ሀ. የሥፍሩ-ዘመናት ትርጉም
መጽሐፍ ቅዱስ በሚጠናበት ጊዜ የእግዚአብሔር ቃል መገለጥ ሥርዓትን በተከተስ መንገድ በተጎለጡ ወቅቶች መመደቡን መረዳት ይገባል። እነዚህ ጊዜያት የተለዩ በመሆናቸው በየምድባቸው ለይቶ ማወቁ የመለኮታዊ ዓላማ አሠራርን ሰመረዳትና ትክክለኛውን የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጓሜ ለማወቅ ወሳኝ ነው። እነዚህ የእግዚአብሔር የመለኮታዊ ዓላማና አሠራር ጊዜያት “ሥፍረዘመናት” ተብለው ይታወቃሉ። በመሆኑም በእግዚኦብሔር አሠራር ውስጥ ዘመናት የተለያየ ስፍራ ስላላቸውና፥ የሚስኩትም በእርሱ የሥራ ዘመን በመሆኑ ተከታታይ ሥፍረ-ዘመናት ተለይተው ይታያሉ።
ሥፍረዘመን ማለት ለየት ባሉ ዘመናት እግዚአብሔር ሰዎችን የመራበትና የሕይወት መመሪያ የሰጠባቸው የጊዚ ክልል ማለት ነው። በእያንዳንዱ ዘመን ውስጥ ሰዎች የእግዚአብሔር መመሪያን መከተል ተስኗቸው ወድቀዋል። ስለዚህ ከውድቀታቸው የተነሣ እያንዳንዱ ሥፍረ-ዘመን በእግዚአብሔር ፍርድ መገለጥ ያጠቃለሳል። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ሥፍረ- ዘመን” እና “ዘመን አንድ አይደሉም። ነገር ግን እያንዳንዱ ዘመን የራሱ የሆነ ሥፍረ-ዘመን ኦለው። ዘመናት መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተጠቅሰዋል (ኤፌ. 2፡7፤ 3፡5፡9፤ ዕብ. 1፡2)። ዘመናት መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተለይተዋል (ዮሐ. 1፡17ን፤ ከማቴ. 5፡21-22፤ 2ኛ ቆሮ. 3፡11፤ እና ከዕብ. 7፡11-12 ጋር አስተያዩ)።
ከሌላ ከማንኛውም የመጽሐፍ ቅዱስ አጠናን ዘዴ ይበልጥ የመጽሐፍ ቅዱስን መልእክቶች ለመረዳት የሚጠቅመውና ሰሚገባም የሚገልጠው፥ የእግዚአብሔርን አሠራር ሥፍረ-ዘመናት ማወቅና መረዳት ነው። (* አውግስጢኖስ (354-430 ዓ.ም.) እንዲህ አለ፡- “በመጽሐፍ ቅዱስ የተጠቀሱ ዘመናትን በትክክል መለየት ከቻልኝ፥ የመጽሐፍ ቅዱስን የተያየዘና ወጥ መሆንን በደንብ እንረዳለን።”) የእግዚአብሔርን ሥፍረዘመናትና፥ ከእነርሱም ውስጥ የተገለጡትን መለኮታዊ ዓላማዎች ውጤቶች በቅድሚያ መረዳት ራሱ የመጽሐፍ ቅዱስን ጠቃሚ እውቀት የመረዳት መጀመሪያ ከመሆኑም ባሻገር፥ ለመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ያለንን ፍላጎት ይቀሰቅሳል። የሰውና የእግዚአብሔር ግንኙነት በየዘመናቱ ሁሉ አንድ ዓይነት አይደለም። በኃጢአት የተበከለውን ሰው በመለኮታዊ ሚዛን ውስጥ አስገብቶ መፈተን አስፈላጊ ነው። ይህ ደግሞ በከፊል በየዘመናቱ የሚታይ የእግዚአብሔር ዓላማ ነው። የፈተናውም ውጤት የሚያሳየው፥ ሰው በማያጠያይቅ ደረጃ ፍጹም በሆነ የውድቀትና የኃጢአተኛነት ሕይወት ውስጥ መሆኑን ያረጋግጣል። በመጨረሻም ሰው ሁሉ የልቡ ምኞትና አሳብ ስንፍናና ቅድስና እንደጎደለው በየዘመናቱ የተረጋገጠ መሆኑ የሚያስደንቅ እውነት ነው።
እያንዳንዱ ሥፍራ-ዘመን የሚጀምረው ሰው አዲስ መብትና ኃላፊነት ውስጥ በመግባቱ ነው። ሥፍራ- ዘመኑ የሚያበቃው ደግሞ፥ ሰው የተሰጠውን ልዩ መብትና ኃላፊነት መወጣት ተስኖት በእግዚአብሔር ጻድቅ ፍርድ ሥር ሲሆን ነው። በየዘመናቱ ሁሉ ለሰው ዘር የሚሰጡ የተለያዩ አመራሮችና ኃላፊነቶች እንደየዘመናቱ ቢለያዩም፥ ዘላለማዊው የእግዚአብሔር የቅድስና ባሕርይ ግን እይላውጥም።
ከዚህ ጋር በተያያዘ ሁኔታ፥ ማንኛውም የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪ፥ የእግዚአብሔር ቃል መጀመሪያም ሆነ በሁለተኛ ደረጃ የተነገረው ለማን መሆኑን መረዳት ይኖርበታል።
የእግዚአብሔር ልጅ የሆነ ሰው ሁሉ ሰቀጥታ ላለበት ዘመን የሚመለከተውን ብቻ መጠቀምና መከተል ይገባዋል። እነዚህን የቃሉን መመሪያዎች ሙሉ በሙሉ እንዲፈጽም ይጠበቅበታል። በሁለተኛ ደረጃ መታየት ያለበት ደግሞ፥ ማንኛውም ክርስቲያን በሌሉች ዘመናት የተሰጡትን ሕጎችና መመሪያዎችን እንደ መንፈሳዊ ትምህርት ሊወስዳቸው ይችላል። በሌሎች ዘመናት ሰዎች እንዲመሩበት ጌታ የሚፈልገው ዓይነት ኑሮን ይኖር ዘንድ እግዚአብሔር አልመረጠውም። መገንዘብ ያለብን መጽሐፍ ቅዱስ የሁሉም ዘመናት ስለሆነ፥ ለሁሉም ዘመን የሚሆን መንፈሳዊ ትምህርት ያለው መሆኑን ነው። ለምሳሌ በዚህ ዘመን ያለ አማኝ፥ አዳም ወይም አብርሃም ወይም እስራኤላውያን በሕግ ይመሩ እንደነበረ የእግዚአብሔር ፈቃድና አሠራር በነበረበት ዘመን ሁኔታ ውስጥ አይደለም፤ ወይም ንጉሡ (ኢየሱስ) መጥቶ መንግሥቱን ምድር ላይ በሚመሠርትበት ወቅት የሚኖሩ ሰዎች ሊኖራቸው የሚገባን ልዩ ሕይወት እንዲኖርም አልተፈጠረም።
የእግዚአብሔር ልጅ ለዕለታዊ ሕይወቱ አጠቃላይ መመሪያ ለማግኘት የሚችለው ከመጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ነው። ነገር ግን የተለያዩ ዘመናት መመሪያዎችና ሕጎች በጣም የተለያዩና አንዳንዴም የሚቃረኑ ይሆናሉ። በዚህ ጊዜ የእግዚአብሔር የጸጋ ልጅ በቀጥታ እርሱን የሚመለከቱ የቃል ክፍሎች ለይቶ ቢያውቅ፥ የእግዚአብሔር ፈቃድና የእግዚአብሔር ክብር ምን እንደሆነ ተረድቶ በዚያው ለመመላለስ ይችላል። መጽሐፍ ቅዱስ የሚሰጠውን አጠቃላይ ምዕክርነት በምናይበት ጊዜ፥ አንድ አማኝ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ተረድቶ እርሱንም ለመፈጸም ይችል ዘንድ ሰቀጥታ የማይመለከተውን ክፍል ማወቁ የሚመለከተውን የማወቅ ያህል አስፈላጊና ጠቃሚ ነው። ስለዚህ አንድ አማኝ የሥፍረ ዘመናትን በቂ እውቀት ሳያገኝ በአሁኑ ዘመን የእግዚአብሔር ዓላማና ፈቃድ ምን እንደ ሆነ ተረድቶና አስተውሎ ራሱን ከሁኔታዎች ጋር ለማገናዘብ እይችልም። ይህ እውቀት ብቻ ነው በሕግ ይሆን የነበረውን ያለፈ ዘመንና፥ ገና ምንም ማድረግ የማይቻለውን መጪ ዘመን በማሰብ ልባችን እንዳይዝል የሚያደርገው።
መጽሐፍ ቅዱስ ወደተለያዩ ቋንቋዎች በሚተረጎምበት ጊዜ፥ የዘመናት ትክክለኛ መግለጫ የሆኑ እንዳንድ ቃላት እገባብ ትክክል ያለመሆኑ ችግር አለ። ለምሳሌ በግሪክ ቋንቋ “አዮን” የሚለው ቃል በአማርኛ “ዓለም” ተብሎ ተተርጉሟል። የቃሉ ትክክለኛ ትርጉም ግን “ዘመን” ወይም “ሥፍረ-ዘመን” ማለት ነው። ማቴዎስ ወንጌል 13፡49 ውስጥ የተጠቀሰው “በዓለም መጨረሻ እንዲሁ ይሆናል” የሚለው ሐረግ የሚያመለክተው፥ የቁሳዊውን ዓለም መጨረሻ (ኢሳ. 66 ፡22፤ 2ኛ ጴጥ. 3፡7፤ ራእይ 20፡11) ሳይሆን፥ ያለንበትን ዘመን መጨረሻ ነው። በመቃረብ ላይ ያለው የዓለም መጨረሻ ሳይሆን፥ የዘመኑ መጨረሻ ነው። በመጽሐፍ ቅዱሳችን መሠረት ሰባት ታላላቅ ሥፍረ-ዘመናት ያሉ ሲሆን፥ እኛ አሁን ያለንበት፥ የስድስተኛው ሥፍረ-ዘመን መዳረሻ ነው። የሺህ ዓመቱ መንግሥት ዘመን ገና ሊመጣ ነው (ራእይ 20፡4፥ 6)።
በመሠረቱ አንድ ሥፍረ-ዘመን ከሌላው የሚለየው፥ በአዲስ መለኮታዊ አሠራርና በምሪት መጀመሩና በእነዚህም ላይ በሚሰጠው መለኮታዊ ፍርድ በመጠናቀቁ ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ብዙዎች የሚረዷቸው ሰባት ሥፍረ-ዘመናት፡-(1). የንጽሕና ሥፍረ ዘመን፥ (2) የሕሊና ሥፍረ-ዘመን (3) የሰብአዊ መንግሥት ሥፍረ-ዘመን፥ (4) የተስፋ ሥፍረ-ዘመን፥ (5) የሕግ ሥፍረ-ዘመን፥ (6) የጸጋ ሥፍረ-ዘመን፥ (7) የሺህ ዓመት መንግሥት ሥፍረ-ዘመን ናቸው።
ዕባቱ ሥፍራ-ዘመናት ሰሚጠኑበት ጊዜ ትምህርቱን ለመረዳት የሚያግዙ አንዳንድ መመሪያዎች ያስፈልጋሉ። አንደኛው፥ የሥፍረ-ዘመናት ትምህርት የሚባለው ሲሆን፥ ይህ ትምህርት መጽሐፍ ቅዱስን የሚገነዘበው፥ ቃል በቃል በሆነ አተረጓጎም ላይ በመመሥረት ነው። ዘመናትንና በውስጣቸው የሚገኙትን ሥፍረ-ዘመናት በደንብ ለይተው ሳያውቁና ሳይረዱ፥ መጽሐፍ ቅዱስን በትክክል ለመረዳትና ለመተርጎም እይቻልም። ሁለተኛው መመሪያ፥ ተከታታይ መገለጥን የሚያሳይ ነው። ይህ በሁሉም የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎች ዘንድ በተጨባጭ ታይቷል። መገለጥ በየደረጃው የሚሰጥ መሆኑን የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎችም ተረድተዋል። ሦስተኛው መመሪያ፥ መጽሐፍ ቅዱስን የሚያብራሩ ሰዎች ሁሉ፥ ተከታዩ መገለጥ ቀዳሚውን ራእይ በመጠኑም ቢሆን የሚተካው መሆኑን ማወቅ ያጎባቸዋል የሚለው ነው። ምክንያቱም የመጀመሪያው መገለጥ በተሰጠበት ወቅት የነበረው ሁኔታ ሊለወጥ፥ ሊቀር ወይም ሌላ የሕይወት መመሪያና ደንብ ሊሰጥ ስለሚችል ነው። ለምሳሌ፥ በሰንበት ቀን እንጨት ሲለቅም በመገኘቱ ወደ ሙሴ ሰፍርድ የመጣው እስራኤላዊ በድንጋይ ተወግሮ እንዲገደል እግዚአብሔር ሙሴን እዞታል (ዘኁል. 15፡32-36)። ዛሬ ይህን ሕግ አንጠቀምበትም። ማድረግም አይገባም። ምክንያቱም በቃሉ መሠረት እኛ የምንኖረው፥ ፍጹም ልዩ በሆነ ሌላ ሥፍረ-ዘመን ውስጥ ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተለይተው የተመለከቱት ሰባት ሥፍረ-ዘመናት ቢሆኑም፥ ሦስቱ ግን ከሌሎቹ ይበልጥ ጠቃሚ ሆነው እናገኛቸዋለን። እነርሱም የሕግ ዘመን (ከሙሴ ጊዜ ጀምሮ እስራኤላውያን በብሉይ ኪዳን ዘመን የተመሩበት)፤ የጸጋ ዘመን (የአሁኑ ዘመን)፤ ወደፊት የሚመጣው እና የሺህ ዓመቱ መንግሥት ዘመን ናቸው።
ለ, የንጽሕና ሥፍረ-ዘመን፡- የነጻነት ዘመን
ይህ ዘመን ከሰው መፈጠር (ዘፍጥ. 1፡26፥ 27) ጀምሮ እስከ ዘፍጥረት ምዕራፍ 3 ቁጥር 6 ድረስ ይሄዳል። በዚህ ዘመን ስው ፍሬያማ እንዲሆን፥ ምድርን በሙሉ እንዲገዛ፥ በእንስሳት ላይ እንዲሠለጥን፥ አትክልትና ፍሬ እንዲመገብና የዔደን ገነትን የአትክልት ስፍራ እንዲጠብቅ ኃላፊነት ተሰጥቶት ነበር (ዘፍጥ. 1፡28-29፤ 2፥ 15)።
ሰው የተከለከው አንድ ነገር፥ ይኸውም መልካምና ክፉን ለመለየት እውቀት ከምትሰጥ የዛፍ ፍሬ እንዳይበላ ነበር (ዘፍጥ. 2፡17)። ምንም እንኳ ሰው የከበረ ስፍራ፥ ፍጹም አካል፥ አእምሮና ባሕርይ፥ እንዲሁም ሕይወትን የሚያረኩ ነገሮች ተስተካክለው ቢሰጡት፥ ሔዋን ተፈትና ተሸነፈችና ከተከለከለው ዛፍ ፍሬ በላች፤ አዳምም አብሮአት ሰመብላት ያለመታዘዝዋ ተባባሪ ሆነ (ዘፍጥ. 3፡1-6)። ከዚህም የተነሣ ውጤቱ ሰማያዊ ፍርድ፥ መንፈሳዊ ሞት፥ የኃጢአት እውቀት፥ እግዚአብሔርን መፍራትና የኅብረት መበላሸት ሆነ።
በእነዚህ ሁኔታዎች ውስጥ እንኳ እግዚአብሔር የጸጋውን መመሪያ፥ የአዳኝን ተስፋ (ዘፍጥ. 3፡15) ሰመስጠት መዳንን የሚያሳይ የቁርበት ልብስ አለበሳቸው (ዘፍጥ. 3፡21)። ከገነት ተባረሩ፤ የግል ሕይወታቸውን ከዚያ ውጪ እንዲመሩ ተፈረደባቸው (ዘፍጥ. 3፡23-24)። በእነርሱ ላይ በተሰጠው ሰዚህ የእግዚአብሔር ፍርድ የመጀመሪያው ሥፍረዘመን አበቃና እዲሱ ሥፍረ-ዘመን ተጀመረ። በዚህ የንጽሕና ሥፍረ-ዘመን እግዚአብሔር የሰውን ውድቀት እሳየ፥ የሚመጣውን አዳኝ ተስፋ ሰጠ፥ በፍጥረቱ ላይ በመፍረዱ ደግሞ ሉዓላዊነቱን (ታላቅነቱን) አስመሰከረ፥ የጻጋውንም መመሪያ ጀመረ።
ሐ. የሕሊና ሥፍረ-ዘመን፡የሰው የመምረጥና የመወሰኝ ዘመን
ይህ ሥፍረዘመን የሚያመለክተው፥ እግዚአብሔር ከአዳምና ከሔዋን ጋር የገባውን ቃል ኪዳን ሲሆን፥ ከኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ 3 ቁጥር 7 ጀምሮ እስከ ምዕራፍ 8 ቁጥር 19 ይደርሳል። በዚህ ጊዜ ሰው ፍጹም አዲስ የሆነ ኃላፊነት ተሰጠው። ሰይጣን ተረጎመ (ዘፍጥ. 3፡14-15)፥ በአዳምና በሔዋን ላይም እርግማን ወደቀባቸው (ዘፍጥ. 3፡16-19)። እርግጥ በዚህ ጊዜ ሰው በዝርዝር የተገለጡ ሕጎች ባይሰጡትም፥ ከርሱ የሚፈለገው በተሰጠው የሕሊና ነጻነት መሠረት፥ እግዚአብሔር በገለጠለት እውቀት መጠን መኖር ብቻ ነበር።
በዚህ ሰሕሊና ዘመንም ቢሆን ሰው ከዚያ በፊት እንደለመደው በመተላለፍ ኃጢአት መውደቁን ቀጠለ። ሕሊና ይወቅሳል እንጂ ለድል አያበቃም (ዮሐ. 8፡9፤ ሮሜ 2፡15፤ 1ኛ ቆሮ. 8፡7፤ 1ኛ ጢሞ. 4 ፡2)። የአዳም ልጆች ከአባታቸው የወረሱት የኃጢአተኛነት ባሕርይ ቃየን የደም መሥዋዕት ባለማቅረቡ (ዘፍጥ. 4፡7) የተገለጠ ሲሆን፥ ውጤቱም አቤልን በመግደሉ ተረጋገጠ (ዘፍጥ. 4፡8)። ከዚህ የተነሣ የቃየን ሥልጣኔ ውጤት ኃጢአተኛነት ነበር (ዘፍጥ. 4፡16-24)፤ አካላዊ ሞትም የተለመደ ሆነ (ዘፍጥ. 5፡5-31)። የሰው ልብ ጠማማነት ይህን ያህል ከፍተኛ ደረጃ ላይ በመድረሱ እንደገና ፍርድ አስፈለጎ (ዘፍጥ. 6፡5፥ 11-13)። ፍርዱም በቃየን ላይ ተገለጠ (ዘፍጥ. 4፡10-15)፥ በአጠቃላይም በሰው ዘር ላይ ሞት ሆነ (ዘፍጥ. 5)። በመጨረሻም እግዚአብሔር በምድር ላይ ታላቁን የጥፋት ውኃ ማምጣት ነበረበት (ዘፍጥ. 7፡21-24)።
በዚህ ዘመን ሳይቀር የእግዚአብሔር መለኮታዊ ጸጋ ሄኖክን በማዳኑና (ዘፍጥ. 5:24)፥ የኖኅን ቤተሰቦች መርከብ ውስጥ ሰውሮ ማዳኑ ተገልጧል (ዘፍጥ. 6፡8-10፤ ዕብ. 11፡7)። ሁላችንም እንደምናውቀው ይህ ሥፍረ-ዘመን በጥፋት ውኃ አማካይነት በተገለጠው ፍርድ ሲጠናቀቅ፥ ኖኅና ቤተሰቦቹ ብቻ ድነዋል።
በዚህ ዘመን የእግዚአብሔር ዓላማ፥ የሰውን ውድቀት በሕሊናው በሚመራበት ሰአዲሱ ሁኔታ ውስጥ ላማሳየት ነበር። ቢሆንም እግዚአብሔር በዚህ ዘመን ሊመጣ ያለውን እዳኝ የትውልድ ሐረግ ይጠብቃል። ዓለሙን በሙሉ በጥፋት ውኃ ሰመቅጣት የራሱን ታላቅነት እሳየ፥ ለኖኅና ለቤተሰቡም ጸጋውን ገለጠ።
መ. የሰው መንግሥት ሥፍረ-ዘመን፡- ከኖኅ ጋር የተደረገ ቃል ኪዳን
ይህ ሥፍረ-ዘመን ከዘፍጥረት ምዕራፍ 8 ቁጥር 20 ጀምሮ እስከ ዘፍጥረት ምዕራፍ 11 ቁጥር 9 ድረስ ያለውን ጊዜ ያጠቃልላል። እግዚአብሔር፥ ለኖኅ የማይፈርስ ቃል ኪዳን (ዘፍጥ. 8፡20-9፡17) የገባለት ሲሆን፥ ከእንግዲህ ወዲያ ምድርን በጎርፍ እንደማያጠፋ እረጋገጠለት (ዘፍጥ. 8፡21፤ 9፡1)። ወራት በተፈጥሮ ሕግ መሠረት ጊዜያቸውን ጠብቀው እንደሚፈራረቁ ሁሉ (ዘፍጥ. 8፡22)፥ ሰውም እንዲባዛ እግዚአብሔር የታደሰ ሕግ ሰጠ (ዘፍጥ. 9፡1)። እንዲሁም ሰው በእንስሳት ላይ ያለውን ሥልጣን እንዲቀጥል (ዘፍጥ. 9፡2) አደረገና ሥጋ መብላትን ፈቀደለት፤ ደም ከመብላት ግን ተከልክሏል (ዘፍጥ. 9፡4)። ከሁሉም ይበልጥ የሚጠቅመው፥ በዚህ ዘመን ነፍሰ ገዳዮች የሚቀጡበት የሰው መንግሥት ሕልውና አግኝቶ የመመሥረቱ ጉዳይ ነው (ዘፍጥ. 9፡5-6)።
ሰሌሎች እንደታየው ሁሉ ለዚህ ዘመንም የሰው ውድቀት በግልጥ ተከስቷል። የኖኅ መስከርና (ዘፍጥ. 9፡21) የልጁ የካም አባቱን (ኖኅን አለማከበር ማስረጃዎች ናቸው (ዘፍጥ. 9፡22)። ዘመኑ ሥነ-ምግባር የጎደለበትና እግዚአብሔርን ማምለክ የቀነሰበት ሆነ (ዘፍጥ. 11፡1-4)። እንደ ሕሊና ሁሉ የሰው መንግሥት የሰውን ኃጢአት ተቆጣጥሮ ሊገታው አልቻለም፤ ውጤቱም የሳሲሉን ግንብ ሆነ (ዘፍጥ. 11፡4)። የእግዚአብሔር ፍርድ ቋንቋቸውን መደበላለቅና (ዘፍጥ. 11፡5-7) ሥልጣኔአቸውን ገትቶ እነርሱን በምድር ሁሉ ላይ መበታተን ነበር (ዘፍጥ. 11፡8-9)።
ይሁን እንጂ በዚህ ዘመን ፈሪሃ እግዚአብሔር ያደረባቸው ሰዎች ከጥፋት በመጠበቃቸውና አብርሃምም በመመረጡ ጻጋ መኖሩ ግልጥ ነበር (ዘፍጥ. 11፡10-12፡3)። የሴቲቱ ዘር ተርፎአል፥ የእግዚአብሔር ታላቅነትና የሁሉ የበላይነትም ተገልጧል። ሥፍረ-ዘመኑ የሚያበቃው በባቢሎን ግንብ ምክንያት በደረሰው ፍርድ ነው።
የሕሊናና የሰው መንግሥት ሁኔታ በሚቀጥሉት ሥፍረ-ዘመናትም ያላበቁ መሆናቸውን ማስተዋል ይገባል። የተስፋ ሥፍረ-ዘመን ውስጥ የሚገኙት አብርሃምና ዘሩ ብቻ ናቸው። በአጠቃላይ ይህ የሰው መንግሥት ሥፍረ-ዘመን፥ ከዚህ አዲስ የሕይወት ድንጋጌ በታች ያለውን የሰውን ውድቀት አሳየ። የእግዚአብሔርን ለይቶ የመፍረድ ሁኔታም ገለጠ። መለኮታዊ ጸጋን ማሳየቱንም ቀጠለ።
ሠ. የተስፋ ሥፍረ-ዘመን፡- ከአብርሃም ጋር የተደረገ ቃል ኪዳን
ይህ ቃል ኪዳን ከዘፍጥረት 11፡10 ጀምሮ እስከ ዘፀአት 19፡2 ይደርሳል። በዚህ ዘመን ለሰው የተሰጠው ኃላፊነት፥ እግዚአብሔር ለአብርሃም የገለጠውን ተስፋ ማመን ነው። †መለኮታዊው መገለጥ ይዘት ለአብርሃም የተስጠውኝ ተስፋ ይጨምራል (ዘፍጥ. 12፡1-2፤ 13፡16፤ 15፡5፤ 17፡6)። ለእስራኤል (የአብርሃም ዘር የተሰጠው ተስፋ ታላቅ መንግሥት እንደሚሆኑ፥ እግዚአብሔርም የቃል ኪዳኑን ተስፋ እንደሚፈጸምባቸው (ዘፍጥ. 12፡2-3፤ 13፡16፤ 15:5፥ 18-21፤ 17፡7-8፤ 28፡13-14፤ ኢያሱ 1፡2-4)፥ እንዲሁም ዓለሙን በሙሉ በአብርሃም በኩል እንደሚባርክ ነበር (ዘፍጥ. 12፡3)። መመሪያውም በግልጥ የተመሰከተ ሲሆን፥ አብርሃምን የሚባርኩትን እንደሚባርክና፥ የአብርሃምን ዘር የሚረግሙትን ደግሞ እንደሚረግም አረጋገጠ።
ከአብርሃም ጋር የነበረው ቃል ኪዳን መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ካሉት ጠቃሚ ቃል ኪዳኖች አንዱ ሲሆን፥ እርሱም፡- እስራኤል ዘላለማዊ መንግሥት የምትመሠርትበት፥ ምድሩንም ለዘላለም የግሷ የምታደርግሰት፥ በመንፈሳዊ ነገሮች የምትባረክበት፥ በመለኮታዊ ጥበቃ ሥር ለዘላለም የምትሆንበት እና ለዚህም ምቹ ሆና ለመገኘት ልዩ የሆነ የመገረዝ ሥርዓት እንደሚያስፈልጋት አጠቃሎ ይገልጣል (ዘፍጥ. 17፡13-14)። ቃል ኪዳኑም በእግዚአብሔር እንጂ በሰው ታማኝነት ላይ የተመሠረተ ስላልሆነ የጸጋ መመሪያ ነበር። የቃል ኪዳኑ ተስፋዎች አብርሃም በሕይወት እያለ በከፊል የተፈጸሙ ቢሆንም፥ እግዚእብሔር ለአብርሃም የገባላት ተስፋና በእርሱም አማካይነት የሚገኙት በረከቶች እስከ ዓለምና የሰው ልጅ ታሪክ ማብቂያ ድረስ መፈጸማቸውን ይቀጥላሉ። እርግጥ ከበረከቶቹ አንዳንዶቹ የዕውን መታዘዝ የሚሹ መሆናቸው በየትውልዱ ተገልጧል፤ የቃል ኪዳኑ ተስፋ ግን ለዘላለም መሆኑ ነው የታወጀው (ዘፍጥ. 17፡7፤ 13፡19፤ 1ኛ ዜና 16፡16-17፤ መዝ. 105፡10)። የሥፍሩ-ዘመን ኃላፊነትን በሚመለከት ከአብርሃም ጋር የነበረው ቃል ኪዳን በቀጥታ አስቀድሞ የሚያመለክተው፥ አብርሃምንና የአብርሃም ዘሮችን ኃላፊነት ነው። ዓለም አጠቃላይ ሰሰው መንግሥትና በሕሊና የሚመራ መሆኑ ቀዳሚ ኃላፊነቱ ስለሆነ በዚሁ ቀጠለ።
ከአብርሃም ጋር በነበረው ቃል ኪዳን ውስጥ ተደጋጋሚ የሆነ ውድቀት የሚታይ ሲሆን፥ ይህም ወደ ተስፋ ምድሩ ከመሄድ መዘግየት (ዘፍጥ. 11፡31)፥ እስማኤልን በመውለድና (ዘፍጥ. 16፡1-16)፥ ወደ ግብፅ ሰመውረድ (ዘፍጥ. 12 ፡10-13፡1) ተገልጧል። ነገር ግን አብርሃም እየቆየ ሲሄድ በእምነትና በጸጋ በማደጉ የተነሣ፥ ልጁን ይስሐቅን እስከ መስዋት ደረጃ ድረስ ስእግዚአብሔር ያለውን ታዛዥነት እስመስክሯል (ዘፍጥ. 22)።
ከአብርሃም በኋላ ይስሐቅ ከግብፅ ጋር በጣም ተቀራርቦ በመኖሩ ወደቀ (ዘፍጥ. 26፡1-16)፤ ያዕቆብም ደግሞ ሲወለድ ለእናቱ እግዚአብሔር የገባላትን የቃል ኪዳን ተስፋ ባለማመኑ ወደቀ (ዘፍጥ. 25፡23፤ 28፡13-15፥ 20)፤ እንዲሁም ያዕቆብ ውሽታም፥ አታላይና ነገረኛ ነበር (ዘፍጥ. 27፡1-29)። በመጨረሻም ከአገሩ ወጥቶ ረሃቡ እሰኪያልፍ ድረስ ወደ ግብፅ ወረደ (ዘፍጥ. 46፡1-4)።
እስራኤላውያን ደግሞ ገና በግብፅ እያሉ እግዚአብሔር በተአምራቱ ጠብቆ ወደ አገራቸው ሊመልሳቸው ተስፋ ከሰጣቸው በኋላ እምነት አጥተው በማጉረምረም ወደቁ (ዘጸ. 2፡23፣ 4፡1-10፤ 5፡21፤ 14 ፡10-12፤ 15፡24)፤ ከግብፅ ከወጡም በኋሳ ወደዚያው ለመመሰስ በመመኘት (ዘፀ. 14፡11-12)፥ እንዲሁም በተከታታይ በማጉረምረማቸው እግዚአብሔርን በደሉ (ዘፀ. 15፡24፤ 16፡2፤ ዘኁል. 14፡2፤ 16፡11፥ 41፤ ኢያሱ 9፡18)። የእግዚአብሔርን ሕግ ሲቀበሉና፥ በቃዴስ የእግዚአብሔር የተስፋ ቃል ሲሰጥ ባለማመናቸው ውድቀታቸው በግልፅ ታየ (ዘኁል. 14) በዘመኑ የአብርሃም የተስፋው ቃል የእነሱ ኃላፊነት መሆኑን ካለማመናቸው የተነሣ የተስፋይቱን ምድር ለጊዜው ሳይወርሱ ቀሩ፤ በግብፅ በባርነት ተቀመጡ። እንዲሁም ወደ ተስፋው ምድር እንደገና ከመግባታቸው በፊት በምድረበዳ ብዙ ተንከራተቱ። ይህ ሁሉ ውድቀታቸው ለሙሴ ሕግ መሰጠት መድረክን አመቻቸ።
በተስፋ ሥፍረ-ዘመን ብዙ መለኮታዊ ጸጋ ከእግዚአብሔር ይሰዛላቸው፥ እግዚአብሔርም ሁልጊዜ ሕዝቡን ይጠብቃቸው ነበር። ከግብፅ አዳናቸው፥ እንዲሁም የፋሲካን ሥርዓት ሰጣቸው። ይህ የተስፋ ሥፍረ-ዘመን ሕግ ለሙሴ ሕግ በተሰጠበት ወቅት (ዘፀ. 19) ያበቃ ቢመስልም፥ እስከ ታሪክ ፍጻሜ ድረስ የሚቀጥል ነው። ለአብርሃም የተገባው ተስፋ በአሁኑ ዘመን ላሰው የጸጋ ሥፍረ-ዘመንና ለወደፊቱ መንግሥት ሥፍረ-ዘመን መሠረት ነው። እንዲያውም ከተስፋው ከፊሉ የማያልቁና በዘላለማዊው መንግሥት ወቅት የሚፈጸሙ ናቸው።
የተስፋ ሥፍረ-ዘመን የመለኮታዊ ሉዓላዊነትን በግልጥ አጸና። ለእስራኤል ልዩ የሆነ የመለኮታዊ መገለጥ መንገድን አዘጋጀለት፥ መለኮታዊ ድነትና በረከትም እንዲቀጥል አደረገ። የእግዚአብሔር ጸጋ የተገለጠበት ከመሆኑም ሌላ ይህን ሁሉ ለዓለም የሚናገር ምስክር እንደሚመጣ የተረጋገጠበት ነው። እንደ ሌሎቹ ሥፍረዘመናት ሁሉ ይህም ሥፍረ-ዘመን ያላቀው፥ እግዚአብሔርን ለመምሰልና ፈቃዱን ለመከተል ካለመቻል የተነሣ በመጣ ውድቀት ነው። ይህም ውድቀት ነው፥ ሕግ ወደ ክርስቶስ የሚያደርስ ሞግዚቱ ሆኖ ለሰው እንዲሰጠው መሠረት የጣለ (ገላ. 3፡24)።
ረ. የሕግ ሥፍረ-ዘመን
ሕግ በሌላ በኩል በመስቀል ላይ የተፈጸመ መሆኑ ቢታወቅም፥ የሕግ ሥፍረ-ዘመን ከዘፀአት ምዕራፍ 19 ቁ.3 ጀምሮ እስከ የሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 2 ዕለተ-ጰንጠቆስጤ ድረስ ያለውን ዘመን በሙሉ ያጠቃልላል። የአሁኑ የጸጋ ዘመን፥ ከወንጌል ክፍሎች እንደ ዮሐንስ ወንጌል ባሉትና በሌሎችም ወንጌሉች በተወሰኑ ሥፍራዎች ተገልጧል።
የሙሴ ሕግ የተሰጠው በቀጥታ ለእስራኤል ብቻ ስለነበር፥ አሕዛብ በዚህ ሕግ መሠረት አልተፈረደባቸውም። ሕጉም በዝርዝር በተመለከቱት ሦስት የሥራ ስልቶችና ክፍሎች ተመድቧል። እነርሱም ትእዛዛት (የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚገልጡ፥ ዘጻ. 20፡1-26)፥ ፍርዶች (የእስራኤላውያን ማኅበራዊና ሕዝባዊ መመሪያዎች፥ ዘጸ. 21፡1 24፡11)፥ እንዲሁም ሥርዓቶች (የእስራኤላውያን ሃይማኖታዊ ሕይወት፥ ዘጸ. 24 ፡12 31 ፡18) ናቸው። የመሥዋዕትና የክህነት ሥርዓት በዚህ ውስጥ የተጠቃለለ ሲሆን፥ ጸጋዊና ሕጋዊም ነበር። የዚህ ሥፍረ-ዘመን መንግሥት እግዚአብሔር ራሱ ይጎዛው ዮነበረ ሲሆን ለአገዛዙ ቢሆንም ይጠቀምባቸው የነበሩት ነቢያት፥ ካህናትና በኋላም ነገሥታት ነበሩ። የሙሴ ቃል ኪዳንም እንደተለመደው ሁሉ ጊዜአዊ ነበር፤ ምክንያቱም ቃል ኪዳኑ በሥራ ላይ የዋለው፥ መሢሑ እስኪመጣ ድረስ ብቻ ነበርና (ገላ. 3፡24-25)። የሥፍረ-ዘመኑ ባሕርይ ደግሞ ሁኔታዊና ምክንያታዊ ነበር። ማለትም መታዘዝ በረከትን የማግኛ ቅድመ
ሁኔታ ነበር።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተጠቅሶ የሚገኘው የዚህ ዘመን ሕግ፥ በሰው ዘር ታሪክ ውስጥም የመጀመሪያው ነው፡፡ከዚህ የተነሣ መጽሐፍ ቅዱስ በዚህ ሕግ አማካይነት ዝርዝርና አጠቃላይ የሆነ ሃይማኖታዊ ሥርዓትን ከመግለጡም በላይ፥ ለይቅርታና ለመንጻት ሁኔታ ያመቻቸ፥ ለአምልኮ፥ ለጸሎትና ለምስጋና ደንብ የሰጠና ለወደፊቱ ተስፋን ያስጨበጠ ነበር።
በሕጉም ወቅት ተከታታይ ውድቀት ነበር። ይህ በተለይ የተረጋገጠው፥ በመሳፍንት አመራር ወቅት ሲሆን፥ ከሰሎሞን ሞትና እንዲሁም የእስራኤል መንግሥት ሁለት ላይ ከተከፈለ በኋላም ውድቀቱ ቀጠለ። ሕጉ ሙሉ በሙሉ ተረስቶ፥ የጣዖት አምልኮ ያየለባቸው ጊዚያትም ነበሩ። አዲስ ኪዳን ይህን የውድቀት ታሪክ መዝግቦታል። ውድቀቱ ከፍተኛ ደረጃ የደረሰው፥ በተስፋ ቃል ኪዳኑ መሠረት ሰውን ሊቤዥና ሊታደግ የመጣውንና ሕግን በመጠበቅ ፍጹም የሆነውን ኢየሱስን በመጥላትና በመስቀል ነው።
በዚህ የሕግ ሥፍረ-ዘመን ወቅት በእስራኤላውያን ላይ ብዙ የእርግማንና የቅጣት ፍርድ እንደተበየነባቸው ዘዳግም 28፡1-30፡20 ውስጥ ተመልክቷል። ከፍርዶቹ ሁሉ ከፍተኛ የሆኑት ለእሥሪያና ለባቢሎን ምርኮ እልፎ መሰጠት ሲሆኑ፥ የእስራኤል ልጆች ጊዜያቸውን ጠብቀው ከምርኮው ተመልሰዋል። በሥፍረ-ዘመኑ መጨረሻ አካባቢም ሌላ ፍርድ መጥቶባቸው ነበር። ይኽውም በ70 ዓ,ም. የተፈጻመው የኢየሩሳሌም መፍረስና የእስራኤላውያን በዓለም ሁሉ መበታተን ነበር። ሌላው “የያዕቆብ መከራ” በመባል የሚታወቀው ታላቁ መከራ ገና ወደፊት ሊመጣ ያለው ነው (ኤር. 30፡1-11፤ ዳን. 12፡1፤ ማቴ. 24፡22)።
በሕግ ደግሞ ኃጢአተኛዋን እሰራኤል ለመታደግ ሲባል መለኮታዊ ጸጋ በመሥዋዕቱ ሥርዓት አማካይነት ይፈጸም ነበር። ይህ ታላቁ የእግዚአብሔር ትዕግሥት ኃጢአተኛዋን እስራኤል ለመመለስ ነቢያትን፥ መሳፍንትንና ነገሥታትን ሰማዘጋጀቱና ዓላማውን እንዲሁም ፍቃዱን በእርስዋ በኩል በመፈጸሙ ይህ ተገልጧል። እውነተኛው የእስራኤል ንስሐ ብዙ ጊዜ በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነትን ያገኘ ሲሆን፥ ብሉይ ኪዳን የተጻፈውም በዚሁ ጊዜ ነበር። ታላቁን በረከት ማለት የክርስቶስን መሢሕ ሆኖ መምጣት የእስራኤል ሕዝብ በአጠቃላይ አልተቀበለውም።
በአንድ በኩል የሕግ ሥፍረ-ዘመን በመስቀሉ ላይ አብቅቷል (ሮሜ 10፡4፤ 2ኛ ቆሮ. 3፡11-14፤ ገላ. 3፡19፥ 25)። በሌላ በኩል ግን አዲሱ የጸጋ ዘመን የጀመረበት የጰንጠቆስጤ ዕለት እስኪደርስ ድረስ የሕግ ሥፍረዘመን አልተጠናቀቀም። ሕጉ ግልጥ የሕይወት መመሪያነቱ ቢያበቃም የእግዚአብሔር የቅድስና መግለጫ እንደሆነ የሚቀጥል ስለሆነ፥ ክርስቲያኖች በደንብ ቢረዱት፥ የእግዚአብሔርን ጳድቅ ባሕርይ ሕጉ ውስጥ የተካተቱት የሥነ-ሥርዓት መመሪያዎች እንዳሉ ይቀጥላሉ። እግዚአብሔር የማይለወጥ በመሆኑ እርሱም አይልም። የዚህ ሥፍረ-ዘመን ሕግ የተሰጠው በቀጥታ ለእስራኤል እንጂ ለቤተ ክርስቲያን ስላልሆነና፥ ሥፍረ-ዘመኑም የተለወጠ በመሆኑ፥ የአሁኑ ዘመን አማኞች ሕጉን በዝርዝር እንዲያከብሩት አይገደዱም። ሕጉን በተለያዩ መንገዶች በሥራ ላይ ለማዋል ቢቻልም፥ ጥብቅ የሆነው አተረጓጎም የሚያስገነዝበው የሙሴ ሕግ ለእስራኤል ብቻ መሆኑን ነው።
ሕግ የተሰጠው ኃጢአትን ወደ ፍርድ ለማምጣትና ለሕይወት የጽድቅ መመሪያ ለመስጠት ነበር። የሥነ-ምግባር፥ የመንግሥትና የሃይማኖት ሕግ እንደማያድንና እንደማይቀድስ በሕግ ሥር የነበሩት የእስራኤላውያን አኗኗር አሳይቷል። ሕግ የተሰጠው ለሰው ድነትን ለማስገኘት አልነበረም። ሕግ ሰራሱ ደካማ ስለነበር፥ ሊያጸድቅ አልቻለም (ሮሜ 3፡20፤ ገላ. 2፡16)፤ ሰውን ሊቀድስ ወይም ፍጹም ሊያደርግም አልቻለም (ዕብ. 7: 18-19)። የሕግ ኃይልና ቆይታ ለተወሰነ ጊዜ ብቻ ነበር (ገላ. 3፡19)፥ ሕግ ሕያው ሊያደርግ አልቻለም (ገላ. 3፡21-22)፥ ተግባሩ ኃጢአትን በይፋ ማውጣት ብቻ ነበር (ሮሜ 7፡5-9፤ 8፡3፤ 1ኛ ቆሮ. 15፡56)። ሰው ሁሉ ጥፋተኛ ወይም ኃጢአተኛ መሆኑን ለማሳየትና የክርስቶስን አስፈላጊነት ጉልህ አድርጎ ለማቅረብ ቻለ (ሮሜ 3፡19፤ 7፡7-25፤ ገላ. 3፡21-27)።
ሰ. የጸጋ ሥፍረ-ዘመን
የጸጋ ሥፍረ-ዘመን በትክክል ከሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 2 ጀምሮ በአዲስ ኪዳን በሙሉ ይቀጥልና በቤተ ክርስቲያን መነጠቅ ይጠናቀቃል። ስለዚህ የጸጋ ሥፍረ-ዘመን ከዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 13 እስከ ምዕራፍ 17 ባለው ክፍል አንዳንድ ትምህርቶች ተስጥተው ነበር። ይህ ዘመን የሚያጠቃልላቸው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች፥ ከሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 1 እስከ ዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ 3 ያሉት ናቸው።
ይህ የጸጋ ሥፍረ-ዘመን የተሰጠው ሰቀጥታ ለቤተ ክርስቲያን ብቻ በመሆኑ፥ መላው ዓለም በሕሊናና በሰው መንግሥት ውስጥ እንዳለ ይቀጥላል። ሰውስጡም ድነት የሚገኘው በእምነት ብቻ መሆኑ የተገለጠ ሲሆን፥ ይህ እውነት ሁልጊዜ ያለና አሁን ደግሞ ይበልጥ ግልጥ የሆነ ነው (ሮሜ 1፡16፤ 3፡22-28፣ 4፡16፤ 5፡15-19)። በዚህ ሥፍረ-ዘመን ያለው የጸጋ መመሪያ ሥፍረ-ዘመኑን ከቀደምት ሥፍረ-ዘመናት ሁሉ ልዩና ታላቅ ያደርገዋል (ዮሐ. 13፡34-35፤ ሮሜ 12፡1-2፤ ፊልጵ. 2፡5፤ ቈላ. 1፡10-14፤ 3፡1፤ 1ኛ ተሰ. 5፡23)።
በጸጋ ሥፍረ-ዘመንም በውድቀት ታይቷል። ምክኝያቱም ጸጋ ቢኖርም ዓለም ሁሉ ክርስቶስን ስላልተቀበለውና ፍጹም የሆነች ቤተ ክርስቲያን ስለማትታይ ነው። ቤተ ክርስቲያን ውስጥ መንፈሳዊነት ከመጉደሉ የተነሣ፥ ሰዎች በሐሰት ተመርዘው ስሕተትን የሚያስፋፉበት ዘመን እንደሚመጣ መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል (1ኛ ጢሞ. 4፡1-3፤ 2ኛ ጢሞ. 3፡1-13፤ 2ኛ ጴጥ, 2-3፤ የይሁዳ መልእክት በሙሉ)። እግዚአብሔር ሕዝቡን ከአይሁድና ከአሕዛብ መካከል እየጠራ ዓላማውን በመፈጸም ላይ ነው። ይሁኝ እንጂ፥ አሁን ባለችው ቤተ ክርስቲያን የሚገኙ፥ ግን ያልዳኑ ሰዎች፥ ቤተ ክርስቲያን ስትነጠቅ እዚሁ ይቀሩና ክርስቶስ መንግሥቱን ሊመሠርት በሚመጣበትና በቤተ ክርስቲያን መነጠቅ መካከል ባለው ጊዜ ፍርዳቸውን ይቀበላሉ (ማቴ. 24፡1-26፤ ራእይ 6፡19)። እውነተኛይቱ ቤተ ክርስቲያን ግን በመንግሥተ ሰማያት በክርስቶስ የፍርድ ወንበር ፊት ፍርዷ ይታያል (2ኛ ቆሮ. 5፡10-11)።
በዚህ ዘመን መለኮታዊ ጸጋ ተገልጧል፡- በተለይም በክርስቶስ መምጣት አማካይነት (ዮሐ. 1፡17)፥ በአማኝ ድነትና በእግዚአብሔር ፊት በመቆማችን (ሮሜ 3፡24፤ 5፡1-2፥ 15-21፤ ገላ. 1፡1-2፣ 21፤ ኤፌ. 2፡4-10)፥ እና ጸጋ ራሱ የሕይወት መመሪያ ሕግ በመሆኑ (ገላ. 3፡1-5፡26)።
የጸጋ ሥፍረ-ዘመን የሚያበቃው፥ በእውነተኛይቱ ቤተ ክርስቲያን መነጠቅ ሲሆን፥ ከዚያ የሚቀጥለው አሰተኛይቱ ቤተ ክርስቲያን ላይ የሚሰጠው ፍርድ ይሆናል (ራእይ 17፡16)። ይህ የአሁኑ የጸጋ ዘመን ልዩ ሥፍረ-ዘመን የሚሆንበት ዋና ምክንያት ቤተ ክርስቲያን ልለምታጠቃልላቸው ከአይሁድና ከአሕዛብ የሆኑትን አማኞች ሁሉ ነው። በተቃራኒው ግን የእስራኤል ሕግ ለእስራኤል ብቻ፥ ሰብዓዊ መንግሥት ለመላው ዓለም፥ እንዲሁም ሕሊና ለሁሉም የሰው ልጅ ሆነው እናገኛቸዋለን። በጸጋ ሥፍረ-ዘምን የሙሴ ሕግ ሙሉ በሙሉ ተሰርዟል። ይሁን እንጂ የእግዚአብሔርን ቅድስና እየመሰከረ፥ የሰውንም ደካማነት እያሳየ፥ በጸጋ ሰመመራት ቢጠቀሙበት ትርፍ ላለበት መንፈሳዊ ትምህርትነት ያለውን ዋጋ እንደያዘ ይቀጥላል። ሁሉም ሥፍረ-ዘመናት በአጠቃላይ የእግዚአብሔር ጸጋ አላቸው። የጸጋ ሥፍረ-ዘመን ግን በሚገኝበት ጸጋ ሙሉነትና በሕይወት መመሪያነቱ ከሁሉም የላቀ መገለጥ ነው።
ሸ. የእግዚአብሔር መንግሥት ሥፍረ-ዘመን
የዚህ መንግሥት ሥፍረ-ዘመን የሚጀምረው በክርስቶስ ዳግም ምጽአት ሲሆን (ማቴ. 24፤ ራእይ 19)፥ በሽግግር ወቅትነት የሚያገለግለውን የመከራ ጊዜ ያስቀድማል። ማስረጃውም ስለሚመጣው መንግሥት በሚናገሩት የብሉይና የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት በሙሉ ይገኛል፡- (በተለይም መዝ. 72፤ ኢሳ. 2፡1-5፤ 9፡6-7፥ 11፤ ኤር. 33፡14-17፤ ዳን. 2፡44-45፤ 7፡9-14፥ 18፥ 27፤ ሆሴዕ 3፡4-5፤ ዘካ. 14፡9፤ ሉቃስ 1፡31-33፤ ራእይ 19-20)። ሰመንግሥቱ ውስጥ የሰው ኃላፊነት፥ በብረት በትር ለሚገዛው ንጉሥ መታዘዝ ብቻ ይሆናል (ኢሳ. 11፡3-5፤ ራእይ 19፡15)። መንግሥቱም እግዚአብሔር ራሱ የሚነግሥሰት ሲሆን፥ አዲስ የመሥዋዕት ሥርዓትና ክህነት ይኖረዋል (ኢሳ. 66፡21-23፤ ሕዝ. 40-48)። የዚህ ዘመን ልዩ ባሕርይ ሰይጣን መታሰሩና አጋንንትም ሥልጣን ተወስዶባቸው ምንም ሊያደርጉ አስመቻላቸው ነው (ራእይ 20፡1-3፥ 7)። ከምንግሥቱ ውስጥ ውድቀትም ይኖራል (ኢሳ. 65፡20፤ ዘካ. 14፡16-19)፤ ሰማብቂያውም አለመታዘዝና ዓመፅ ይኖራል(ራእይ 20፡7-9)።
ቀጥሎ የሚመጣው መለኮታዊ ፍርድ፥ የዓመፀኞች በእሳት መጥፋትና (ራእይ 20፡9)፥ የአሮጌው ሰማይና ምድር በተመሳሳይ ሁኔታ መጥፋትን ያጠቃልላል (2ኛ ጴጥ. 3፡7፥ 10-12)።
በዚህ የሺህ ዓመት መንግሥት ውስጥም መለኮታዊ ጻጋው አዲሱን ቃል ኪዳን በመፈጸም (ኤር. 31፡31-34)፥ በድነት (ኢሳ. 12)፥ በቁሳዊ ብልጽግና (ኢሳ. 35)፥ ራእይ አትረፍርፎ በመስጠት (ኤር. 31፡33-34)ይቅርታ በማብዛት (ኤር. 31፡34)፥ እንዲሁም በእስራኤል እንደገና መስብስብ ይገለጣል (ኢሳ. 11፡11-12፤ ኤር. 30፡1-11፤ ሕዝ. 39፡25-29)። ይህ የሺህ ዓመት መንግሥት ሰአሮጌው ሰማይና ምድር መጥፋት የሚጠናቀቅ ሲሆን፥ ቀጥሎ የዘላለም መንግሥት ይከተላል(ራእይ 21-22)።
የሺህ ዓመቱ መንግሥት ሥፍረ-ዘመን ከቀደሙት ሥፍረ-ዘመናት በሙሉ የሚለየው፥ የሰው ሥነ-ምግባር የሚፈተንበት የመጨረሻ ቅርጽ በመሆኑ ነው። ይህ ሥፍረ-ዘመን ከሁሉ የሚሻልባቸው መንገዶች ፍጹም የሆነ መንግሥት፥ የክርስቶስ በክብርና በግርማ መገኘት፥ አጠቃላይ በሆነ የእግዚአብሔር እውቀት መሞላት፥ ድነትን መረዳትና የሰይጣን ኃይል መወሰድ ናቸው። የዚህ መንግሥት ዘመን በብዙ ረገድ የመጨረሻው ከመሆኑም በላይ፥ እግዚአብሔር ከሰው ጋር ያለው ጉዳይ የሚጠናቀቅበት ነው።
በየዘመናቱ እግዚአብሔር ከሰው ጋር ያለውን ጉዳይ በተለያዩ ስልቶችና መንገዶች አሳይቷል። በዘመናት ሁሉ ሰው ይወድቃል፥ የእግዚአብሔር ጸጋ ብቻ ነበር ብቁ። በሥፍረ-ዘመናቱ በተፈጥሯዊው ዓለምና ስሰው ታሪክ አማካይነት የእግዚአብሔር ክብር ተገልጧል። እግዚአብሔር ሰው ወደ ድነት የሚደርስበትን ወይም በራሱ ችሎታና ብቃት ለቅድስና የሚበቃበትን ሌላ ዕድል ሊሰጥ ይችል ነበር ወይ? ብሎ ማንም ጥያቄ ለማንሣት እይችልም። ስለዚህ የእግዚአብሔርን የተለያዩ ሥፍረ-ዘመናት መረዳቱ 1ኛ. በታሪክ ውስጥ የእግዚአብሔርን ዓላማ፥ 2ኛ. እግዚአብሔር ከሰው ጋር ያለውን ግንኙነት፥ 3ኛ. ሲል ራሱ የሰጠውን መለኮታዊ መገለጥ እና 4ኛ. በዘመናቱ ሁሉ ሰው የነበረበትን ድካምና የጌታን ታላቅ ፍቅር ላመገንዘብ ይረዳል።
ምንጭ፡- “ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ ጭብጦች” መጽሐፍ በዶክተር ሉዊስ ስፔሪ ቼፈር የተጻፈ እና በተክሉ መንገሻ የተተረጎመ ነው፡፡ እግዚአብሔር ስለ እነዚህ ቅዱሳን ድንቅ ስራ የተመሰገነ ይሁን፡፡ ማሳሰቢያ፡- ይህን ጽሁፍ መቀየርም ሆነ ለሽያጭ ማዋል በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡