የኀጢአት ምንነት

ሀ) ሃጢአት ማለት ምን ማለት ነው?

የሚከተሉት ንዑስ ርዕሶች ኀጢአትን ይበይናሉ፡፡ ኀጢአት በእግዚአብሔር ማመጽ ማለት ነው፡፡ ሁሉ ኃጢአትን ስለሠሩ (ሮሜ 3፡23)፣ ከእግዚአብሔር ፍቅር በመለየት ሁሉም ከአግዚአብሔር ጋር ጠላቶች ሆነዋል – ዘዳ 9፡7-8፤ ኢያሱ 1፡18፤ ኢሳ 59፡2

– የመጀመሪያው ኀጢአት ግንኙነታችንን አበላሸ – ዘፍ 3፡1-24

– ጣኦትን ማምለክ ኃጢአት ነው – ዘጸ 32፡31፤ 1ነገ 12፡28-30፤ ኢሳ 31፡7፤ ኤር 17፡3፤ 32፡3፤ 32፡35፤ ሕዝ 23፡49፤ ሆሴዕ 13፡2

– ለሃሰተኛ አማልክት ዕጣን ማጠን ኃጢአት ነው- ኤር 44፡23

– ጥንቆላ ኃጢአት ነው- 1ሳሙ 15፡23

– ሕግን መተላለፍ ኃጢአት ነው – ዘሌ 16፡16፤ ነህ 1፡6-7፤ 1ዮሐ 3፡4

– ለእግዚአብሔር ትዕዛዛት አለመታዘዝ ኃጢአት ነው – ዘጸ 9፡27፣ 34፤ 10፡16-17፤ ዘሌ 5፡17

– ኀጢአት ባለማስተዋል (ሳያውቁ) ሊሰራ ይችላል – ዘሌ 4፡2፣ 13፣ 22፣ 27፤ 5፡15፣ 17

– ኀጢአት በድብቅ ሊሰራ ይችላል – መዝ 90፡8፤ ምሳሌ 28፡13

– ዐመጽ ሁሉ ኃጢአት ነው- 1ዮሐ 5፡17

– ወሲባዊ ኢ-ሞራላዊነት ኃጢአት ነው፣ ትዳርና ቤተሰብ የሚለውን ርዕሰ ጉዳዩ ይመልከቱ – ክፍል ሰ9.

– ግብረ ሰዶማዊነት ኃጢአት ነው – ዘፍ 9፡22፤ 18፡20፤ 19፡5-9፤ ዘሌ 18፡22፤ ሮሜ 1፡24-27፤ 1ቆሮ 6፡9

– ከእንስሳት ጋር ወሲብ መፈጸም ኃጢአት ነው – ዘሌ 18፡23

– ከዘመድ ጋር ወሲብ መፈጸም – ዘፍ 19፡33-39፤ ዘሌ 18፡6-20

– በዘመድ መካከል በተደረገ ግንኙነት የተገኘ ዘር ኀጢአት ነው (ሞአብና አሞን) – ዘዳ 23፡3፤ መሳ 10፡6፤ 1ነገ 11፡4፣ 7፤ 2ነገ 21፡

– ምንዝርና ኃጢአት ነው – ማቴ 5፡32፤ ሐዋ 15፡20-29፤ 1ቆሮ 5፡1፣ 11፤ 10፡8

– ጣኦት ማምለክ ኃጢአት ነው – ዘፍ 20፡7-9፤ 39፡7-10፤ 1ቆሮ 6፡9፤ 7፡2፤ ገላ 5፡19

– መልካምን ነገር ማድረግ እንዳለብን እያወቅን አለማድረግ ኃጢአት ነው – ዘሌ 5፡1፤ ያዕ 4፡17 (ባለማድረግ የሚሠራ ኀጢአት)

– የስንፍና አሳብ ኃጢአት ነው – ምሳሌ 24፡9

– ከንቱ ንግግር ወይም የቃል ብዛት ኃጢአት ነው – ምሳሌ 10፡19

– ንቀት፣ ትዕቢት ኃጢአት ነው – ምሳሌ 14፡21፤ 21፡4

– አለማመን እና ያለእምነት የሚደረግ እርምጃ (ድርጊት) ኃጢአት ነው – ሮሜ 14፡23፤ ዕብ12፡16፤ ራዕ 2፡14፣ 20፤ 9፡21

ለ) ኀጢአት በሚከተሉት መንገዶች ተገልጿል

– በአዳም አማካኝነት ወደ አለም ገባ – ዘፍ 3፡1,24፤ ኢሳ 43፡27፤ ሮሜ 5፡12

– የዲያብሎስ ነው – 1ዮሐ 3፡8፤ ዮሐ 8፡44

– የጨለማ ሥራ ነው – ኤፌ 5፡11-14

– ለማጥቃት በበር ቆሞ ያደባል – ዘፍ 4፡7

– ከልብ ይመነጫል – ማቴ 15፡19-20

– የምኞት ውጤት ነው – ያዕ 1፡15

– በዘር በኩል ይመጣል – ዘጸ 20፡5፤ መዝ 37፡28፤ ምሳሌ 14፡11

– የሰው ልጆች መከራና ጭንቀት ምክንያት ነው – ኢዮብ 15፡20፤ ምሳሌ 13፡15፤ ሮሜ 2፡9ማመካኛ የለውም – ሮሜ 1፡20፤ 2፡1፤ ዮሐ 15፡22

ሐ) ኀጢአት ያደረገ  ወይም ያለበት ማነው?

– ኀጢአትን ያላደረገው ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው – 2ቆሮ 5፡21፤ ዕብ 4፡15፤ ዕብ 7፡26፤ 1ዮሐ 3፡5

– ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ የሰው ልጅ ከኀጢአት በታች እንደሆኑ ይናገራሉ – ገላ 3፡22፤ መዝ 53፡3 ፤ ኢሳ 53፡6

– ሁሉ ኀጢአትን አድርገዋል – 1ዮሐ 1፡8፤ 1ነገ 8፡46፤ ሮሜ 3፡23

– በዘር ሁላችን ኀጢአተኞች ነን – ኢዮብ 15፡14፤ ኢዮብ 25፡4፤ መዝ 51፡5፤ ሮሜ 5፡12-19፤ 1ቆሮ 15፡21-22

– ሴት የኀጢአተኛው አዳም አምሳል ነበር – ዘፍ 5፤ 3

– በሁለንተናችን ኀጢአትን ሰርተናል

– በተግባራችን (በአካላችን /በሰውነታችን) – ገላ 5፡17-21

– በዝንባሌዎቻችን (በነፍሳችን) – ማቴ 5፡21-22፤ ያዕ 2፡8-9

– በኀጢአት ሁኔታ ውስጥ ነን (በመንፈሳችን) – ዮሐ 16፡8-9

– ስለዚህ ሁሉ ኀጢአተኛ ነው – ሮሜ 3፡23

መ) የኀጢአት ውጤት

– ከእግዚአብሔር ይለያል – ዘፍ 3፡23፣ 24፤ ኢሳ 59፡2

– ኀጢአተኞችን ከመንግስተ ሰማይ ይለያቸዋል – 1ቆሮ 6፡9፤ ገላ 5፡19-21፤ ኤፌ 5፡5-7፤ ራዕ 21፡27

– ሞትን ያመጣል – ዘፍ 3፡2-3፤ 19፤ ያዕ 1፡15፤ ሮሜ 6፡23፤ ሕዝ 18፡4

– የእግዚብሔርን ቁጣ ያመጣል – ዘጻ25፡16፤ ምሳሌ 6፡16-19፤ 1ነገ 16፡2

– የእግዚአብሔርን እርግማን ያመጣል

– ምድር በኀጢአት ምክንያት ተረገመች – ዘፍ 3፡17-18

– ድካምና ላብ የኀጢአት ውጤቶች ናቸው – ዘፍ 3፡16፣ 17፣ 19፤ ኢዮብ 14፡1

– በምጥ ጊዜ ሕመም የኀጢአት ውጤት ነው – ዘፍ 3፡16

– ፍጥረት በእስራት ውስጥ – ሮሜ 8፡21-22

– አደጋ ያስከትላል

– ድርቅ – ኤር 5፡24፤ 2ዜና 6፡26-28፤

– ጦርነት – 2ዜና 6፡36-39

– በሽታ – መዝ 38፡3

– አገራዊ ችግር – ምሳሌ 14፡34፤ ኤር 8፡14-16፤ 2ዜና 25፡4

– የእግዚአብሔርን ፍርድ ያመጣል

– የአሁን ጊዜ – ኢሳ 13፡11፤ አሞፅ 3፡2፤ ኤር 5፡25፤ ሉቃስ 12፡47፤ ሮሜ 2፡8-9

– የሚመጣ ጊዜ ቅጣት – ማቴ 18፡18፤ ማር 3፡29፤ ሉቃስ 3፡17፤ 2ተሰ 1፡9፤ 2ጴጥ 2፡9፤ ራዕ 14፡11፤ ራዕ 20፡15

ሠ) ለኀጢአት ችግር እግዚአብሔር ያዘጋጀው መፍትሄ

– ወንጌል የሚለውን ርዕስ ይመልከቱ – ክፍል ረ3 ፣ ረ4 ፣ ረ5

– ድነት የሚለውን ርዕስ ይመልከቱ – ክፍል ሠ2

– ሞትና የመጨረሻው ዘመን የሚለውን ርዕስ ይመልከቱ – ክፍል ሸ

1 thought on “የኀጢአት ምንነት”

  1. Pingback: ወንጌል በድረ-ገፅ አገልግሎት | Apostolic Servant of Lord

Leave a Reply

%d bloggers like this: