የ2ኛ ሳሙኤል ዋና ዋና ትምህርቶች 

ከ2ኛ ሳሙኤል የምንመለከታቸው ሦስት ዋና ዋና ትምህርቶች አሉ።

  1. ንጉሡ ዳዊት የእስራኤል የመጨረሻ ንጉሥ የሆነው የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነበር። ዳዊት በንጉሣዊ አስተዳደር የመጀመሪያው የእስራኤል ንጉሥ እንደሆነ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ መሢሑ የዳዊት ልጅም በእስራኤል ቤት ሁሉና በዓለምም ላይ የመጨረሻው ንጉሥ ነው።
  2. እግዚአብሔር ሰዎች ሁሉ ወዳጆቹ እንዲሆኑ ይፈልጋል።

አብርሃም የእግዚአብሔር ወዳጅ ነበር። ሙሴም እንደዚሁ ዳዊትም ደግሞ እንዲሁ ነበር። የእግዚአብሔር ወዳጅ መሆን ማለት ያለ ኃጢአት መሆንና ፍጹም ቅዱስ መሆን ማለት አይደለም፤ ነገር ግን እግዚአብሔርን በፍጹም ልባችን በመውደድ፥ ወደ ልባችን ለእግዚአብሔር ንቃት ኖሮት ኃጢአት ባደረግን ጊዜ ወዲያውኑ ንስሐ በመግባትና በማስተዋል ለእግዚአብሔር በመታዘዝ መኖር አለብን ማለት ነው። የቤተ ክርስቲያን መሪዎች የሆንን ሰዎች በተለይ ከእግዚአብሔር ጋር የቅርብ ግንኙነት ሊኖረን ይገባል። የእግዚአብሔር ወዳጆች መሆን ይጠበቅብናል።

የውይይት ጥያቄ፥ ሀ) የእግዚአብሔር ወዳጅ ነህን? መልስህን አብራራ። ለ) የእግዚአብሔር ወዳጅ ለመሆን ማድረግ ያለብህ ነገር ምንድን ነው?

  1. የእግዚአብሔር ሕዝብ መሪዎች ኃጢአት እንዳይሠሩ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው፤ ምክንያቱም በበርካታ ሰዎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርጉና የበርካታ ሰዎችን ሕይወት ሊያጠፉ ይችላሉና ነው። መሪዎች ለውድቀት ብዙ ጊዜ ቅርብ የሚሆኑት እጅግ ውጤታማና ስኬታማ ሲሆኑ ነው። በሚገባ እየታወቁና እግዚአብሔር በሥራቸው ከፍተኛ በረከት እየሰጣቸው ሲሄዱ ለመውደቅ የሚቃረቡት ያኔ ነው፤ ምክንያቱም ትዕቢት የሚሰማቸውና በራሳቸው ችሎታ መተማመን የሚጀምሩት ያኔ ነው። ዳዊት ውጤታማነቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ በደረሰ ጊዜ፥ በአመንዝራነትና በመግደል ኃጢአት ወደቀ። ውጤቱም እግዚአብሔር በእርሱ፥ በቤተሰቡና በአጠቃላይ በእስራኤል ሕዝብ ላይ ጥፋት አመጣ።

መጽሐፍ ቅዱስ «ስለዚህ እንደ ቆመ የሚመስለው እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ» ይላል (1ኛ ቆሮ. 10፡12)፤ ደግሞም «በሃይማኖት ብትኖሩ ራሳችሁን መርምሩ ራሳችሁን ፈትኑ» ተብለን ታዘናል (2ኛ ቆሮ. 13፡5)። በኃጢአት አንወድቅም ብለን የምናስብበት ጊዜ፥ ከየትኛውም ጊዜ በታላቅ ሁኔታ ለመውደቅ የምንችልበት ጊዜ ስለሆነ እንጠንቀቅ።

የውይይት ጥያቄ፥ ከ2ኛ ሳሙኤል ያገኘሃቸውንና ለቤተ ክርስቲያንህ መንፈሳዊ እድገት ለማስተማር የምትችላቸውን መንፈሳዊ እውነቶች በርዝር። 

(ማብራሪያው የተወሰደው በ ኤስ.አይ.ኤም ከታተመውና የብሉይ ኪዳን የጥናት መምሪያና ማብራሪያ፣ ከተሰኘው መጽሐፍ ነው፡፡ እግዚአብሔር አገልግሎታቸውን ይባርክ፡፡)

1 thought on “የ2ኛ ሳሙኤል ዋና ዋና ትምህርቶች ”

  1. ሠላም ሠላም
    ሠላም ለእናንተ ይሁን ወገኖቼ
    አንድ ጥያቄ ነበረኝ ይህውም የ2ኛ ሳሙኤል ዋና ዋና ትምህርቶች ላይ
    ባነበብኩት መረረት የእስራኤል የመጀመሪያ ንጉስ ዳዊት እንደሆነ ነው ያገኘሁት ።
    ሳኦል ከዳዊት በፊት አልነበረም እንዴ ?
    ይሄን ብታብራሩልኝ ?
    ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ይባርካችሁ ።

Leave a Reply to ማትዮስCancel reply

Discover more from

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading