በዚህ ምዕራፍ፥ ክርስቶስ ከቅዱሳኑ ጋር እና ለቅዱሳኑ መምጣቱን የሚያመለክተው ትምህርት ለአንዳንዶች ግር ይላቸዋል፥ ስለዚህ ልዩነታቸውን ለማጤን ሁለቱን ክንውኖች በጣምራ ማጥናቱ ተጎቢ ይሆናል።
ሀ. ከክርስቶስ ዳግም ምጽአት የሚቀድሙ ዓበይት ሁኔታዎች
ኋላ ከመጨረሻው ዘመን ትንቢት ጋር በተያያዘ መልኩ በምናደርገው ጥናት እንደምናገኘው፥ ቤተ ክርስቲያን መነጠቅና በክርስቶስ መንግሥቱን ለመመሥረት ዳግም መምጣት መካከል ያለው ጊዜ ግልጥ በሆኑ ሦስት ወቅቶች ተከፋፍሏል።
1. ዮዝግጅቱ ወቅት ክቅዱሳን መነጠቅ ቀጥሎ የሚመጣ ሲሆን፥ ያን ጊዜ ስምታንሠራራው ጥንታዊት የሮም መንግሥት ሥር አሥር መንግሥታት በኮንፌዴሬሽን አስተዳደር ይጠቃለላሉ። ከዚህ አስተዳደር ውስጥ መጀመሪያ ሦስቱን፥ ቍጥሉ ደግሞ አሥሩንም መንግሥታት የሚገዛ አምባገነን መሪ ይነሣል።
2. ይህ መሪ ከእስራኤል ጋር በሚያደርገው የሰባት ዓመት ቃል ኪዳን መሠረት በሜዲትራንያን ባሕር አካባቢ የሠላም ጊዜ ይሆናል(ዳን. 9:27)።
3. ቃል ኪዳን ከተደረገ ሦስት ዓመት ተኩል በኋላ እምባገነኑ መሪ ቃሉን ስለሚያፈርስ፥ በእስራኤልና በክርስቶስ በሚያምኑ ሁሉ ሳይ ስደት ይነሣል። ይህ መሪ የዓለም አምባገነን መሪ ይሆናል፥ ስግደት ለርሱ ብቻ እንዲሆን ከመሻቱ የተነሣ የዓለም ሃይማኖቶችን ሁሉ ያጠፋል። ከርሱ ፈቃድ በቀር መገብየት እንዳይኖርና፥ ያለርሱ ፈቃድ መሸጥ ወይም መግዛት እንዳይቻል ለማድረግ በዓለም ያለውን የንግድ እንቅስቃሴ ሁሉ ይቆጣጠራል።
ይህ የሦስት ዓመት ተኩል ጊዜ ታላቁ ፍዳ ይባላል (ዳን. 12፡1፤ ማቴ. 24፡21 ፤ ራእይ 7፡14)። በዚህ ጊዜ የእግዚአብሔር ታላቅ ፍርድ ይወርዳል (ራእይ 6፡1-18፥ 24)። ታላቁ ፍዳ ወደ ታላቅ የዓለም ጦርነት ይሸጋገራል (ራእይ 16፡14-16)። ጦርነቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ በሚደርስበት ጊዜ፥ ክርስቶስ ሰማዕት ያልሆኑ ቅዱሳንን ለመታደግ፥ በምድር ላይ ሊፈርድና የጽድቅ መንግሥቱን ሊመሠርት ይመጣል። ከብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ለመረዳት እንደሚቻለው፥ ይህ ታላቅ፥ የሁከት ሁኔታ ከክርስቶስ ዳግም ምጽአት ይቀድማል። እነዚህ ክንውኖች ሳይፈጸሙ የክርስቶስን ዳግም ምጽአት ይሆናል ብሎ መጠባበቅ አይቻልም።
ለ. ከዳግም ምጽአቱ ጋር የሚዛመዱ ወሳኝ እውነታዎች
1. ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ምድር ቀሚመለስ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ ያስተምራል (ዘካ. 14፡4)፤ በእካል (ማቴ. 25፡31፤ ራእይ 19፡11-16)፤ በደመና እንደሚመለስ (ማቴ. 24፡30፤ ሐዋ. 1፡11፤ ራእይ 1፡7)። ስለዚህ የሚናገሩ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ሁሉ እንደሚገልጡት ይህ ሁኔታ ዓለም ሁሉ የሚያየውና የከበረ ዕለት ነው (ራእይ 1፡7)።
2. በኢየሱስ ክርስቶስ በራሱ እንደተገለጠውና ማቴዎስ 24፡26-29 ውስጥ እንደተመዘገበው፥ የርሱ መገለጥ የመብረቅ ብርሃን ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ እንደሚታይ ይሆናል። ክርስቶስ ከመምጣቱ በፊት ከዚያች ወራትም መከራ በመባል በሚታወቁት ጊዜያት፥ በሰማይ ሁከት ይሆናል፥ ፀሐይ ትጨልማለች፥ ጨረቃ ብርሃን አትሰጥም፥ ከዋክብት ከሰማያት ይወድቃሉ፥ ሰማያት ራሳቸው ይናወጣሉ። ራእይ 6፡12-17፤ 16፡1-21 ውስጥ ሁኔታው በበለጠ ዝርዝር ተብራርቷል። የክርስቶስ ዳግም ምጽአት በምድር በሚኖሩ ሁሉ የሚታይ ይሆናል (ማቴ. 24፡30፤ ራእይ 1፡7)። “የምድር ወገኖች ሁሉ ዋይ ዋይ ይላሉ፡” (ማቴ. 24፡30)። ምክንያቱም ብዙዎቹ ፍርድ የሚጠብቃቸው በዚህ ጌታ ያላመኑ ሕዝብ ናቸው።
3. ክርስቶስ በዳግም ምጽአቱ ወቅት በቅዱሳንና በመላእክት በድምቀት ይታጀባል። ሁኔታው ራእይ 19፡11-16 ውስጥ በዝርዝር ተገልጧል። ዮሐንስ እንዲህ ነው የጻፈው:- “
ሰማይም ተከፍቶ አየሁ፤ እነሆም አምባላይ ፈረስ፥ የተቀመጠበትም የታመነና እውነተኛ ይባላል፤ በጽድቅም ይፈርዳል፤ ይዋጋልም። ዓይኖቹም እንደ እሳት ነበልባል ናቸው፤ በራሱ ላይም ብዙ ዘውዶች አሉ፤ ከእርሱ በስተቀር አንድ እንኳ የማያውቀው የተጻፈ ስም አለው፤ በደምም የተረጨ ልብስ ተጎናጽፏል፤ ስሙም የእግዚአብሔር ቃል ተብሏል። በሰማይም ያሉ ጭፍሮች ነጭና ጥሩ ቀጭን የተልባ እግር ልብስ ለብሰው በአምባላዮች ፈረሶች ተቀምጠው ይከተሉት ነበር። አሕዛብንም ይመታበት ዘንድ ስለታም ሠይፍ ከአፉ ይወጣል፤ እርሱም ሰብረት በትር ይገዛቸዋል፤ እርሱም ሁሉን የሚገዛ የእግዚአብሔር የብርቱ ቁጣውን ወይን መጥመቂያ ይረግጣል። በልብሱና በጭኑም የተጻፈበት የነገሥታት ንጉሥና የጌቶች ጌታ የሚል ስም አለው”።
የክርስቶስ በቅዱሳን ሁሉና በመላእክት የታጀበ መሆኑ፥ ሂደቱን ዝግ ያለና ብዙ ሰዓት የሚወስድ መሆኑን ያመለክታል። በዚህ ጊዜ ዓለም ሁሉ ክንውኑን ያይ ዘንድ መሬት ትሽከረከራለች። የዳግም ምጽአቱ ክንውን ክርስቶስ ወደ ሰማይ በዐረገበት በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ያበቃል (ዘካ. 14፡1-4፤ ሐዋ. 1፡9-12)። በዚያን ጊዜ የክርስቶስ እግሮች ደብረ ዘይት ተራራ ላይ ያርፋሉ፤ ተራራውም ሁለት ላይ ደካፈልና ከኢየሩሳሌም ወደ ምሥራቅ እስከ ዮርዳኖስ የሚዘልቅ ሸለቆ ይፈጠራል።
4. ክርስቶስ በሚመጣበት ጊዜ በመጀመሪያ በጦርነቱ የተሳተፈውን የዓለም ጦር ሥራት ይቀጣል (ራእይ 19፡15-21)። መንግሥቱንም እንደመሠረተ እስራኤልን ሰብስቦ ወደ ሺህ ዓመቱ መንግሥት ለመግባት ካላቸው ብቃት አንጻር ይፈርድባቸዋል (ሕዝ. 20፡34-38)። በተመሳሳይ ሁኔታ ‘አሕዛብን” ሰብስቦ ይፈርድባቸዋል (ማቴ. 25፡31-46)። ከዚህ ሁሉ በኋላ የጽድቅና የሰላም መንግሥቱን ምድር ላይ ይመሠርታል። ሰይጣን ይታሰርና ግልጥ የሆኑ ዓመፃዎች ሁሉ ፍርዳቸውን ያገኛሉ። ይህን አሳብ በሚቀጥሉት ምዕራፎች ላይ በስፋት እንመለከታለን።
ሐ. ዳግም ምጽአቱ ከመነጠቅ ጋር ሲነጻጸር
ባለፈው ምዕራፍ እንደታየው በክርስቶስ ለቅዱሳኑ መምጣትና፥ በቅዱሳኑ ታጅቦ መምጣት መካከል ብዙ ማነጻጸሪያዎች አሉ። ሁለቱን ክንውኖች፥ ማለት የክርስቶስን ለቅዱሳኑ መምጣትና ከቅዱሳኑ ጋር መምጣትን በዚህ አኳኋን ለመለየት ይቻል ይሆናል። ልዩነታቸውን በደንብ ለመገንዘብ የክርስቶስን ለቅዱሳኑ መምጣትና ከቅዱሳን ጋር መመለሱን በተመለከተ ከዚህ በታች ያለውን ሠንጠረዥ ይመልከቱ።
ለቅዱሳን መምጣቱ
(1) “በአንድነት ወደ እርሱ መሰብሰባችን”።
(2) እንደ ንጋት ኮከብ” ይመጣል (ራእይ 2፡28፤ 22 ፡16፤ 2ኛ ጴጥ. 1፡19)፡፡
(3) “የክርስቶስ ቀን” (1ኛ ቆሮ. 1፡8፤ 2ኛ ቆሮ. 1፡14፤ ፊልጵ. 1፡6፤ 10፤ 2፡16)፡፡
(4) ያላ ምልክት እንደ ሌባ በድንገት የሚመጣ ቀን ነው።
(5) ድንገተኛ፥ በማንኛውም ጊዜ ሊሆን የሚችል፡፡
(6) ስለ ኃጢአት አልተጠቀሰም፡፡
(7) እስራኤል አትለወጥም፡፡
(8) ቤተ ክርስቲያን ከምድር ትወሰዳለች፡፡
(9) መንግሥታት አይለወጡም
(10) ፍጥረት አይለወጥም፡፡
(11) አስቀድሞ ያልተገለጠ “ምስጢር”፡፡
(12) ተስፋ ክርስቶስ ላይ ብቻ ይሆናል “ጌታ በደጅ ነው” (ፊልጵ 4፡5)፡፡
(13) ክርስቶስ እንደሙሽራ፣ እንደጌታ እና የቤተ ክርስቲያን ራስ ይገለጣል (ኤፌ 5፡25-27፤ ቲቶ 2፡13)፡፡
(14) አመጣጡን አለም አያየውም
(15) ክርስቲያኖች ሊሸለሙ ካለው ነገር አንጻር ለብያኔ ይቀርባሉ፡፡
ከቅዱሳን ጋር መምጣቱ
(1) “የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መምጣት” (2ኛ 1 ተሰ. 2፡1)።
(2) እንደ “ጽድቅ ፀሐይ” (ሚል. 4፡2)።
3) “የጌታ ቀን” (2ኛ ጴጥ. 3፡10)።
(4) መቃረቡ ይታያል (1ኛ ተሰ. 5፡4፤ ዕብ. 10፡25)።
(5) ስለ ቀኑ የተነገረው ትንቢት አስቀድሞ ይፈጸማል (2ኛ ተሰ 22፡23)፡፡
(6) ኃጢአት ይጠፋል፥ ሰይጣን ይፈረድበታል፥ የኃጢአት ሰው ይደመሰሳል (2ኛ ተሰ. 2፡8፤ ራእይ 19፡20፤ 20፡1-4)። ሊሆን የሚችል።
(7) ቃል ኪዳኗ ሁሉ ይፈጸማል (ኤር. 23፡5 -8፤ 30፡3-11፤ 31፡27-37)።
(8) ከክርስቶስ ጋር ትመለሳለች (1ኛ ተሰ. 4፡17፤ ይሁዳ 14-15፤ ራእይ 19፡14)።
(9) መንግሥታት ይፈርድባቸዋል (ማቴ. 25፡31-46)።
(10) ፍጥረት ከክፉ እሥራት ነጻ ይወጣል (ኢሳ. 35፤ 65፡17-25)።
(11) በብሉይና በአዲስ ኪዳን በአጠቃላይ ታይቷል (ዳን. 7፡13-14፤ ማቴ. 24፡27-30፤ 1ኛ ቆሮ. 15፡51-52)።
12) መንግሥቱ ትመጣለች (ማቴ. 6፡10)።
(13) ክርስቶስ እንደ ንጉሥ፥ መሢሕ እና የእስራኤል መድኅን ይገለጣል (ኢሳ. 7፡14፤ 9፡6-7፤ 11፡1-2)፡፡
(14) በታላቅ ሥልጣንና ክብር ይመጣል (ማቴ. 24፡27፥ 30፤ ራእይ 1፡7)።
(15) ነገሥታት ለርሱ ከሰጡት ምላሽ አንጻር ይበየንባቸዋል (2ኛ ቆሮ. 5፡10-11፤ ማቴ. 25፡31-46)።
ጠቃሚ ጥቅሶች
ዮሐ. 14፡1-3፤ 1ኛ ቆሮ. 15፡51-52፤ 1ኛ ተሰ. 4፡13-18፤ ፊሊጵ 3፡20-21፤ 2ቆሮ 5፡10፤
ዘዳ. 30፡1-10፤ መዝ. 72፤ የነቢያትን ትንቢቶች በሙሉ ያስተውሉ (ማቴ. 25፡1-46፤ ሐዋ. 1፡11፤ 115፡13-18፤ 2ኛ ተሰ 22፡112፤ 2ኛ ጴጥ. 2፡1-3፡8፤ ራእይ. 19፡11-20፡6)።
ምንጭ፡- “ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ ጭብጦች” መጽሐፍ በዶክተር ሉዊስ ስፔሪ ቼፈር የተጻፈ እና በተክሉ መንገሻ የተተረጎመ ነው፡፡ እግዚአብሔር ስለ እነዚህ ቅዱሳን ድንቅ ስራ የተመሰገነ ይሁን፡፡ ማሳሰቢያ፡- ይህን ጽሁፍ መቀየርም ሆነ ለሽያጭ ማዋል በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡