ትንሣኤዎቹ

ሰዎች ሁሉ በአንድ ጊዚ ይነግሉ ከሚሰው ድጋፍ-አልባ ንድፈ-አሳብ ሳቢያ በትንቢት አተረጓጎም ዙሪያ እያሌ ውዝግብ ሲፈጠር ቆይቷል። ይህ ንድፈ-አሳብ መጽሐፍ ቅዱዕ ሰለተለያዩ ትንሣኤዎች ያስቀመጣቸውን ዝርዝር ጉዳዮች ጎለል ያደርጋል። መጽሐፍ ቅዱስ የሚያቀርብልን ወደ ሰባት የሚደርሱ ትንሣኤዎችን ነው። ከእነዚህም አንዳንዶቹ ከዚህ በፊት የተከናወኑ ሲሆኑ፥ ሌሎቹ ደግሞ በረዥም ክፍለ-ጊዚያት የተራራቁ ናቸው። እነዚህም ከክርስቶስ የሺህ ዓመታት አገዛዝ ቀድመው ወይም ተከትለው የሚፈጸሙ ትንሣኤዎች ናቸው። ሁሉም በየራሳቸው ጊዜና ቦታ እንደሚሠ እና የሰው ዘር ሕልውና ግን ለዘላለም እንደሚቀጥል መጽሐፍ ቅዱስ ያስተምራል። የትንሣኤው ትምህርት ጥናት እንደሚያመለክተው፥ ይህን የክርስትና እምነትና ተስፋ ማዕከላዊ እውነት በተመለከተ ትንቢታዊው ፕሮግራም ውስጥ ጠቃሚ መግለጫ አለ። 

ሀ. የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ 

በትንሣኤዎች ቅደም ተከተል መሠረት፥ ቀዳሚውን ስፍራ የያዘው የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ነው። ያም በብሉይ ኪዳን ትንቢት (እንደ መዝሙር 16፡9-10)፥ ሰአራቱ ወንጌላትና በሥነ-መለኮታዊ ረገድ ደግሞ ከሐዋርያት ሥራ ጀምሮ አዲስ ኪዳን ውስጥ የተብራራ ጉዳይ ነው። ሐዋርያው ጳውሎስ 1ኛ ቆሮንቶስ ምዕራፍ 15 ውስጥ በስፋት እንደሚሟገተው፥ የክርስቶስ ትንሣኤ የክርስቲያን እምነትና ተስፋ ሁሉ የሚያርፍበት ማዕከላዊ ትምህርት ነው። ከአንድ የሚበልጡ ትንሣኤዎች እንዳሉ የሚያረጋግጡትን ሐቆች በምንመለከትበት ጊዜ፥ የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ቀደም ሲል የተፈጻመ ልዩ ክሥተት መሆኑን ሁሉም ሊቀበሉት ይገባል። 

ለ. የኢየሩሳሌሙ የቅዱሳን ትንሣኤ 

ማቴዎስ 27፡52-53 ውስጥ ያለው ቃል እንደሚያስረዳን፥ ክርስቶስ ከሞት በተነሣ ጊዜ የቅዱሳንም ምሳሌነት ትንሣኤ ተካሂዷል። በኢየሱስ ክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ወቅት የሚከተለው ክሥተት እንደተፈጸሙ ምንባቡ እንዲህ ይጎልጣል፡- “መቃብሮችም ተከፈቱ፥ ተኝተው ከነበሩትም ከቅዱሳን ብዙ ሥጋዎች ተነሡ። ከትንሣኤውም በኋላ ከመቃብሮች ወጥተው ወደ ቅድስት ከተማ ገቡና ለብዙዎች ታዩ።” 

ይህን እንግዳ ክሥተት በተመለከተ የቀረበ ማብራሪያ የትም አይገኝ። መቃብሮች በክርስቶስ ሞት ጊዜ ቢከፈቱም፥ ክርስቶስ እስከተነሣበት ጊዜ ድረስ ቅዱሳኑ ከሞት ያልተነሡ ይመስላል። ለዚህም ምክንያቱ፥ በኩራት የሆነው ክርስቶስ ለዘላለም በማይጠፋ የትንሣኤ አካል ከሞት በመነሣት የቀዳሚነቱን ስፍራ እንደያዘ መጽሐፍ ቅዱስ በግልጥ መናገሩ ነው። በአንጻሩም እንደ አልዓዛር ከሞት የተነሡ ሰዎች እንደገና ሞተው ተቀብረዋል። ክርስቶስ ግን ዳግም ወደ መቃብር ላይመለስ ነው የተነሣ። 

በክርስቶስ ትንሣኤ ተነሡትና በአንጻራዊነት አነስተኛ ቁጥር ለነበራቸው ቅዱሳን ትንሣኤ ተስማሚ ፍች ሊሆን የሚችል እሳብ ባለፈው በተፈጸመው የሌዋውያን መሥዋዕት ክንውን ውስጥ የሚገኝ ይመስላል። ሦስተኛው የመከር በኩራት በዓል (ዘሌ. 23፡9-14) ከሚያካትታቸው ነገሮች አንዱ፥ በመከሩ መጀመሪያ እስራኤላውያን የበኩራቱን ነዶ በእግዚአብሔር ፊት የሚወዘውዙበትና፥ ቀጣዩን መከር በመጠበቅ ተስማሚ መሥዋዕት የሚያቀርቡበት ሥርዓት ይገኝበታል። በክርስቶስ ትንሣኤ ወቅት የሆነው የነዚያ ቅዱሳን ትንሣኤ በኩርነት በመወከል፥ ክርስቶስ በትንሣኤው ብቻውን እንዳልሆነና ለሚመጣው ታላቅ መከር የፈር ቀዳጅነቱን ተግባር እንደሚወጣ ያሳያል። እነዚህ ቅዱሳንም የትንሣኤ ምሳሌዎች ነበሩ። 

ምንም እንኳን አንዳንድ ሰዎች ማቴዎስ ወንጌል ውስጥ የሚገኙትን ማጣቀሻዎች እንደ አልዓዛር ትንሣኤ ወደ ሕይወት መመለስ ብቻ እድርገው ቢተረጉሟቸው፥ በክርስቶስ ትንሣኤ ወቅት መፈጸሙ ዘላቂ ትንሣኤን የሚያመለክት ነው። ስለሆነም፥ እነዚህ ቅዱሳን ተልእኳቸውን ከፈጸሙ በኋላ ወደ ሰማይ ያረጉ መሆናቸው አያጠራጥርም። ያም ሆነ ይህ+ የእነዚህ ቅዱሳን ትንሣኤ፥ ትንሣኤዎች ሁሉ በአንድ ታላቅ የወደፊት ትንሣኤ እንደማይጠቃለሱ የሚያረጋግጥ ታሪካዊ ክሥተት ነው። 

ሐ. የቤተ ክርስቲያን ትንሣኤ 

ቀደም ሲል ክርስቶስ ለቅዱሳኑ ሰሰሚመጣበት ሁኔታና ስለመነጠቅ በተነሣው ትምህርት ውስጥ እንደተገለጠው፥ ክርስቶስ የራሱ ለሆኑት ሲመጣ በርሱ የሞቱት ይነሣሉ። ከዚያም በሕይወት ከነበሩትና ከሚለወጡት ክርስቲያኖች ጋር፥ ጌታን በአየር ይቀበሉና ወደ ሰማይ ያርጋሉ። 1ኛ ተሰሎንቄ 4:13-18 እና 1ኛ ቆሮንቶስ 15፡51-58 እንደሚያዕተምሩት፥ ከሞት የተነሡትና በሕይወት የነበሩት ክርስቲያኖች የክርስቶስን የሚመስል ትንሣኤ አካል ይቀበሳሉ (1ኛ ዮሐ. 3፡2)። የቤተ ክርስቲያን ትንሣኤ የመጀመሪያው ብዝሃ ትንሣኤ ሲሆን፥ ለተከታታይ ትንሣኤዎች ግንባር ቀደሙ ነው። 

መ. የብሉይ ኪዳን ቅዱሳን ትንሣኤ 

ኢዮብ 19፡25-26 ውስጥ እንደተገለጠው፥ ምንም እንኳኝ ብሉይ ኪዳን በተደጋጋሚ ስለ ትንሣኤ ትምህርት ቢያመለክትም፥ ትንቢት ውስጥ ከፍተኛ ስፍራ አልተሰጠውም። ይሁንና፥ ተጠቅሰው የምናገኛቸው አሳቦች የሚያመለክቱት የብሉይ ኪዳን ቅዱሳን ትንሣኤ የሚፈጸመው፥ በንጥቀት ወቅት ሳይሆን፥ ወደ ምድር በሚመለስበት ዳግም ምጽአቱ ጊዜ መሆኑን ነው። 

ዳንኤል፥ ምዕራፍ 12 ቁጥር 1 ውስጥ ታላቁን መከራ ከገለጠ በኋላ፥ ቁጥር 2 ውስጥ ደግሞ ትንሣኤን ያብራራል። ከዚህ ክፍል እንደምንመለከተው፥ ትንሣኤ ከታላቁ መከራ የሚቀጥልና የመጨረሻ ክፍል ሆኖ ቀርቧል። ስለሆነም፥ የብሉይ ኪዳን ቅዱሳን የሚነሡት፥ በመነጠቅ ጊዜ ሳይሆን፥ በመንግሥት ምሥረታ ወቅት ነው። ከመጽሐፈ ኢዮብ ተመሳሳይ አሳብ ለመረዳት እንደሚቻለው፥ ትንሣኤ ክርስቶስ እግሮቹን በምድር ላይ ከሚያሳርፍበት መን ጋር ተያይዟል። 

በተመሳሳይ ሁኔታ፥ ሙታን ከመቃብር የሚነቁበት የትንሣኤ ትምህርት ክርስቶስ በዓለም ላይ ሊፈርድ ከሚመጣበት ዘመን ጋር ተዛምዷል (ኢሳ. 26፡19-21)። በተጨማሪም፥ “በክርስቶስ የሞቱት” የሚለው ሐረግ ሰመነጠቅ ጊዚ የሚነሡትን ለመግለጥ እንዳገለገለ መረዳቱ ተገቢ ነው (1ኛ ተሰ. 4፡16)። “በክርስቶስ” የሚለው እገላለጥ ከመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት የተነሣ አማኙ አሁን ያለውን ስፍራ ያመለክታል። 

ይህ ገለጣ ለመጀመሪያ ጊዜ የታየው፥ ሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 2 ውስጥ ሲሆን፥ ስለ ብሉይ ኪዳን ቅዱሳን አልጎለጠም። ምንም እንኳ የመጽሐፍ ቅዱስ ተርጓሚዎች አሳብ ሲለያዩና አንዳንዶቹ መነጠቅ የብሉይ ኪዳን ቅዱሳንን ይጨምራል ቢሉ፥ አብዛኛው መረጃ የሚያመለክተው ግን፥ የብሉይ ኪዳን ቅዱሳን የሚነሡት በክርስቶስ ዳግም ምጽአት ወቅት መሆኑን ነው። ያም ሆነ ይህ፥ የብሉይም ሆነ የእዲስ ኪዳን ቅዱሳን ከሺህ ዓመቱ መንግሥት በፊት ይነሣሉ። 

ሠ. የታላቁ መከራ ወቅት ቅዱሳኝ ትንሣኤ 

በታላቁ መከራ ወቅት በሰማዕትነት ስለሞቱ ሰዎች ክርስቶስ መንግሥቱን በምድር ላይ ለመመሥረት ከሚመጣበት ሁኔታ ጋር በተያያዘ መንገድ ልዩ ስሳ ተሰጥቷል። ራእይ 20፡4 ውስጥ ዮሐንስ ስለእነዚህ ወገኖች የሚከተላውን ገልጧል፡- “ስለ ኢየሱስም ምስክርና ስለ እግዚአብሔር ቃል ራሶቻቸው የተቆረጡባቸውን ሰዎች ለአውሬውና ለምስሉም ያልሰገዱትን፥ ምልክቱንም በግንባሮቻቸው በእጆቻቸውም ላይ ያልተቀበሉትን አየሁ፤ ከክርስቶስም ጋር ሺህ ዓመቱኝ ኖሩና ነገሡ”። 

በታላቁ መከራ ዘመን በሰማዕትነት የሚሞቱ ቅዱሳን ክርስቶስ መንግሥቱን ለመመሥረት ሰሚመለስበት ጊዜ የሚነሡ ስለመሆናቸው ከላይ የቀረበው ዓረፍተ ነገር ግልጥ መረጃ ነው። ራእይ 20፡5 ውስጥ የተጠቀሰው ቃል፥ “የቀሩቱ ሙታን ግን ሺህ ዓመት እስኪፈጸም ድረስ በሕይወት አልኖሩም። ይህ የፊተኛው ትንሣኤ ነው” ሲል ያውጃል። ከእርሱ በፊት የክርስቶስ፥ የቤተ ክርስቲያንና የብሉይ ኪዳን ቅዱሳን ትንሣኤዎች ተካሂደው ሳለ፥ ይህ እንዴት የፊተኛው ትንሣኤ ይሆናል? የሚል ተገቢ ጥያቄ ይነሣል። 

ለዚህ መልሱ “የፊተኛው ትንሣኤ” የሚለው ሐረግ ምንም እንኳ በጊዜ ርዝመት ቢለያዩ፥ የጻድቃንን ትንሣኤዎች ሁሉ ያመለክታል የሚል ነው። ሁሉም ከኃጢአተኞች የመጨረሻ ትንሣኤ በፊት የሚከናወኑና “ፊተኛ” ናቸው። ስለሆነም፥ «{የፊተኛው ትንሣኤ” የሚለው ሐረግ የክርስቶስን ትንሣኤ ጨምሮ፥ የሁሉንም የቅዱሳን ትንሣኤዎች የሚመለከት ነው። 

ረ. የሺህ ዓመቱ ቅዱሳን ትንሣኤ 

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በየትኛውም ስፍራ ስለ ሺህ ዓመቱ ቅዱሳን ትንሣኤ በግልጥ የተቀመጠ እሳብ ባለመኖሩ፥ አንዳንዶች ወደ ሺህ ዓመቱ መንግሥት የሚገቡ ቅዱሳን ከቶውንም እንደማይሞቱ ይናገራሉ። በሺህ ዓመቱ መንግሥት መጨረሻ ላይ ሕይወት የሚኖሩ ሰዎች ስለመነጠቃቸውም መጽሐፍ ቅዱስ የሚገልጠው ነገር የለም። እነዚህ ሁለቱም ትንቢታዊ ነገሮች ዛሬ በሕይወት ለሚኖሩ ቅዱሳን አንገብጋቢ ጉዳዮች አይደሉም። ከዚህ ጋር የሚዛመደው እውነት ክርስቶስ መንግሥቱን ለመመሥረት ከተመለሰ በኋላ ሊገለጥ ይችላል። 

ይሁን እንጂ፥ የመከራውን ዘመን የሚያልፉ ቅዱሳኝ ዕድሜያቸው የሚገፋ ከመሆኑም ሌላ፥ በሺህ ዓመቱ አገዛዝ ዘመን ሁሉ በሕይወት የመኖራቸው ነገር አጠራጣሪ ነው። አዳምና ቀደምት ክርስቲያኖች እንኳ ለሺ ዓመት በሕይወት አልኖሩም። ስለሆነም ምንም እንኳ ዕድሜያቸው ሊረዝም ቢችል፥ ሺሁን ዓመት በሙሉ እንደማይኖሩና መሞታቸው እንደማይቀር ይታመናል። 

ኢሳይያስ 65፡20 ውስጥ፥ ከዚያ ወዲህ ጥቂት ዘመን ብቻ የሚኖር ሕፃን፥ ወይም ዕድሜውን ያልፈጸመ ሽማግሌ አይገኝም፥ ጎልማሳው መቶ ዓመት ሆኖት ይሞታልና፥ ኃጢአተኛውም የመቶ ዓመት ሆኖት የተረገመ ይሆናልና” የሚል ቃል አለ። በሌላ በኩል፥ ይህ ዓረፍተ ነገር ዕድሜ በከፍተኛ ደረጃ እንደሚጨምርና እንድ ሰው መቶ ዓመት ሆኖት ገና ሕፃን እንደሚሆን ያመለክታል። ሰሺህ ዓመቱ መንግሥት ዘመን፥ ሰዎች ዕድሜ እስኪጠግቡ ይኖራሉ። ይህ ግን ላለመሞታቸው ዋስትና አይሰጥም። በተቃራኒው በመቶ ዓመት ዕድሜው የሚሞት ሰው የሚሞተው በኃጢአቱ ምክንያት ስለሚሆን ሞት የሚመጣው እንደ ፍርድ ነው። 

ሰሺህ ዓመቱ መንግሥት ሞተው፥ በዚያው ዘመን መጨረሻ የሚነሥ ሰዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ የሚያሳይ መረጃ አለ። ይሁንና፥ ይህ ትምህርት ግልጥ በሆነ የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ላይ የተመሠረተ አይደለም። ቢሆንም ከዚህ የተሻለ ማብራሪያ ለማቅረብ አይቻልም። የሺህ ዓመቱ ቅዱሳን ከሞት እንደሚነሡ ሁሉ፥ በሕይወት የሚኖሩ የሺህ ዓመቱ ቅዱሳን ይነጠቃሉ ወይም እንደ ቤተ ክርስቲያን ሞትን ሳይቀምሱ ይወሰዳሉ። ይህም አሁን ያላቸውን ምድርና ሰማያትን ለመጠቅለል የሚደረግ ዝግጅት ነው። 

ሰ. የኃጢአተኞች ትንሣኤ 

የመጨረሻው ትንሣኤ ኃጢአተኞችን ብቻ የሚመለከት ይመስላል። ስለ ታላቁ የነጭ ዙፋን ፍርድ ራእይ 20፡11-15 ውስጥ የተጻፈው ቃል እንደሚያስረዳው፥ ቀደም ሲል ያልተነ ሙታን ሁሉ ከሞት ተነሥተው በእግዚአብሔር ፊት ለፍርድ ይቆማሉ። ከአዲስ ሰማያትና ምድር መፈጠር በፊት ይህ የመጨረሻው ትንሣኤ ነው። የዚህ ፍርድ ዝርዝር ነጥቦች በቀጣዩ ምዕራፍ ውስጥ ይቀርባሉ። 

በአጠቃላይ፥ ሰዎች ሁሉ ከሞት እንዲነሡ የተወሰነ ስለመሆኑ መጽሐፍ ቅዱስ በግልጥ ይናገራል። ዳንኤል ጠቅለል አድርጎ እንዲህ ይገልጠዋል። “በምድርም ትቢያ ውስጥ ካንቀላፉት ብዙዎች ይነቃሉ፤ እኩሌቶቹ ወደ ዘላለም ሕይወት፥ እኩሌቶቹም ወደ እፍረትና ወደ ዘላለም ተስቁልና ፣ (12፡2)። ሰዎች ቢሞቱም ይነሣሉ። ነገር ግን ትንሣኤዎች አንድ ዓይነት አይሆኑም። የሕይወት ትንሣኤ፥ የአማኞች አካል የክርስቶስን የትንሣኤ አካል የሚመስልበት የከበረ ትንሣኤ ነው። 

የኩነኔ ትንሣኤ ግን እጅግ የከፋ ትእይንት ይሆናል። የዚህ ትንሣኤ ተቋዳሾች ለዘላለም የሚኖር አካል ቢሰጣቸውም፥ ኃጢአተኛና ለሥቃይ የተጋለጠ አካል ይሆናል። እንደ ዲያብሎስና እጋንንቱ ለዘላለም በእሳት ባሕር ውስጥ ይኖራሉ። ይህ አስገዳጅ እውነት ነው ሰዎች ወንጌልን እስከ ዓለም ዳርቻ ይዘው እንዲሄዱ ያደረጋቸው። ጥረቱ በተቻለ መጠን ብዙዎችን ከእሳት ነጥቆ ለማውጣትና በኃጢአተኞች ላይ ሊመጣ ከተቆረጠው የእግዚአብሔር ቁጣ ለማዳን ነው (ይሁዳ 23)። ለጻድቃን ግን የትንሣኤው ትምህርት የተስፋ መሠረት ነው። ምንም እንኳን የመጨረሻው የቤተ ክርስቲያን ትውልድ ሞትን ሳይቀምስ የሚነጠቅ ቢሆን፥ ለአብዛኛው ዓለም ግን ከመቃብር ትንሣኤ ለምድር የተዘጋጀውን አካል እግዚአብሔር ለከበረ ሕልውናው ተስማሚ አድርጎ የሚለውጥሰት እሠራር ነው።

ምንጭ፡- “ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ ጭብጦች” መጽሐፍ በዶክተር ሉዊስ ስፔሪ ቼፈር የተጻፈ እና በተክሉ መንገሻ የተተረጎመ ነው፡፡ እግዚአብሔር ስለ እነዚህ ቅዱሳን ድንቅ ስራ የተመሰገነ ይሁን፡፡ ማሳሰቢያ፡- ይህን ጽሁፍ መቀየርም ሆነ ለሽያጭ ማዋል በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡

Leave a Reply

%d bloggers like this: