የዘላለም ሕይወት እንዳልዎት እርግጠኛ ነዎት?

በመጀመሪያ እንኳን ወደዚህ የደህንነት ትምህረት ጥናት መጡ እያልን መጽፍ ቅዱስ ለማጥናት ላደረጉት ቆራጥ ውሳኔ ልናደንቅዎ እንወዳለን፡፡  ይህ ‹የደኅንነት ትምህርት› ኮርስ የዘላለም ሕወትዎን በተመለከተ ወሰኝ ርእሰ ጉዳይ መሆኑን ልብ ይበሉ፡፡ በዚህ ጥናት ውስጥ የቀረቡ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች እርሶ ወደ መንግስተ ሰማይ ለሚያደርጉት የጉዞ መሰናዶ በእጅጉ እንደሚጠቅሞዎት እናምናለን፡፡ በዚህ ኮርስ ውስጥ የቀረቡ ሃሳቦች የእኛን አስተሳሰብና ግምት የያዙ ሳይሆኑ በቀጥታ መጽሐፍ ቅዱስ የሚለውን የሚናገሩ ናቸው፡፡ መጽሐፍ ቅዱሱ ሲናገር ልንናገር፣ ዝም ሲል ደግሞ ዝም ልንል ግድ ነውና፡፡ የምናደርጋቸውን ነገሮች ሁሉ በመጽሐፍ ቅዱስ መሰረት ልናደርጋቸው፣ በጽሐፉ በስማቸው የሚጠራቸውንም በግልጽ ልንጠራቸው ይገባል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ከሚለው የነሰ፣ የበዛ፣ ወይም የተለየ ነገር ሁሉ የስህተት ትንህርት ነው፡፡

ከእግዚአብሔር ቃል እውቀት ማነስ የተነሳ በተፈጠሩት በርካታ ሃይማኖቶች ምክኒያት በአለም ሕዝቦች መካከል ከፍተኛ ግራ በጋባት ይስተዋላል፡፡ በአሁኑ ሰአት በአለማችን ላይ የተለያየ አስተምህሮዎች፣ የስነ መለኮት ምልከታዎች እና አስተሳሰቦች ያልዋቸው ከ 600 በላይ ቤተ እምነቶች ይገኛሉ፡፡ በእነዚህ በርካታ እምነቶች ‹የእመን› ጥያቄ የሚቀርብላቸው የአለማችን ሰዎች ምን እና ማንን ማመን እንዳለባቸው ለመወሰን ግራ ተጋብተዋል፡፡ አዳኛችን የሆነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ በፈቃዱ በከፈለው ስቃይና ሞት ለኃጢአታችን ይቅርታ የሚያስፈልገውን ሁሉ አቅርቦልናል፡፡ በፍርድ ቀን ከሰይጣንና ከመላእክቱ ጋር ወደ ወደ ዘላለም እቶን እሳት መጣል አይገባንም፡፡ እናም ለመዳን የወንጌልን እውነት መታዘዝ ይኖርብናል፡፡ ወንጌል ምንድን ነው? ለመዳን ምን ማድረግ ይኖርብኛል? በዚህ ጥናት ውስጥ እግዚአብሔር በሰማይ ያዘጋጀልንን የዘላለም ሕይወት ስጦታ ለመውረስ መጽሐፍ ቅዱስ ምን ማድረግ እንዳለብን የሚናገረውን አብረን እናያለን፡፡

ከመጽሐፍ ቅዱስ የተወሰዱ ጥቅሶች በሙሉ ጠመም/ዘመም ባለ የፊደል አጻጻፍና ደማቅ ሆነው የቀረቡ ሲሆን ለእነዚህ ጥቅሶች ልብዎንና አእምሮዎን ሊከፍቱ ይገባል፡፡ እግዚአብሔር በእነዚህ ቃሎች ውስጥ ምን ሊያስተላልፍ እንደፈለገ መግለጥ የዚህ ኮርስ ዋነኛ አላማ ነው፡፡ ከመጽሐፍ ቅዱስ የተወሰዱትን እነዚህን ጥቅሶችን ሲያነቡ ለተሰመረባቸው ቃላት ልዩ ትኩረት እንዲሰጡ እናሳስባለን፡፡

“የዘላለም ሕይወት እንዳልዎት እርግጠኛ ነዎት?” የሚለው ይህ ኮርስ በ10 ትምህርቶች የተከፋፈለ ነው፡፡ ከእያንዳንዱ ትምህርት በኋላ የምርጫ እና የእውነት/ውሸት ጥያቄዎች ቀርበዋል፡፡ የጥያቄዎቹን ትክክለኛ መልሶች ከጥያቄዎቹ ጋር በቀረቡት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች ውስጥ ያገኙዋቸዋል፡፡ ይህን ኮርስ ማጥናት በዘላለም ሕይወትዎ ላይ ታላቅ ሚና እንዲጫወት የዘወትር ጸሎታችን ነው፡፡ ማነኛውም ጥያቄ ሆነ አስተያየት ቢኖርዎ ለመምህሮ ያሳውቁ ወይም በሚከተለው አድራሻ ቢልኩልን ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት ቃል እንገባለን፡፡

መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን የሕይወትዎ ጌታ በማድረግ ቀሪው ዘመንዎን ለመኖር ወስነው ከሆነ፣ ይህንን ሊንክ በመጫን ስምዎንና የኢ-ሜይል አድናሻዎን ይላኩልንና፣ ለመንፈሳዊ ሕይወት እድገትዎ የሚቻለንን ሁሉ እገዛ እናደርግሎታለን።

Leave a Reply

%d bloggers like this: