የእግዚአብሔር ስራ (ምግባሩ) ምነድን ነው?

ሀ) መግቢያ

– በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማያትን ፈጠረ – ዘፍ 1፡1 ይህ የሆነው ምናልባት መላዕክት በተፈጠሩበት ጊዜ ሊሆን ይችላል፡፡

– የምድርና ቅርብ ያሉ ሰማያት መፈጠር – ዘፍ 1፡1-31 ይህ ስለምድርና አካባቢዎ ስላሉ ፍጥረታት ይመለከታል

ለ) የፍጥረት ልደት

– እግዚአብሔር አጽናፈ አለሙን ካለመኖረ ወደ መኖር አመጣ – ዘፍ 1፡1፤ ኢሳ 42፡5፤ ዓሞጽ 5፡8

እግዚአብሔር ሁሉን ነገር ደግሞ ሊያበጅ ይችላል (ያበጃልም) – አሳ 65፡17፤ ራዕ 21፡1

– የተፈጠረው ነገር ሲፈጠር እጅግ መልካም ነበር – ዘፍ 1፡31 የክፋት ችግር ከዚህ የፍጥረት ልደት በኋላ የመጣ ነው የክፋት ችግር ከሰው እንጂ ከእግዚአብሔር አልመጣም

– የፍጥረት ባለቤት አብ – ሮሜ 11፡36 ወልድ፣ ቃሉ – ዮሐ 1፡1-3 መንፈስ ቅዱስ – ዘፍ 1፡2

– በምድር ለሚኖሩ ሕዝቦች እስትንፋስን የፈጠረ እግዚአብሔር ነው – ኢሳ 42፡5፤ ዘካ 12፡1

– መንፈሳዊ ሃይላትንና ስልጣናትን የፈጠረው እግዚአብሔር ነው – ቆላ 1፡16-17 እግዚአብሔር ብቻውን መናፍስትን ሊያጠፋ ይችላል – ማቴ 10፡28፤ ሉቃስ 12፡4-5

– እግዚአብሔር በአፉ ቃል ፈጠረ – ዘፍ 1፡3፤ መዝ33፡6፣ 9፤ ዕብ 11፡3 እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ፣ አላማና ጥበብ – ኤፌ 1፡11፤ ራዕ 4፡11

– እግዚአብሔር የሁሉ ነገር ፈጣሪ ስለሆነ፣ ከዋክብትን፣ መናፍስትን፣ ጣኦትን፣ ሰዎችን፣ እፅዋትን ወይም እንስሳትን ልናመልካቸው አይገባም – ሮሜ 1፡20-25

ሐ) መግቦቱና መገኘቱ አይቋረጥም

– እግዚአብሔር ሁሉን ነገር በቃሉ ደግፎ ይይዛል – ዕብ 1፡3

– እርሱ ለሁላችንም ቅርብ ነው – ሐዋ 17፡27-28

በተለይም ለአማኞች ግድ ይለዋል – ዕብ 13፡5

እንደያዕቆብ፣ መገኘቱን ላናስተውል እንችላለን – ዘፍ 28፡16

– የምንኖረው በእግዚአብሔር ያልተቋረጠ መግቦት ነው – መዝ 36፡6

– እግዚአብሔር ፍላጎቶችን ይሞላል – መዝ 23፡1-6፤ 147፡1-9፤ 1ጴጥ 5፡6-7፤ ማቴ 5፡45፤ 6፡25-34፤ ሐዋ 14፡17

– እግዚአብሔር ይጠብቀናል ያድነናል – ዘፍ 28፡15፤ ዘዳ 32፡11፤ ኢሳ 25፡4፤ ማቴ 23፡37፤ ዮሐ 17፡11፤ ፊል 4፡6-7፤ 2ተሰ 3፡3፤ ይሁዳ 24-2

– እግዚአብሔር አንዳንድ ጊዜ ከተፈጥሮ ሥርዐት ውጪ በተአምራት ይሰራል – ክፍል ለ2

መ) እግዚአብሔር ድነትን ለሁሉ አቅርቧል – ክፍል ሠ

ሠ) እግዚአብሔር በሚከተሉት መልኮች ከሰው ልጅ ጋር ሕብረት ማድረጉን አላቋረጠም፡

– እንደ አባት – የእግዚአብሔር አባትነት የሚለውን ይመልከቱ – ክፍል ለ7

– እንደ ፈጣሪ – የፍጥረት ልደት የሚለውን ይመልቱ

– እንደ ባል – ለእስራኤል – ኤር 3፡20

– እንደ ንጉስ – የእግዚአብሔር መንግስት የሚለውን ይመልከቱ – ክፍል መ6

– እንደ ፈራጅ – ሞትና የመጨረሻው ዘመን የሚለውን ይመልከቱ – ክፍል ሸ

– እንደ አዳኝ – ደኅንነት የሚለውን ይመልከቱ – ክፍል ሠ

– እንደ መምህር – መንፈስ ቅዱስ/የእግዚአብሔር ቃል የሚለውን ይመልቱ – ክፍል ለ12 እና ለ13

– እንደሙሽራና ባል – ሞትና የመጨረሻው ዘመን የሚለውን ይመልከቱ – ክፍል ሸ

ረ) እግዚአብሔር ሰማያትና እና ምድርን ዳግመኛ ይፈጥራል – ራዕ 21፡5

– የመጀመሪያው ሰማይና የመጀመሪያው ምድር ይጠፋሉ – ራዕ 21፡1

– አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር – ራዕ 21፡1፣ 5፤ ኢሳ 65፡17 –

በእዚያ ሃዘን፣ ሞትና በሽታ የሉም – ራዕ 21፡4

– እኛም ኢየሱስን እንመስላለን – 1ዮሐ 3፡2

Leave a Reply

%d bloggers like this: