የ2ኛ ነገሥት አስተዋጽኦ እና ዓላማዎች

የ2ኛ ነገሥት አስተዋጽኦ

  1. የመጨረሻው የኤልያስ አገልግሉትና ወደ ሰማይ መወሰዱ (2ኛ ነገ. 1-2፡18) 
  2. የጌታ ነቢይ የሆነው የኤልሳዕ አገልግሎት (2ኛ ነገ. 2፡19-8፡15) 
  3. የእስራኤልና የይሁዳ ነገሥታት እስከ እስራኤል ምርኮ ድረስ (2ኛ ነገ. 8፡16-17፡41) 

ሀ. የይሁዳ ንጉሥ ኢዮራም (8፡16-24) 

ለ. የይሁዳ ንጉሥ አካዝያስ (8፡25-29) 

ሐ. የእስራኤል ንጉሥ ኢዩ (9-10) 

መ. የይሁዳ ንግሥት ጎቶልያ (11) 

ሠ. የይሁዳ ንጉሥ ኢዮአስ (12) 

ረ. የእስራኤል ንጉሥ ኢዮአካዝ (13፡1-9) 

ሰ. የእስራኤል ንጉሥ ዮአስ (13፡10-25) 

ሸ. የይሁዳ ንጉሥ አሜስያስ (14፡1-22)

ቀ. የእስራኤል ንጉሥ ዳግማዊ ኢዮርብዓም (14፡23-29) 

በ. የይሁዳ ንጉሥ ዖዝያን (15፡1-7) 

ተ. የእስራኤል ንጉሥ ዘካርያስ (15፡8-12) 

ች. የእስራኤል ንጉሥ ሻሎም (15፡13-16) 

ኀ. የእስራኤል ንጉሥ ምናሔም (15፡17-22) 

ነ. የእስራኤል ንጉሥ ፋቂስያስ (15፡23-26) 

ኘ. የእስራኤል ንጉሥ ፋግፈ(15፡27-31) 

አ. የእስራኤል ንጉሥ ኢዮአታም (15፡32-38) 

ከ. የይሁዳ ንጉሥ አካዝ (16)

ኸ. የእስራኤል ንጉሥ ሆሴዕ (17፡1-6)

ወ. የእስራኤል መማረክ (17፡7-41) 

  1. ከሕዝቅያስ ጀምሮ ይሁዳ እስከተማረከች ድረስ የነበሩ የይሁዳ ነገሥታት (2ኛ ነገ. 18-25) 

ሀ. ሕዝቅያስ (18-20) 

ለ. ምናሴ (21፡1-18) 

ሐ. አሞን (21፡19-26)

መ. ኢዮስያስ (22፡23-30) 

ሠ. የይሁዳ ንጉሥ ኢዮአሐዝ (23፡31-35) 

ረ. የይሁዳ ንጉሥ ኢዮአቄም፡- የመጀመሪያው የባቢሎን ምርኮ (23፡36-24፡7) 

ሰ. የይሁዳ ንጉሥ ዮአኪን፡- ሁለተኛው የባቢሎን ምርኮ (24፡8-17) 

ሸ. የሴዴቅያስ በምርኮ ወደ ባቢሎን መወሰድ (24፡18-25፡21)

ቀ. በምርኮ ጊዜ የተፈጸሙ ድርጊቶች (25፡22-30) 

2ኛ ነገሥት የተጻፈባቸው ዓላማዎች 

  1. ከ853 ዓ.ዓ. ጀምሮ የእስራኤልና የይሁዳ መንግሥታት ወደ ምርኮ እስከ ተወሰዱበት ጊዜ ድረስ በእስራኤልና በይሁዳ የነገሡ ነገሥታትን ታሪክ በአጭሩ ለመተረክ ነው። 
  2. የእስራኤልና የይሁዳ መንግሥታት ወደ ምርኮ የተወሰዱበትን ምክንያት ለመግለጥ ነው። ይህ መጽሐፍ በግልጽ የሚያሳየው እስራኤልና ይሁዳ የጠፉት አሦርና ባቢሎን ታላቅ ስለ ነበሩ አለመሆኑን ነው። እንዲሁም አጋጣሚ ወይም ተፈጥሮአዊ የሆነ የታሪክ ክስተትም አይደለም። እስራኤልና ይሁዳ የጠፉት ትእዛዛቱን ስላልጠበቁ፥ እግዚአብሔር በቀጥታ ባመጣባቸው ፍርድ ነው። በእግዚአብሔር ላይ ዓመፁና በዚያ ፈንታ ሌሎች አማልክትን አመለኩ። 

የ2ኛ ነገሥት ታሪክ እግዚአብሔር በታሪክ ሁሉ ውስጥ ያለውን አመለካከት ያሳየናል። ታሪክ የነገሮች ተፈጥሮአዊ አፈጻጸም ብቻ አይደለም። አንድ ሕዝብ ሌላውን የሚወጋበት፥ አንድ ንጉሥም ሌላውን የሚገዛበት ታሪክ ብቻ አይደለም። ተፈጥሮአዊ የሆነ የድርቅ፥ የበሽታና የሞት ታሪክም አይደለም። ይህኛው ክርስቲያን ያልሆኑ ሰዎች ታሪክን የሚመለከቱበት መንገድ ነው። እግዚአብሔር ግን ታሪክን የሚመራ ነው። ራንና በሽታን የሚልክ እርሱ ነው። ጦርነቶችንና አሕዛብን ሁሉ የሚቆጣጠር እርሱ ነው። ሕዝቡ በምርኮ እንዲወሰዱ የሚፈቅድ እርሱ ነው። ክርስቲያኖች ግን በጎም ሆኑ ክፉ ነገሮችን ሁሉ ያያሉ። እንዲሁም የእግዚአብሔር እጅ በሥራ ላይ ሆኖ ማየት ይቻላል።

የውይይት ጥያቄ፥ ሀ) ክርስቲያኖች በታሪክ ላይ ይህን አመለካከት ማስታወስ የሚያስፈልጋቸው ለምንድ ነው? ለ) መንግሥት በትምህርት ቤቶች ካስተማረን ታሪክ እዚህ ያለው አመለካከት እንዴት ሊለያይ ቻለ? 

  1. ከምርኮ በኋላ የሚኖሩ እስራኤላውያንና ክርስቲያኖች ከእግዚአብሔር ቅጣት እንዳያገኛቸው ለእርሱ በመታዘዝ መኖር እንዳለባቸው ለማስጠንቀቅ ነው። 

የውይይት ጥያቄ፥ ሀ) ክርስቲያኖች የ2ኛ ነገሥትን እውነት ማወቃቸው በጣም አስፈላጊ የሚሆነው ለምን ይመስልሃል? ለ) የእግዚአብሔር ፍርድ ሳይመጣባቸው በቅድስና ይኖሩ ዘንድ ይህንን መልእክት ለቤተ ክርስቲያንህ አባሉች ለማስተማር የምትችለው እንዴት ነው? 

የውይይት ጥያቄ፥ 2ኛ ነገሥት 1-8፡15 አንብብ። ሀ) በእነዚህ ዓመታት የተጠቀሱትን የተለያዩ ነገሥታት ዘርዝር። ለ) ባሕርያቸው ምን ይመስል ነበር? ሐ) ኤልሳዕ የሠራቸውን የተለያዩ ተአምራት ዘርዝር።

እንደምታስታውሰው፥ የ1ኛ ነገሥት መጨረሻና የ2ኛ ነገሥት መጀመሪያ የሚያተኩሩት ኤልያስና ኤልሳዕ በተባሉ ሁለት ነቢያት ላይ ነው። እነዚህ ሁለት ነቢያት በእስራኤል የሠሩና ሕዝቡን ወደ እግዚአብሔር ለመመለስ የጣሩ ነበሩ። የኤልያስ ታሪክ በአብዛኛው የሚገኘው በ1ኛ ነገሥት ውስጥ ነው። የሕይወቱ የመጨረሻ ታሪክ በ2ኛ ነገሥት 1-2 ውስጥ ይገኛል። 2ኛ ነገሥት 2-8 የሚያተኩረው ደግሞ በኤልሳዕ ታሪክ ላይ ነው።

(ማብራሪያው የተወሰደው በ ኤስ.አይ.ኤም ከታተመውና የብሉይ ኪዳን የጥናት መምሪያና ማብራሪያ፣ ከተሰኘው መጽሐፍ ነው፡፡ እግዚአብሔር አገልግሎታቸውን ይባርክ፡፡)

Leave a Reply

%d bloggers like this: