እስራኤል በታሪክና በትንቢት

ሀ. እስራኤል ከሥፍሩ-ዘመናት ጋር ያላት ግንኙነት 

የእስራኤል ታሪክ በዘፍጥረት ምዕራፍ 12 ለአብርሃም በቀረበለት ጥሪ የሚጀምር ሲሆን፥ የብሉይ ኪዳን ዓቢይ አሳብ ነው። አዲስ ኪዳን ወንጌሳትና የሐዋርያት ሥራ ውስጥ፥ ከመጀመሪያው ክፍለ-ዘመን ስለ እስራኤል ተጨማሪ ግንዛቤ ተሰጥቷል። በሌሎች የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት ውስጥም ስለ እስራኤል የተጠቀሱ ታሪካዊና ትንቢታዊ ነገሮች አሉ። 

ከተስፋ ቃሉ ሥፍረ-ዘመን (ምዕራፍ 20ን ይመልከቱ) ጀምሮ፥ እስራኤል የሁሉም ሥፍረ-ዘመናት ተካፋይ ናት። በተስፋ ሥፍረ-ዘመን ከአብርሃም ጋር የተደረገው ቃል ኪዳን እግዚአብሔር በቀጣይ ትውልዶች ከእስራኤል ጋር ላከናወናቸው ተግባራት ሰፊ መሠረት ጥሏል። የሕግ ሥፍረ-ዘመን በዘፍጥረት ምዕራፍ 19 የሚጀምር ዋነኛ የእስራኤል ሕይወት ነው። ይህ ዘመን የብሉይ ኪዳን ዋና ሥፍረ-ዘመን እንደመሆኑ፥ የእስራኤልን ታሪክ እስከ ጌታ ስቅለት ድረስ የሚወስን በመሆን ኖሯል። ከተመዘገበው የእስራኤል ታሪከ አብዛኛው ከሕግ ሥፍረ-ዘመን ጋር ይዛመዳል። 

በጸጋ ሥፍረዘመን፥ እስራኤል የጸጋን ዕድሎች ማለት ድነትንና የሕይወትን መመሪያ ከአሕዛብ ጋር ትጋራለች። እስራኤል በወደፊቱ ሥፍረ-ዘመን ተስፋ የተገባላትን ምድር በመያዝና ለኢየሱስ ክርስቶስ ንጉሥነት በመገዛት ዓቢይ ሚና ትጫወታለች። ምንም እንኳ ከአሕዛብ ጋር ሲነጻጸር አነስተኛ ቢሆን፥ እስራኤል ከእብርሃም ጀምሮ እስከ መጨረሻው ባለው የዓለም ታሪክ ውስጥ ከፍተኛ ሚና ትጫወታለች (ለተጨማሪ ማብራሪያ ስፍረ-ዘመናት የሚልውን ርዕስ ይመልከቱ)። 

ለ. እስራኤል ከቃል ኪዳኖች አንጻር 

መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቃል ኪዳኖች ከተለያዩ ሥፍረ-ዘመናት ጋር በቅርብ የተያያዙ ናቸው። ዘፍጥረት ምዕራፍ 12 ውስጥ ከሚገኘው የአብርሃም ቃል ኪዳን ጀምሮ በእያንዳንዱ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቃል ኪዳኖች ውስጥ እስራኤል ዋነኛ ሚና አላት። (ምዕራፍ 21 ውስጥ ፡፡ቃል ኪዳኖቹ” የሚለውን ይመልከቱ።) 

በእስራኤል ታሪክና በትንቢት ውስጥ አምስቱ ቃል ኪዳኖች ወሳኝ ናቸው። አስቀድሞ እንደተገለጠው፥ አብርሃማዊው ቃል ኪዳን ለእስራኤል ፕሮግራም መሠረት ነው። በሕግ ሥፍረ-ዘመን የሙሴ ሕግ የእስራኤልን ሕይወት እቅድመ ሁኔታነት የሚወሰን ሲሆን፥ ከዘጸአት 19 ጀምሮ ከጠቅላላው ብሉይ ኪዳን ጋር ይዛመዳል። ከነዓንን ይወርሱ ዘንድ የተሰጠው ቃል ኪዳን ከእስራኤል የመሬት ይዞታ ጋር ይገናኛል። የመሬት ይዞታው ተለዋዋጭ ገጽታ ሲኖረውም፥ የኋላ ኋላ በሺህ ዓመቱ መንግሥት ጊዜ የከነዓን ምድር ለዘለቄታው በእስራኤል ቁጥጥር ሥር ይውሳል። ለዳዊት የተገባለት ቃል ኪዳን እስራኤል ከዳዊት ዙፋን ጋር ያላትን ግንኙነት የሚወሰን ሲሆን፥ ወደፊት በሺህ ዓመቱ ዘመን ክርስቶስ በምድር ላይ እንደሚነግሥና፥ ዳዊትም ከሞት ተነሥቶ በልዑልነት የሚገዛ መሆኑን ያመለክታል። ብሉይ ኪዳን ውስጥ የተተነበየው አዲስ ኪዳን እስራኤል በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ ከምታገኘው በረከት ጋር የሚገናኝ ሲሆን፥ በሙሴ በኩል ከተሰጠው ቃል ኪዳን ጋር የሚነጻጸርና የሚተካውም ነው። ቃል ኪዳኖች ከእስራኤል ጋር ያላቸው ዝርዝር ግንኙነት ምዕራፍ 21 ውስጥ ተዘርዝሯል። 

ሐ. የእስራኤል ታሪክ በብሉይ ኪዳን 

ምንም እንኳ ትክክለኛው የእስራኤል ታሪክ የሚጀምረው እስራኤል ከተባለው ያዕቆብ ሲሆን፥ በአብዛኛው የአብርሃምንና የይስሐቅን ሕይወት ያካትታል። አብርሃምና ይስሐቅ የያዕቆብ አባትና አያት ናቸው። መጀመሪያ በከለዳውያን ዑር ይኖር የነበረው አብርሃም በሰሜን ምዕራብ ወደምትገኘው ካራኝ ሁለት ሺህ ኪሎ ሜትር ያህል ከእሳቱ ጋር ተጉዞ በመሄድ ሀብታም ከብት አርቢ ሊሆን በቅቷል። አባቱ ከሞተ በኋላ ለእግዚአብሔር በመታዘዝ፥ ከሚስቱ ሣራና ከወንድሙ ልጅ ሎጥ ጋር ወደ ተስፋይቱ ምድር ተጓዘ። ያም ከካራን ወደ ሰሜን ምዕራብ ተጨማሪ የሁለት ሺህ ኪሎ ሜትር መንገድ ነበር። ከዚያም እግዚአብሔር ሰተስፋይቱ ምድር ከአብርሃም ጋር ይሠራ ጀመር። 

ታላቅ በሆነው አብርሃማዊ ቃል ኪዳን አማካይነት ታላቅ ሰውና የታላቅ ሕዝብ አባት እንደሚያደርገው፥ እንዲሁም በዘሩ በኩል ዓለሙን ሁሉ እንደሚባርክ እግዚአብሔር ለአብርሃም ቃል ገብቶለታል። ቀደም ሲል አብርሃማዊው ቃል ኪዳን ውስጥ እንደተመለከተው (ምዕራፍ 21)፥ እነዚህ የተስፋ ቃሎች በትክክል ተፈጽመዋል። አብርሃምና ሣራ እጅግ ካረጁና የመውለጃ ዕድሜያቸው ካለፈ በኋላ፥ በተአምራዊ መንገድ ይሰሐቅ ተወለደ። ከዚያም በተወሰነው ጊዜ፥ ይስሐቅና ርብቃ ያዕቆብንና ዔሳውን ወለዱ። ከመንትያ ወንድማማቾች መካከል ታናሹ ያዕቆብ የእስራኤል ሕዝብ መሪ ይሆን ዘንድ እግዚአብሔር መረጠው። 

የአብርሃም፥ የይስሐቅና የያዕቆብ ታሪክ ከዘፍጥረት 12-50 የተዘረዘረ ሲሆን፥ ከዚህ የምንረዳው እግዚአብሔር በዚህ ታሪክ ላይ የሰጠውን ትኩረት ታላቅነት ነው። በተለይም ጠቅላሳው የፍጥረት ታሪክ በሁለት ምዕራፎች (ዘፍጥ. 1-2)፥ ፀኃጢአት የመውደቅ ሁኔታም በአንድ ምዕራፍ (ዘፍጥ. 3) ብቻ ተጠቃሎ እንደቀረበ ስንመለከት፥ የነአብርሃም ታሪክ ዋነኛነት በግልጥ ይታያል። ከመለኮታዊ ዕይታ አንጻር፥ የእስራኤል ታሪክ ለጠቅላላው ታሪክ ቁልፍ ነው። 

ዘፍጥረት 15፡13-14 ውስጥ ለአብርሃም ከተሰጠው ትንቢት ጋር በሚስማማ መልኩ፥ በረሃብ ወቅት እስራኤላውያን ወደ ግብፅ ወረዱ። ወደዚያ የሚሄዱበት መንገድ የተጠረገላቸው የአገሪቱ ከፍተኛ ባለሥልጣን በነበረው ዮሴፍ አማካይነት ነበር። ግብፅ አብርሃምንና ቤተሰቡን በመልካም ሁኔታ ተቀብላ ዮሴፍ በሕይወት በኖረባቸው ጊዜያት ሁሉ ስትንከባከባቸው ቆየች። ይሁን እንጂ፥ የተደረገው የአገዛዝ ለውጥ የድሉት ማዕረጋቸውን ነጥቆ፥ ባሪያዎች ስላደረጋቸው፥ እስራኤሳውያን ላአያሌ መቶ ዓመታት የሥቃይ ሕይወት ኖሩ። በባርነታቸው ወደ ጌታ በጮኹ ጊዜ፥ ጌታ ሕዝቡን ወደ ተስፋይቱ ምድር ይመራቸው ዘንድ ሙሴንና ኢያሱን አስነሣቸው። ምንም እንኳ እስራኤላውያን በቃዴስ በርኔ እግዚአብሔርን ባይታዘዙት (ዘኁ. 14)፥ እና ከዚህም የተነሣ ለአርባ ዓመታት በምድረ በዳ ሲቅበዘበዙ፥ በመጨረሻ ግን እግዚአብሔር ከዮርዳኖስ በስተ ምሥራቅ ምድሪቱን እንዲይዙና ከሙሴ ሞት በኋሳ ዮርዳኖስን ተሻግረው አብዛኛውን ክፍል እንዲቆጣጠሩ አስችሏቸዋል። 

እስራኤላውያን ሰኢያሱ ዘመን ወደ ተስፋይቱ ምድር ተመልሰው እንደ አንድ አገር ቢበለጥጉም፥ መጽሐፈ መሳፍንት ውስጥ እንደተመለከተው በሥነ-ምግባራዊ ሕይወታቸው ከእግዚአብሔር ተለይተው ተዋረዱ። 

በዚህም ጊዜ እግዚአብሔር ነቢዩ ሳሙኤልን አስነሣ። እርሱም በአብዛኛው የእስራኤልን መንፈሳዊ ሕይወት ዳግም በመገንባት፥ ሰሳኦል፥ በጻዊትና በሰሎሞን ዘመነ መንግሥት ለነበረው ክብር መሠረት ጥሏል። የመጀመሪያው የእስራኤል ንጉሥ የነበረው ሳኦል ባይሳካለትም፥ እርሱን የተካው ዳዊት ታላቅ የጦር ሰው በመሆኑ የተስፋይቱ ምድር አካል የሆኑትን ሰፊ ግዛቶች ላመያዝ ችሏል። 

የዳዊት ልጅ ሰሎሞን ለአብርሃም የተነገሩትን አብዛኛዎቹን አካባቢዎች ማለት፥ ከግብፅ ወንዝ እስከ ኤፍራጥስ ወንዝ እስኪቆጣጠር ድረስ ድንበሩን አሰፋ። ሚስቶችን እንዳያበዛና ሰፈረሶች ብርታት እንዳይደገፍ እግዚአብሔር የሰጠውን ትእዛዝ አለመስማቱ (ዘዳግ. 17፡16-17)፥ መንግሥቱ እንዲከፋፈልና ከርሱ በኋላ የእስራኤል ኃይል በፍጥነት እንዲንኮታኮት ምክንያት ሆኗል። የሰሎሞን ልጆች ያደጉት ለእግዚአብሔር ሕግ ግድ ባልነበራቸው አረማውያን ሚስቶቹ ነበር። ከርሱ ሞት በኋላ ብዙም ሳይቆይ፥ እሥሩ የስሜን ነገዶች (እስራኤል) ለብቻቸው ተገንጥሰው በክፉ ነገሥታት ሲመሩ ኖረዋል። እነዚህ ወገኖች በ721 ዓ.ዓ. በአሦራውያን እንዲማረኩ እግዚአብሔር ፈርዶባቸዋል። ሁለቱ የደቡብ መንግሥት ነገዶች (ይሁዳ)፡ምንም እንኳን አንዳንድ ፈሪሃ እግዚአብሔር ያደረባቸው ነገሥታት የተነሡላቸው ቢሆንም፥ እንደ እስራኤል ሁሉ በኃጢአት ወጥመድ መያዛቸው አልቀረም። ከዚህም የተነሣ፥ በ605 ዓ.ዓ. በባቢሎናውያን ምርኮ ተወሰዱ። 

ኤርምያስ 29፡10 ውስጥ በተሰጠው የተስፋ ቃል መሠረት፥ ከሰባ ዓመቱ የባቢሎናውያን ምርኮ ፍጻሜ በኋሳ እስራኤል ወደ ምድሯ ተመለሰች። መጽሐፈ ዕዝራ የሕዝቡን መመለስና ቤተ መቅደሱን ለመገንባት ለሀያ ዓመታት ያደረጉትን ጥረት ይገልጣል። ነህምያ ደግሞ ከአንድ መቶ ዓመታት ያህል ጊዜ በኋላ የኢየሩሳሌምን ቅጥሮችና የከተማይቱን ዳግም መታነጽ በመግለጥ ታሪኳን ይቋጫል። ይሁንና፥ እስራኤላውያን ወደ ምድራቸው ቢመለሱም፥ እግዚአብሔርን ባለመከተላቸው ሳቢያ ለ200 ዓመታት ሰሜዶንና በፋርስ አገዛዝ ሥር ቆይተዋል። ታላቁ እስክንድር በ323 ዓ.ዓ. ከሞተ በኋላ ደግሞ ከሦሪያና ከግብፅ ጋር ይዋጉ ጀመር። 

በ242 ዓ.ዓ. ኃያሉ የሮማውያን አገዛዝ ሲሲሊን በመውረር የመስፋፋት ዘመቻውን ተያያዘው። ኢየሩሳሌም ራሷ በ63 ዓ.ዓ. ታምፒዬስ በተባለው የሮም ጄኔራል በቅኝ ተያዘችና በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አይሁዶችን በባርነት ያጋዙ ሮማውያን ጭካኔ 

ማነጣጠሪያ ሆነች። በኋላ በሮማውያን ባለሥልጣናት ኢየሱስ ክርስቶስ ተሰቀለ። በመጨረሻም (በ70 ዓ.ም.) የኢየሩሳሌም ከተማ ተደመሰሰች፥ እስራኤላውያንም አገራቸውን ጥለው በዓለም ሁሉ እንዲበተኑ ተደረገ። እስከ ሀያኛው ክፍለ-ዘመን ድረስ እሰራኤላውያን ወደ አገራቸው ለደመሰሰና ምድራቸውን እንደ አገር ለማደራጀት አልቻሉም ነበር። በ1948 ዓ.ም. ነው እንደ አንድ ፖለቲካዊ መንግሥት እውቅና ያገኙት። 

መ. የእስራኤል ታሪክና የተፈጸመ ትንቢት 

የብሉይ ኪዳን ታሪክ በአብዛኛው የታላላቅ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትንቢቶች ፍጻሜ ነው። በመቶዎች የሚቆጠሩ ትንቢቶች ቃል በቃል ተፈጽመዋል። ለአብርሃም በተሰጡት ትንቢቶች መሠረት፥ እስራኤል ታላቅ እገር ሆነች። ብሉይ ኪዳን እስራኤላውያን ከምድራቸው እንደሚወጡ የሚናገሩ ሦስት ትንቢቶችን ያስተላለፈ ሲሆን፥ እነዚህም በሚከተለው መንገድ ተፈጻሚነትን አግኝተዋል፡- (1) ወደ ግብፅ መሄዳቸው፥ ለባርነት መዳረጋቸውና ተለቀው መመለሳቸው፥ (2) በባቢሎናውያኝና አሦራውያን ምርኮ ተወስደው ከሰባ ዓመት በኋላ ወደ አገራቸው ተመልሰዋል፥ (3) በ70 ዓ.ም. ኢየሩሳሌም በተደመሰሰች ጊዜ ከምድራቸው ተበትነዋል። የእስራኤላውያን ምድራቸውን መያዝና እንደገና የመነጠቅ ሰፊ እንቅስቃሴ ለጠቅላላው ታሪካቸው ጠቃሚ መነሻ ፈጥሯል (ዘፍጥ. 15: 13-16፤ ዘዳ. 28፡62-67፤ ኤር. 25 ፡11-12፤ በተጨማሪም ዘሌ. 26፡3-46፤ ዘዳ. 30፡1-3፤ ህ . 1፡8፤ መዝ. 106፡1-48፤ ኤር. 9፡16፤ 18፡15-17፤ ሕዝ. 2 ፡14-15፤ 20፡23፤ 22፡15፤ ያዕ. 1፡1)። 

ስለ ያዕቆብ ልጆች ባሕርይና ፍጻሜ የተሰጡት ትንቢቶች ለእስራኤል ታሪክ በጣም አስፈላጊዎች ናቸው (ዘፍጥ. 49፡1-28)። እግዚአብሔር ከአሥራ ሁለቱ የእስራኤል ልጆች ጋር ስለሚኖረው ግንኙነት ብሉይ ኪዳን ውስጥ ብዙ ትንቢቶች ተሰጥተዋል። 

ሌላው የትንቢትና ፍጻሜው ዋና ጉዳይ ከዳዊት መንግሥት ጋር ይዛመዳል። ለዳዊት ከተገባለት ቃል ኪዳን ጋር በተያያዘ ለርሱና ለዘሩ በተገባለት ቃል ኪዳን መሠረት የመንግሥት ዙፋን ለዘላለም ከቤቱ እንደማይጠፋ ተስፋ ተሰጥቶታል (2ኛ ሳሙ. 1፡16፤ መዝ. 89፡35-36፤ ኤር. 33፡21፤ ዳን. 7፡14)። እግዚአብሔር ከሳኦል፥ ዳዊትና ሰሎሞን፥ እንዲሁም ከቀጣዮቹ የእስራኤልና የይሁዳ መንግሥታት ጋር የገባቸው የበረከትና የመርገም ቃል ኪዳኖች በቀጥታ ተፈጽመዋል። 

ሠ. ስለ እስራኤል 490 ዓመታት የተነገረ ትንቢት 

[* “ሻቡአ” የሚለው የዕብራይስጥ ቃል በብሉይ ኪዳን የጭሰሳት ስብስብ” የሚል አሳብ አለው። ይህ ቃል በብሉይ ኪዳን ውስጥ 20 ጊዜ ተጠቅሷል። ከእነዚህ ሦስት ጊዜ “ሰባት ስብስብ” የሚል ትርጉምን “ቀን” ከሚል ቃል ጋራ በመያያዝ ተሰጥቶታል (ሕዝ. 45፡21፤ ዳን. 10፡2፥3)። ስድስት ጊዜ ደግሞ “በሳምንት ያሉን ሰባት ቀናትን” በማመልከት ጥቅም ላይ ውሏል (#ፍጥ. 29፡27 ፥ 28፤ ዘሌዋ. 12፡5፤ ዘዳ. 16፡9፤ ኤር. 5፡24)። አምስት ጊዜ ደግሞ የሰባቱ ሱባኤ ሰዓል* የሚገልጥ ሆኖ እናገኛለን (ዘፀ. 34፡22፤ ዘኁ. 28፡26፤ ዘዳ. 16፡10፥ 16 2ኛ ዜና 8፡13)። 

ምንንም ሳያመለክት የሰባት ስብስብ” የሚል ትርጉምን ሰባት ጊዜ ተጠቅሷል (ዳን. 9:24-27)። ከእነዚህ ክፍሎች የቃሉን ትርጉም የዐውደ ምንባቡ ይዞት ነው የሚወስነው** 

ሰአጠቃላይ የሻሱአ” የሚለው ቃል ሱባኤ ማለት ሲሆን ጥሬ ቃሉ ያዘለው አሳብ ግን የሰባት ስብስብ” ሆኖ፥ ትክክለኛው ትርጉም ግን በዐውደ ምንባቡ የሚወሰን ነው። ዳንኤል 9፡24-27 ውሰጥ ይህ ቃል አሎሳኤ” ተብሎ የተተረጎመ ሲሆን፥ ፅንሰ-አሳቡ ግን ሰባት የዓመታት ስብስብን ያመለክታል። በዚህ ክፍል ነቢዩ የሚናገረው ስለተለያዩ ሰባት ዓመታት ነው (ማለትም 490 ዓመታት)። በ1980 ዓ.ም. ሰአማርኛ የታተመው የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም እንደዚህ ነው የሚተረጎመው። ለዚህ አተረጓጎም ምክንያቶቹ የሚከተሉት ናቸው፡–1, ዳንኤል 9፡24-27 ውስጥ ያለውን አሳብ ከማንሣቱ በፊት ሰ9፡2 ስለ ናዓምታት” ተናግሯል። ይህም ኤርምያስ 25፡11 እና 29፡10)፡፡ ውስጥ የተጠቀሰውን የምርኮ ወቅት የሚያመለክት ነው። ይህ ምርኮ እስራኤል የጌታን ሕግ፥ ሰትለይም የስድስት ዓመቱ ምድሩን የማሳረፍን ሕግ ሳልመጠበቋ የደረሰባት ቅጣት ነው (ዘሌዋ. 25፡24 4፥ 8፣ 26፡34፥ 43)። እስራኤል ይህን ሕግ ሰባ ጊዜ መተላለፏን ስናሰላ 490 ዓመት ያህል ይሆናል። ስለዚህ ቅጣታቸው ለሰሳ ዓመት ያህል ነበር። 

2. ዳንኤል 9፡24-27 ውስጥ የተጠቀሰው ሁኔታ 490 ቀናትኝ የሚያመለክት ጊዜ ሊሆን አይችልም። 3. በዳንኤል 9፡27 ውዕጥ ክሲዩ ኪዳኑ “ሰሰባኛው ቡአ አጋማሽ” እንደሚፈርስ ይተነብያል። ይህ (4ዓመታትን” እንደሚያመለክት ተደርጎ ከተወሰደ ዳንኤል 7፡25 እና 12፡7 ውስጥ እንዲሁ ከራእይ 12፡14 ውስጥ ካለው አሳብ ጋር የሚስማማ ይሆናል። 

በማጠቃለል ሳቡአ በዳንኤል 9 መሠረት በአመዛኙ የሚያመለክተው የሰባት ዓመታት ስብስብ” ነው። ከዚህ ሌላ ምንም ዓይነት ትርጓሜ ክፍሉ ጋር የሚሄድ አይሆንም፤ ይህ ቢሆንም የአማርኛውን የመጽሐፍ ቅዱስ አጠቃቅም ለመከተል ሰባት ሰብስብ” የሚለው አሳብ በተቀረው በዚህ ምዕራፍ ክፍል ሰባት” ከማለት 

“ሱባዔ” በሚለው ቃል ተተክቷል። ** ይህ “እር”” ከሚለው ቃል ትርጓሜ ጋር ይመሳሰላል። “አሦር” የሚለው የዕብራይስጥ ቃል በአብዛኛው “አሥር ቀን” የሚል ትርጓሜ ይሰጠዋል። ይህ ቃል ብሉይ ኪዳን ውስጥ ከተጠቀሰባቸው 16 ስፍራዎች 13 ያህሉ ያሉበት ዕውደ ምንሳብ እንዲህ ያለ ትርጓሜ እንዲሰጠው ያደርጉታል። ሆኖም ሦስት ጊዜ የሙዚቃ መሣሪያን አስመልክቶ “አምሮ፡ይባል አሥር አውታር” የሚል ትርጉምን ይዟል (መዝ. 33፡2፣ 9፡3፤ 144፡9)። “አሦር፡፡ልክ እንደ ወላቡአ” ስብስብን የሚያመለክት ቃል ነው። ስለዚህ የአሥር ስብስብ” የሚል አሳብ አለው። በመሆኑም እንደ ዐውደ ምንባሱ ትርጉሙም ይለያያል።] 

በዳንኤል በኩል ከተሰጡት ዓበይት ትንቢቶች አንዱ፥ ዳንኤል 9፡24-27 ውስጥ የሚገኘው ነው። በዚህ ስፍራ መልአኩ ገብርኤል ለዳንኤል በገለጠው መሠረት የእስራኤል የወደፊት ታሪክ “ሰባ ሱባዔ”* ወይም ሰባ ሰባቶችን (490 ዓመታት) የሚያካትት ይሆናል። “ዓመፃን ይጨርስ፥ ኃጢአትንም ይፈጽም፥ በደልንም ያስተሥርይ፥ የዘላለምን ጽድቅ ያገባ፥ ራእይንና ትንቢትን ያትም፥ ቅዱሰ ቅዱሳኑንም ይቀባ ዘንድ በሕዝብህና በቅድስት ከተማህ ሳይ ሰባ ሱባኤ ተቆጥሮአል” (ዳን. 9፡24)።

ትንቢቱ የሚጀምረው ኢየሩሳሌምን ለማደስና ለመገንባት ትእዛዝ በሚወጣበት ጊዜ ሲሆን (ዳን. 9:25)፥ መሢሕ የሆነው ልዑል ከመምጣቱ በፊት ከጠቅላላዎቹ 490 ዓመታት 483ቹ ይፈጸማሉ። የመጽሐፍ ቅዱስ ምሁራን ይህን ምንባብ በተለያየ መንገድ ቢፈቱትም፥ ከሁሉም የሚሻለው፥ ይህንኑ የ490 ዓመታት ክፍለ ጊዜ ህምያ ኢየሩሳሌምን ዳግም ከገነባበት 445ዓ.ዓ. መጀመሩ ይመስላል። ይህ የሚፈጸመው ክርስቶስ በመስቀል ላይ በሚሠዋበት በ32 ዓ.ም. ገደማ ነበር። በቅርቡ የተደረገው ምሁራዊ ትንታኔ ክርስቶስ የሞተበትን ጊዜ 33 ዓ.ም. ቢያደርገውም፥ ብዙዎቹ ተንታኞች ግን 30 ዓ.ም. ነው ብለዋል። 

በዳንኤል ትንቢት መሠረት ከ483 ዓመታት በኋላ መሞት ነበረበት። ይህም የሰባው ዓመት ሱባዔን በተመለከተ ያልተፈጸመ ሰባት ዓመት እንዳለ ያሳያል (ዳን. 9፡26)። የኢየሩሳሌም መፍረስ እንደተተነበየው በ70 ዓ,ም ኢየሩሳሌም በፈረሰችበት ወቅት ተፈጽሟል። 

በ483ቱ ዓመታት ወይም 69ኙ “ሳምንታት” ሱባዔ እና በመጨረሻዎቹ ሰባት ዓመታት ጅማሬ ወይም በሰባተኛው “ሳምንት” መካከል ረጅም ጊዜ መኖሩ ዳንኤል ትንቢት ውስጥ ተመልክቷል። የመጨረሻው ሳምንት ከተማይቱን ካጠፉት ሕዝቦች የወደፊት ልዑል ጋር የተደረገ ቃል ኪዳንን የሚያመለክት ይመስላል። የኢየሩሳሌምን ከተማ የደመሰሷት ሮማውያን በመሆናቸው፥ የሚመጣው አለቃ” (ዳን. 9፡26) የሚታደሰው የሮም መንግሥት ገዥ ሳይሆን አይቀርም። ብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ምሁራን ይህ የሚፈጸመው፥ ወደፊት ቤተ ክርስቲያን ከተነጠቀች በኋላ ነው ይላሉ። 

ዳንኤል 9፡27 ውስጥ እንደተመለከተው፥ ይህ አለቃ ከእስራኤል ጋር ለሰባት ዓመታት የሚቆይ ቃል ኪዳን ያደርጋል። ቃል ኪዳኑ በሱባዔው መካከል ስለሚፈርስ፥ የመጨረሻዎቹ ሦስት ተኩል ዓመታት ለእስራኤል የመከራና የስደት ጊዜ ይሆናሉ። ይህ ክፍለ-ጊዜ ራእይ 6-18 ውስጥ የተመሰከተው ትንቢት ርእሰ ጉዳይ ሲሆን፥ ራእይ 19 ውሰጥ በተገለጠው የክርስቶስ ዳግም ምጽአት ይጠናቀቃል። የሚመጣው ገዥ መሥዋዕትና ቁርባን አስቀርቶ ቤተ መቅደሱን እንደሚያስረክስ መተንበዩ ልብ ሊባል የሚገባ ነገር ነው። ይህ የሚያመለክተው፥ ወደፊት ኢየሩሳሌም ከተማ ውስጥ ቤተ መቅደስ እንደሚሠራና መሠረታውያን አይሁዶች ከክርስቶስ ዳግም ምጽአት በፊት የሙሴ የመሥዋዕት ሥርዓትን የሚጀምሩ መሆኑን ነው። 

የመጀመሪያዎቹ 483 ዓመታት እንደተተነበዩ በቃል መፈጸማቸው ጠቃሚ ጉዳይ ነው፡ዳንኤል 9፡25 ውስጥ እንደተመለከተው፥ ኢየሩሳሌም ሰመጀመሪያዎቹ 49 ዓመታት ውስጥ እንደገና ተገንብታለች። ከ483 ዓመታት በኋላ መሢሑ ተገድሏል። የመጨረሻው ሱባዔ ክስተቶች ገና ወደፈት የሚፈጸሙና ወደ ክርስቶስ ዳግም ምጽአት የሚያመራውን 

የጊዜ ቅደም ተከተል የሚያሰናዱ ናቸው። 

ረ. ስለ መሢሑ ምጽአት የተነገረ ትንቢት 

የብሉይ ኪዳን ነቢያት የመሢሑን ሁለት ምጽአቶች ሊለዩ እንዳልቻሉ ከ1ኛ ጴጥሮስ 1፡10-11 እንረዳለን። በእግዚአብሔር ምክር ውስጥ የአሁኑ ዘመን ፍጹም ስውር ስለነበር፥ በክርስቶስ የመጀመሪያ ምጽአት የተፈጻሙትና ገና በዳግም ምጽአቱ የሚፈጸሙ ሁነቶች የአፈጻጻም ጊዜ ለብሉይ ኪዳን ነቢያት ግልጥ ሆኖ አልታያቸውም። 

ኢሳይያስ 61፡1-2 ይህን ሁኔታ ያብራራዋል። ክርስቶስ ይህን ምንባብ ቅፍርናሆም ምኩራብ ውስጥ ስለ መጀመሪያ ምጽአቱ የተጠቀሱትን ነገሮች (ሉቃስ 4፡18-21) ካነበበ በኋላ፥ በዳግም ምጽአቱ የሚፈጸሙትን በዝምታ አልፏቸዋል። በተመሳሳይ ሁኔታ፥ መልአኩ ገብርኤል ስለ ክርስቶስ አገልግሎት ሲናገር፥ የመጀመሪያውንና ሁለተኛውን ምጽአቶች ተግባራት አንድ ላይ አጣምሮ ገልጧቸዋል (ሉቃስ 1፡31-33)። 

ክርስቶስ ብሉይ ኪዳን ትንቢቶች ውስጥ ዝም እንደሚል የመሥዋዕት በግ (ኢሳ. 53፡1-12) እና ድል እንደሚነሣ ገናና የይሁዳ ነገድ እንበሳ (ኢሳ. 11፡1-12፤ ኤር. 23፡5-6) ተገልጧል። የብሉይ ኪዳን ነቢያት እነዚህን ሁለት የተራራቁ የትንቢት መሥመሮች በመመልከት፥ ይህ ሁሉ መች ይፈጸም ይሆን? ብለው ማሰባቸው አያስገርምም (1ኛ ጴጥ. 1፡10-11)። 

በትንቢት እንደተነገረው፥ መሢሑ ከይሁዳ ነገድ (ዘፍጥ. 49፡10)፥ ከዳዊት ቤት (ኢሳ. 11፡1፤ ኤር. 33፡23)፥ ከድንግል የመወለድ (ኢሳ. 7፡14)፥ በይሁዳ ቤተልሔም የሚወለድ (ሚክ. 5፡2)፥ የመሥዋዕትነት ሞት የሚሞት (ኢሳ. 53፡1-12)፥ የሚሰቀል (መዝ. 22፡1-21)፥ ከሞት የሚነሣ (መዝ. 16፡8-11) እና በሰማይ ደመና (ዳን. 7፡13) ዳግም ወደ ምድር የሚመለስ መሆኑ ተገልጧል (ዘዳ. 30፡3)። የናዝሬቱ ኢየሱስ ማንም ሊፈጽም በማይቻለው መልኩ ስለ መሢሑ የተነገሩትን ትንቢቶች ሁሉ ፈጽሟል። የቀሩትንም ወደፊት በዳግም ምጽአቱ ይፈጽማቸዋል። 

ሰ. ስለ እስራኤል በመጨረሻ መበተንና መሰብሰብ የተነገረ ትንቢት 

እስራኤልን አስመልክቶ ብሉይ ኪዳን ውስጥ የሚገኙት እጅግ ጠቃሚ ትንቢቶች በመጨረሻ መበተኗንና መሰብሰቧን የሚመለከቱ ናቸው። እስራኤላውያን ሁሉ ስለ ኃጢአታቸው በተተነበየባቸው ብሔራዊ ቅጣት መሠረት የሰሜኑ መንግሥት በአሦር፥ የደቡቡ በባቢሎን ምርኮ በመወሰድ ወደተለያዩ የዓለም ክፍሎች ተበትነዋል። ይህ የብዙ ትንቢቶች ፍጻሜ ነበር (ዘሌ. 26፡32-39፤ ዘዳ. 28፡63-68፤ ነህ. 1፡8፤ መዝ. 44፡11፤ ኤር. 9፡16፤ 18፡15-17፤ ሕዝ. 12፡14-15፤ 20፡23፤ 22፡15፤ ያዕ . 1፡1)። 

ለብዙ መቶ ዓመታት ብትበተንም እንኳ የእስራኤል ብሔራዊ ማንነት አልጠፋም (ኤር. 31፡36፤ ማቴ. 24፡34)። መሢሑ በመጀመሪያው ምጽአቱ ለመሰብሰባቸውና ለመንግሥታቸው ክብር ያቀረበላቸውን መለኮታዊ ችሮታ አልተቀበሉም (ማቴ. 23፡37 39)። በረሃ ለበረሃ መቅበዝበዛቸው ባበቃበት ቃዴስ በርኔ ላይ (ዘኍ. 14፡1-45)፥ ቅጣታቸው እንደገና ተራዘመ። ጌታ ዳግም እስኪመጣ ድረስም የሚቀጥል ይሆናል። ያኔ ያሕዌ ሕዝቡን ወደራሳቸው ምድር በመሰብሰብ፥ የገባላቸውን ቃል ኪዳናት ባርኮትና ክብር ሁሉ ያቀዳጃቸዋል (ዘዳ. 30፡1-10፤ ኢሳ. 11፡11-12፤ ኤር. 23፡3-8፤ ሕዝ. 37፡21-25፤ ማቴ. 24፡31)። 

ሽ. ስለ መጨረሻው ዘመን የተነገረ ትንቢት 

በዳንኤል 9፡27 ላይ በተመሠረተ አጭር ጥናት እንደተገለጠው፥ እስከ ክርስቶስ ዳግም ምጽአት ድረስ በሚዘልቁት የመጨረሻው ዘመን ክስተቶች ውስጥ እስራኤል አስደናቂ ሚና ትጫወታለች። መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን፥ የእስራኤልን የወደፊት ሁኔታ በተመለከተ በዘመኑ መጨረሻ አራት ዓበይት እንቅስቃሴዎች ይኖራሉ። 

1. እስራኤል እንደ ፖለቲካዊ መንግሥት ዳግም እንደምትቋቋም ተገልጧል። “ከሚመጣው አለቃ” ጋር ቃል ኪዳን ለማድረግ ይቻላት ዘንድ፥ እንደ ፖለቲካዊ መንግሥት እንደገና መቋቋም ያስፈልጋታል። ይህም በሚያስደንቅ ሁኔታ እንደ አገር እውቅናና ተስፋ ከተገባለት ምድር የተወሰነ ክፍል ባገኘችበት ሚያዝያ 1948 ዓ.ም. (እ.አ.አ.) ተፈጽሟል። ከዚያ በኋላ በነበሩት ዓመታት፥ ዳርቻዋ እየሰፋ ከመሄዱም በላይ ኃይሏም እየተጠናከረ መጥቷል። ምንም እንኳ ዛሬ እስራኤል አነስተኛ አገር ብትሆን፥ በዓለም ጉዳዮች ላይ ዋና ስፍራ ለመያዝ በቅታለች። ይህ ወደፊት ለሚፈጸሙት ሌሎች ትንቢቶች መግቢያ ነው። 

2. ዳንኤል 9፡27 ውስጥ እንደተገለጠው፥ እስራኤል ከሜድትራኒያን የሮም እሕዛብ እለቃ ጋር ለሰባት ዓመታት ቃል ኪዳን ታደርጋለች። በዚህም ሠላምና ዋስትና ወደምታገኝበት የቃል ኪዳን ክፍለ-ጊዜ ትዘልቃለች። በዚህ ጊዜ ሌሎችም አይሁዶች ወደ ተስፋይቱ ምድር እንደሚመለሱና፥ አገሪቱ መዋለንዋያዊም ሆነ ፓለቲካዊ የብልጥግና እርከን ላይ እንደምትወጣ አይጠረጠርም። 

3. ይሁን እንጂ፥ የተገባው ቃል ኪዳን ከስት ዓመት ተኩል በኋላ ይፈርስና እስራኤል ከምገስ ይልቅ ስደት ይገጥማታል። ይህ “የያዕቆብ የመከራ ቀን” (ኤር. 30፡7)፥ የተባለው ታላቅ መከራ ነው (ዳን. 12፡1፤ ማቴ. 24፡21፤ ራእይ 7፡14)። በሚቀጥሉት ሁለት ምዕራፎች በዚህ ጉዳይ ላይ ሰፋ ያለ እሳብ ይቀርባል። 

4. በሺህ ዓመቱ መንግሥት የእስራኤል ስከብር መመለስ የክርስቶስን ዳግም ምጽአት ተከትሎ የሚከናወን ሲሆን፥ ክርስቶስ በምድር ላይ በሚገዛበት የሺህ ዓመት ጊዜ ሁሉ ይቀጥላል። 

የእስራኤልን መመለስ አራት ደረጃዎች የመረዳቱ አስፈላጊነት። የመጀመሪያው ደረጃ ከዚህ ቀደም ከመፈጸሙና ሁለተኛው ደረጃ ምናልባትም ቤተ ክርስቲያን እስከምትነጠቅበት ጊዜ ድረስ የሚዘገይ ከመሆኑ እውነት አንጻር ሊታይ ይችላል። ለማንኛውም እስራኤል ከፍተኛ ሚና ለምትጫወትበት የመጨረሻ ዘመን ክስተቶች ሁኔታዎች በመመቻቸት ላይ ናቸው። 

ቀ. ስለ መሢሐዊው መንግሥትና የእግዚአብሔር ቀን የተነገረ ትንቢት 

ይህን እሳብ በተመለከተ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከሰፈሩት ጥቅሶች መሐዊውን መንግሥት የሚመለከተውን ያህል ብሉይ ኪዳን ትንቢት ውስጥ የተተኮረሰት ጉዳይ የለም። እስራኤል ላይ እንደሚደርሱ ከተተነበዩት ቅጣቶች ሁሉ ባሻገር፥ ሕዝቦቿ ዳግም ወደ አገራቸው ሲሰበሰቡ የምትጎናጸፈው ክብር ይገኛል። ይህም በመሢሑ ንጉሣቸው የከበረ ዘመን የሚሆንና ከቁጥር ሁሉ ከላቀ በረከት ጋር የሚመጣ ሲሆን፥ ራእዩ ለነቢያት ሁሉ ተሰጥቷል። ትንቢቱ ይፈጸም ዘንድ እስራኤላውያን ከምድራቸው ተበትነው ለብዙ ምዕት ዓመታት እንደተሠቃዩ ሁሉ፥ በተቤዠችውና በከበረችው ምድር አስደናቂ በረከቶችን ወደ መቀበሉ ተሐድሶ የሚደርሱትም ሰተምሳሌታዊ ሳይሆን በቀጥተኛ መልኩ ነው (ኢሳ. 11-12፤ 24፡22-27፡13፤ 35፡1-10፤ 52፡12፥ 54-55፤ 59፡20-66፡24፤ ኤር. 23፡3-8፤ 31፡1-40፤ 32፡37-41፤ 33፡1-26፤ ሕዝ. 34፡11-31፤ 36፡32-37፡28፤ 40፡1-48፡35፤ ዳን. 2፡44-45፣ 7፡14፤ ሆሴ. 3፡4-5፤ 13፡9-14 :9፤ ኢዩ. 2፡28-3፡21፤ አሞጽ 9፡11-15፤ ሰፎ. 3፡14-20፤ ዘካ. 8፡1-22፤ 14፡9-21)። 

የእግዚአብሔርን መንግሥት በተመለከተ የብሉይ ኪዳን ትንቢቶች ብዙውን ጊዜ የንጉሡ መመለስ ትንቢቶች አካል ናቸው። እነዚህ ሁለት ጉዳዮች በአንድ ላይ ሲዋሐዱ “የእግዚአብሔር ቀን” የሚል አሳብ ይሰጡናል። ይህ ከቤተ ክርስቲያን መነጠቅና ያን ተከትሎ በምድር ላይ ከሚፈጸሙ ፍርዶች በመጀመር እስከ የሺህ ዓመቱ ፍጻሜ የሚዘልቅ ረዥም ክፍለ ጊዜ ነው (ኢሳ. 2፡10-22፤ ዘካ. 14)። 

የእግዚአብሔር ቀን የቤተ ክርስቲያን መነጠቅን ተከትሉ ወዲያው የሚመጣ መሆንን የሚያመለክቱ ጥቆማዎች አሉ። ስለሆነም፥ የእግዚአብሔር ቀን ዓበይት ክስተቶች፥ ታላቁን መከራና ከክርስቶስ ዳግም ምጽአት በፊት፥ ብሎም በዳግም ምጽአቱ ወቅት የሚሰጡትን ፍርዶችና ጠቅላላውን የሺህ ዓመት መንግሥት የሚያካትት ይመስላል። 

ብሉይ ኪዳን በተጠናቀቀበት ወቅት ብዙዎቹ ታላላቅ ትንቢቶች እስካልተፈጸሙ፥ የብሉይ ኪዳንን አያሌ ትንቢቶች ፍጻሜና ገና የሚፈጸሙትንም ትንቢቶች የተሟላ ዘገባ ለማቅረብ የአዲስ ኪዳን ተጨማሪ መገለጥ ወሳኝ ነው። የእስራኤል ታሪክ በአብዛኛው በትንቢትም ሆነ በታሪክ ተፈጽሟል። ገና ወደፊት የሚፈጸሙ ታላላቅ ክስተቶችም እሱ። እስራኤል የራሷ ወደሆነው እንደገና የምትመጣበት ጊዜ እንደቀረበ የሚያመለክቱ መረጃዎች ብዙ ናቸው። ይህን በተመለከተ፥ በሚቀጥሉት ምዕራፎች ዝርዝር አሳቦች ቀርበዋል።

ምንጭ፡- “ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ ጭብጦች” መጽሐፍ በዶክተር ሉዊስ ስፔሪ ቼፈር የተጻፈ እና በተክሉ መንገሻ የተተረጎመ ነው፡፡ እግዚአብሔር ስለ እነዚህ ቅዱሳን ድንቅ ስራ የተመሰገነ ይሁን፡፡ ማሳሰቢያ፡- ይህን ጽሁፍ መቀየርም ሆነ ለሽያጭ ማዋል በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡

Leave a Reply

%d bloggers like this: