የመጽሐፈ ዕዝራ አስተዋጽኦ እና አላማ

የመጽሐፈ ዕዝራ አስተዋጽኦ

  1. የመጀመሪያው የአይሁድ ቡድን ከምርኮ መመለስና የቤተ መቅደሱ እንደገና መሠራት (ዕዝራ 1-6)፡-

ሀ. የምርኮኞቹ መመለስ (1) 

ለ. ከምርኮ የተመለሱት ሰዎች ዝርዝር (2) 

ሐ. የመሠዊያው መሠራትና የቤተ መቅደሱ ሥራ መጀመር (3)

መ. በቤተ መቅደሱ ሥራ ላይ የደረሰው ተቃውሞና በአይሁድ ላይ የደረሱ ሌሎች ተቃውሞዎች (4፡1-23)

ሠ. የቤተ መቅደሱ ሥራ መፈጸም (4፡24-6፡22)። 

  1. ሁለተኛው የአይሁድ ቡድን በዕዝራ መሪነት ከምርኮ መመለሱና መንፈሳዊው ተሐድሶ (7-10) 

ሀ. ለመመለስ የሚያስችል ፈቃድ (7) 

ለ. የተመለሱት ሰዎች ስም ዝርዝር (8)

ሐ. ዕዝራ በኢየሩሳሌም የቀሰቀሰው ተሐድሶ (9-10) 

የመጽሐፈ ዕዝራ ዋና ዋና ዓላማዎች

መጽሐፈ ዕዝራ የተጻፈባቸው ሁለት ዐበይት ምክንያቶች አሉ፡- 

  1. አይሁድ ከምርኮ ተመልሰው እንደገና በይሁዳ መኖር እንዴት እንደ ጀመሩ ለመናገር ነው። በሁለት ክፍለ ጊዜያት የተከፈለ ሲሆን አንዱ በዘሩባቤል፥ ሌላው ደግሞ በዕዝራ መሪነት ከምርኮ ስለተመለሱት አይሁድ ይናገራል። ይህ ታሪክ ከ538-456 ዓ.ዓ. የተፈጸመው ነገር ባጭሩ የቀረበበት ነው።
  2. የዕዝራ መልእክት የተጻፈው በይሁዳ ይኖሩ ለነበሩት አይሁዳዊያን ጭምር ሲሆን፥ እግዚአብሔር ሊሠራ የጀመረውን ነገር እንደተወና እንደረሳቸው ተሰምቶአቸው እጅግ ተስፋ ቆርጠው ስለነበር፥ እነርሱን ለማበረታታት ነበር። ጸሐፊው እግዚአብሔር በነቢያት በኩል የተናገረውን ትንቢት ለመፈጸም ታማኝ እንደሆን ሊያሳያቸው ፈልጎ ነበር (ለምሳሌ፡- ኢሳ. 43፡1-7)። ይህም ትንቢት አንድ ቀን እግዚአብሔር ሕዝቡን ከምርኮ እንደሚመልስ የሚናገር ነበር። እግዚአብሔር እስካሁንም ድረስ በአይሁድ ታሪክ እየሠራ ነበር። የቤተ መቅደሱ ሥራ እግዚአብሔር በመካከላቸው እንደሚሠራ የሚያሳይ አንዱ ምልክት ነበር። ጸሐፊው የዚህን ዘመን ታሪክ በመጠቀም፥ ሕዝቡ የእግዚአብሔርን በረከት ለመለማመድና የይሁዳ መንግሥትም ቀድሞ ወደነበረው ታላቅነት እንዲመጣ ከፈለጉ፥ የቃል ኪዳኑ ሕዝብ እንደመሆናቸው መጠን ለእግዚአብሔር በመታዘዝ መኖር እንደነበረባቸው ለማስጠንቀቅ ፈልጎአል። የንጽሕና ሕይወት መኖር አለባቸው።

የውይይት ጥያቄ፥ ሀ) በግል ሕይወታችን፥ በቤተ ክርስቲያናችንና በኅብረተሰባችን ውስጥ የምናገኘው በረከት ለእግዚአብሔር ቃል ከመታዘዛችን ጋር የሚያያዘው እንዴት ነው? ለ) ለእግዚአብሔር ለመታዘዝ በሕይወትህ ውስጥ ልትለውጣቸው ከሚገቡ ነገሮች አንዳንዶቹን ጥቀስ። ሐ) በተሻለ ሁኔታ ለእግዚአብሔር ለመታዘዝ በቤተ ክርስቲያንህ ውስጥ ልታደርጋቸው የሚገቡ አንዳንድ ነገሮችን ጥቀስ።

(ማብራሪያው የተወሰደው በ ኤስ.አይ.ኤም ከታተመውና የብሉይ ኪዳን የጥናት መምሪያና ማብራሪያ፣ ከተሰኘው መጽሐፍ ነው፡፡ እግዚአብሔር አገልግሎታቸውን ይባርክ፡፡)

Leave a Reply

%d bloggers like this: