Site icon

የመጽሐፈ ኢያሱ ዋና ዓላማ

መጽሐፉ የተሰየመው፥ በመጽሐፉ ውስጥ በሚገኘው ዋና ተዋናይ በኢያሱ ቢሆንም፥ ትኩረቱ ግን በእርሱ ላይ ሳይሆን በእግዚአብሔር ላይ ነው። የእግዚአብሔር ሕዝብ መሪ የሆነውና የእስራኤልን ጦር በመምራት ድልን ያስገኘው እግዚአብሔር ነው። ኢያሱ በእግዚአብሔር ትእዛዝ ሥር ያለ ሰብአዊ መሪ በመሆኑ ትእዛዙን በቀጥታ ይፈጽም ነበር።

ከሌሎች መጻሕፍት (መጽሐፈ መሳፍንት፥ ሳሙኤልና ነገሥት) ጋር በአንድነት ሆኖ የመጽሐፈ ኢያሱ ዋና ዓላማ እግዚአብሔር በታሪክ ውስጥ ከእስራኤል ጋር የገባውን ቃል ኪዳን እንዴት እንደፈጸመ ማሣየት ነው። መጽሐፈ ኢያሱ የሚያሳየው፥ እስራኤላውያንን ወደ ከነዓን ምድር በማምጣትና ለአብርሃም ከብዙ መቶ ዓመታት በፊት የገባውን ቃል ኪዳን በመፈጸም፥ የቃል ኪዳን ተስፋዎቹን በታማኝነት እንዴት እንደጠበቀ ነው (ዘፍ. 15፡18-2)። የእግዚአብሔር ሕዝብ ምንም ያህል አስቸጋሪ ሆኖ ቢታይም፥ እግዚአብሔር ለሰጠው ተስፋ ታማኝ መሆኑን አሳየ።

መጽሐፈ ኢያሱ በጠላቶች ላይ ድል የሚገኘው በእግዚአብሔር ኃይልና አመራር ብቻ መሆኑን ያሳያል። ሕዝቡ በእርሱ ላይ በእምነት በሚደገፉበትና ሙሉ ለሙሉ እርሱን በሚታዘዙበት ጊዜ ብቻ ይፈጸማል። ኃጢአት የእግዚአብሔርን ሥራ የሚከለክል ሲሆን፥ እምነት ግን በእግዚአብሔር ሕዝብ መካከል የእግዚአብሔር ኃይል እንዲገለጥ ያደርጋል። ድል የሚገኘው በመታመንና በመታዘዝ ነው።

የውይይት ጥያቄ፥ ሀ) የመጽሐፈ ኢያሱ ዓላማ በመንፈሳዊ ሕይወት ጠላቶቻችን ላይ ድልን የማግኛ ምሥጢር ምን እንደሆነ የሚያስተምረን እንዴት ነው? ለ) ይህ በሕይወትህ ሲፈጸም ያየኸው እንዴት ነው? ሐ) እግዚአብሔር በሕይወትህ ስለሠራው ሥራ እርሱን ለማመስገን አሁኑኑ ጊዜ ይኑርህ።

(ማብራሪያው የተወሰደው በ ኤስ.አይ.ኤም ከታተመውና የብሉይ ኪዳን የጥናት መምሪያና ማብራሪያ፣ ከተሰኘው መጽሐፍ ነው፡፡ እግዚአብሔር አገልግሎታቸውን ይባርክ፡፡)

Exit mobile version