ለግልም ሆነ ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ማዋል የተፈቀደ ቢሆንም ያለአሳታሚው ፈቃድ ጽሁፉን መለወጥም ሆነ ለሽያጭ ማዋል ግን ፈጽሞ በሕግ የተከለከለ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡ መልካም ጥናት!
የትምሕርቶቹ ዝርዝር
ስለ ጌታ እራት ኢየሱስ የሰጣቸውን በርካታ መመሪያዎች መገንዘብ አስፈላጊ ነው
ቅዱስ ቁርባን (የጌታ እራት) ማለት ምን ማለት ነው?
አላግባብ የጌታን እራት ስለመውሰድ የተሰጡ ማስጠንቀቂያዎች