Site icon

1ኛ ዜና 1 እስከ 2ኛ ዜና መጨረሻ

በመጽሐፈ ዜና መዋዕል የሚገኙ አብዛኛዎቹ ታሪኮች ከመጽሐፈ ሳሙኤልና ከነገሥት ታሪክ የተደገሙ ስለሆኑ፥ ለሚቀጥሉት ሦስት ቀናት 1ኛና 2ኛ ዜና መዋዕልን በሙሉ በማንበብ ጥያቄዎችን ትመልሳለህ። እነዚህን ምዕራፎች በሚመለከት የሚሰጥ መግለጫ አይኖርም። 

1ኛ ቀን፡- 1ኛ ዜና 1 – 21

የውይይት ጥያቄ፥ ሀ) ከእነዚህ ምዕራፎች ስለ እግዚአብሔር የምንማራቸውን ነገሮች ዘርዝር። ለ) በእነዚህ ምዕራፎች እንደሚታየው፥ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኙ የተግባር ሰዎች ስለመሆን፥ ከዳዊት ሕይወት ምን መማር እንችላለን? ሐ) ከእነዚህ ጥቅሶች ስለ አምልኮ ልንማራቸው የምንችል አንዳንድ ነገሮች ምንድን ናቸው?

2ኛ ቀን፡- 1ኛ ዜና 22 – 2ኛ ዜና 9

የውይይት ጥያቄ፥ ሀ) ከሰሎሞንን ሕይወት እግዚአብሔርን ስለማገልገል የምንማራቸውን ነገሮች ዘርዝር። ለ) ከእነዚህ ምዕራፎች ስለ አምልኮ ልንማራቸው የምንችል አንዳንድ ነገሮች ምንድን ናቸው? ሐ) በእነዚህ ምዕራፎች ውስጥ ሕይወትህን የነኩትን መንፈሳዊ ትምህርቶችን ዘርዝር። 

3ኛ ቀን፡- 2ኛ ዜና 10-36

የውይይት ጥያቄ፥ ሀ) ከእነዚህ ምዕራፎች ስለ እግዚአብሔር ልንማራቸው የምንችል ነገሮችን ዘርዝር ለ) ለመንፈሳዊ መሪነት መልካም ምሳሌ የሚሆኑ የነገሥታትን ስም ዘርዝር። ከአመራራቸው የምንማረው ነገር ምንድን ነው? ሐ) ከእነዚህ ምዕራፎች ስለ አምልኮ የምንማረው ነገር ምንድን ነው? መ) ከእነዚህ ጥቅሶች ስለ ንስሐ ልንማራቸው የምንችል አንዳንድ ነገሮችን ጥቀስ። 

Exit mobile version