የመንፈስ ቅዱስ ግብር

በብሉይ ኪዳን ወቅት አብ በግልጽ ይታይ ነበር፡፡ ኢየሱስ በምድር ላይ በነበረበት ወቅት፣ ወልድ በግልጽ ይታይ ነበር፡፡ በአሁኑ ዘመን ደግሞ መንፈስ ቅዱስ በግልጽ ይታያል፡፡

ሀ) በብሉይ ኪዳን የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

– በፍጥረት ሥራ – ዘፍ 1፡2

– ትንቢትን በመስጠት – ሕዝ 2፡2፤ 8፡3፤ 11፡1-5

በልአም – ዘኁ 24፡2-9

ሳኦል – 1ሳሙ 10፡6፣ 10

ዳዊት – ሐዋ 1፡16

– ችሎታን በመስጠት

ለባስልኤል የግንባታ ጥበብ – ዘጸ 31፡2-5

– የመንግስት አስተዳደር ጥበብ

የሴፍ – ዘፍ 41፡38-44

ሙሴና 70ዎቹ ሽማግሌዎች – ዘኁ 11፡14-17፣ 25-29

ጎቶንያል – መሳ 3፡9-10

ሳምሶን – መሳ 14፡19፣ 15፡14

ዳዊት – 1ሳሙ 16፡13

ጌዴዎን – መሳ 6፡34

ሳኦል – 1ሳሙ 10፡10

– አኗኗርን በመቀየር

ፍትህ፣ ጻድቅና ሰላም – ኢሳ 32፡15-20

ለጌታ አምልኮ – ኢሳ 44፡3-5

አዲስ ልብ – ሕዝ 36፡26-28

ለ) መንፈስ ቅዱስ ከቅዱሳት መጻሕፍት ጋር ያለው ግንኙነት

– የቅዱሳት መጽሐፍ ደራሲ

መንፈስ ቅዱስ ሰዎች ስለ እግዚአብሔር እንዲናገሩ መራ – 2ጴጥ 1፡20-21

ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ የ “እግዚአብሔር እስትንፋ” (መንፈስ) ውጤቶች ናቸው – 2ጢሞ 3፡16

መንፈስ ቅዱስ በቅዱሳት መጻሕፍት ይናገራል – ራዕ 2፡7፣ 11፣ 17፣ 29

– የእግዚአብሔርን ጥበብ የሚፈታ (የሚገልጥ፣ የሚያብራራ) – 1ቆሮ 2፡9-14፤ ኤፌ 1፡17፤ ዮሐ 15፡26-16፡15

ሐ) ኢየሱስ በምድር ላይ በነበረ ጊዜ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

– መንፈስ ቅዱስ በኢየሱስ አገልግሎት ውስጥ የነበረው ሚና

ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስ ተጸነሰ – ሉቃስ 1፡35፤ ማቴ 1፡18

ኢየሱስ መንፈስ ቅዱስን በጥምቀቱ ወቅት ተቀበለ – ሉቃስ 3፡21-22

ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስ በሰይጣን ይፈተን ዘንድ ወደ ምድረበዳ ተመራ – ማር 1፡12፤ ማቴ 4፡1

ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስ ሃይል ተጓዘ – ሉቃስ 4፡14

ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስ ቅባት ሰበከ – ሉቃስ 4፡18

ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስ አጋንንትን አስወጣ – ማቴ 12፡28

ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስ ሃሴት አደረገ – ሉቃስ 10፡21

ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስ ከሞት ተነሳ – ሮሜ 8፡11

– መጥምቁ ዮሐንስ

በማሕፀን ውስጥ ሳለ በመንፈስ ተሞላ – ሉቃስ 1፡15

መንፈስ ቅዱስ በኢየሱስ ላይ ሲመጣ አየ – ማቴ 3፤ 16፤ ዮሐ 1፡31

ኢየሱስ በመንፈስ ያጠምቃል ብሎ መሰከረ – ማር 1፡7-8

መ) በቤተ ክርስቲያን ዘመን የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

– መንፈስ ቅዱስ፣ ከእስራኤል ሌላ በእግዚአብሔር መንግስት ውስጥ ድርሻ ያላቸው መኖራቸውን አስታወቀ።

– የአሕዛብ መካተት ምስጢር – ኤፌ 3፡5-8

– በአሕዛብ ሁሉ ላይ የመንፈስ ቅዱስ መፍሰስ – ኢዩ 2፤ 28 ከ ሐዋ 2፤ 16-18 ጋር

ሠ) ስለ መንፈስ ቅዱስ የአስተምህሮ ምንባብ – ዮሐ 14፡16-16፡15

በኢየሱስ ስም ከአብ ዘንድ የተላከ – ዮሐ 14፡26

ከአብ ዘንድ በኢየሱስ የተላከ – ዮሐ 15፡26

ስለ ኢየሱስ የሚመሰክር – ዮሐ 15፡26-27

ኃጢአተኞችን የሚወቅስ – ዮሐ 16፡7-8

ወደ እውነት የሚመራን – ዮሐ 16፡13

ስለ አብና ወልድ የሚናገር – ዮሐ 16፡14-15

ረ) ስለ መንፈስ ቅዱስ ግብር የአስተምህሮ ምንባብ – ሮሜ 8፡1-39

ከኃጢአትና ከሞት ሕግ ነፃ አወጣን – ሮሜ 8፡2

የሕግን ፈቃድ በመንፈስ በመጓዝ እናሟላለን – ሮሜ 8፡4 ለ

ሰውነታችን ሃይልን ይሰጣል – ሮሜ 8፡11

በመንፈስ ሰላምና ሕይወት አለን – ሮሜ 8፡5-6

ክፉ ተግባሮቻችን በመንፈስ ተወግደዋል – ሮሜ 8፡13

በድካማችን እንድንጸልይ ይረዳናል – ሮሜ 8፡26

በመንፈስ አማካኝነት የእግዚአብሔር ልጆች እንጂ ባሮች አይደለምን – ሮሜ 8፡15-17

ሰ) መንፈስ ቅዱስ በኤፌሶን መጽሐፍ

የእግዚአብሔር መሆኔን በምን አውቃለሁ? በክርስቶስ፣ በመንፈስ – ኤፌ 1፡13-14

መንፈስ እንዴት ይረዳናል? የጥበብና የመገለጥን መንፈስ በመስጠት – ኤፌ 1፡17

በሰማይ ወደ አለው አብ እንዴት መቅረብ እችላለሁ? በመንፈስ ወደ አብ መግባት እንችላለን – ኤፌ 2፡18

እግዚአብሔር በመካከላችን (በቤተ ክርስቲያን በመቅደሱ) እንዴት ይኖራል? እግዚአብሔር በመንፈስ አማካኝነት በመካከላችን ያድራል – ኤፌ 2፡22

አሕዛብ በኢየሱስ አማካኝነት ምህረት እንደ ተደረገላቸው እግዚአብሔር እንዴት ገለጠው? የእግዚአብሔር መንፈስ ለሐዋሪያትና ነቢያት ገለጠው – ኤፌ 3፡4-6

ኢየሱስ በልባችን ይኖር ዘንድ እንዴት ልንጠነክር እንችላለን? የእግዚአብሔር መንፈስ በውስጥ ሰውነታችን ያጠነክረናል – ኤፌ 3፡16-17

በውስጣችን ካለው የእግዚአብሔር መንፈስ ጋር እንዴት በሰላም እንኖራለን? መራርነትና ንዴት የመሰሉትን በማስወገድ – ኤፌ 4፡30-32

ለሕይወቴ የእግዚአብሔር ፈቃድ ምንድን ነው? በመንፈስ ቅዱስ እንድሞላ – ኤፌ 5፡17-18

ከመከላከያ የዘለለው የእግዚአብሔር የጦር እቃ ምንድን ነው? የመንፈስ ሰይፍ (የእግዚአብሔር ቃል ) – ኤፌ 6፡17

– በመንፈስ ቅዱስ መጸለይ – ኤፌ 6፡18

– መንፈስ ቅዱስ ደኅንነታችንን (ድነታችንን) ያረጋግጥልናል/በሕይወታችንም እንድናጣጥመው ያደርገናል

– ስለኃጢአት፣ ጽድቅና ፍርድ ይወቅሰናል – ዮሐ 16፡7-8

– ከመንፈስ መወለድ አለብን – ዮሐ 3፤ 3-6፤ ቲቶ 3፡5

– ከዚህ ልደት በኋላ መንፈስ በአማኙ ውስጥ ያድራል/ይሞላል – ሐዋ 2፡4፤ ኤፌ 5፡18፤ 1ቆሮ 6፡19

– በኃጢአት ጸንቶ የማይኖር ሕይወት እንድንኖር ሃይል ይሰጠናል – ሮሜ 8፡2

– የእግዘዚአብሔርን አገልግሎት እንድናገለግል በሃይል ይሞላናል – ዮሐ 14፡11-17፤ ሐዋ 1፡8፤ 1ቆሮ 2፤ 4

– ይመራናል ያስተምረናል – ዮሐ 14፡26፤ 16፡13

– በአማኙ ሕይወት ውስጥ የመንፈስ ፍሬን ያፈራል – ገላ 5፡22-23

Leave a Reply

%d bloggers like this: