Site icon

የሺህ ዓመቱ መንግሥት

ህ. የእግዚአብሔር መንግሥት ፅንሰ-ሃሳብ 

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የእግዚአብሔር መንግሥት ሲባል በአጠቃላይ እግዚአብሔር ዓለማትን የሚገዛ መሆኑን ያመለክታል። እግዚአብሔር ሁልጊዚ ሉዓሳዊና ሁሉን ቻይ ሆኖ ስለሚኖር መንግሥቱም ዘላለማዊ መሆኑ ይታመናል። ሰእግዚአብሔር ብርታት ዝቅ የተደረገው የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ለዚህ አባባል እንዲህ በማለት ምስክርነቱን ይሰጣል፡- «ዘመኑም ከተፈጸመ በኋላ እኔ ናቡከደናዖር ዓይኔን ወደ ሰማይ አሣሁ፥ አእምሮዬም ተመለሰልኝ፤ ልዑሉንም ባረክሁ፥ ስቶሳሰም የሚኖረውን አመሰገንሁ አከበርሁትም፤ ግዛቱ የዘላለም ግዛት ነውና። ምድርም የምኖሩ ሁሉ እንደ ምናምን ይቆጠራሉ፤ በሰማይም ሠራዊት በምድርም ላይ ሰሚኖሩ መካከል እንደ ፈቃዱ ያደርጋል፤ እጁንም የሚከለክላት ወይም ምን ታደርጋለህ የሚለው የለም” (ዳን. 4፡34-35)። 

ከዘመናት በፊት ሰይጣንና እርሱን የደገፉ የመላእክት ጭፍሮች የእግዚአብሔርን የዓለማት ገዢነት ተቃውመው ነበር። እግዚአብሔር ዓመፀኞቹን በመቅጣት ሉዓላዊነቱን አሳይቷል። የኃጢአት ወደ ዓለም መቀባትም በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ የእግዚአብሔርን ሉዓላዊነት እስገንዝቧል። ይህ የሚያመለክተው፥ የመለኮታዊ መንግሥትን ፅንሰ-አሳብን ነው። በሌላ አባባል እግዚአብሔር ምንም እንኳን ዛሬ በፍጥረታቱ አማካይነት ቢሠራ፥ ብቸኛና ታላቅ ገዢ ግን እርሱ ነው። 

አዳም ሲፈጠር ምድርን እንዲገዛ ተፈቅዶለት ነበር (ዘፍጥ. 1፡26፥ 28)። ይሁንና፥ አዳምና ሔዋን ለእግዚአብሔር ባለመታዘዝ የተከለከለውን የዛፍ ፍሬ በሉ። አዳም በኃጢአት በመው፪ቁ የመግዛት መብቱን አጣ። ከዚህም የተነሣ እግዚአብሔር በሉዓላዊነቱ የተወሰኑ ሰዎችን ብቻ መርጦ የአገዛዝ ኃላፊነት ሰጣቸው። በዚሁ መሠረት አንዳንድ ሰዎች ገዥነት የተፈቀደላቸው መሆኑን ከታሪክ እንረዳለን። ለምሳሌ፥ ዳንኤል እግዚአብሔር ናቡከደነፆርን የቀጣው መሆኑን ሲገልጥ፥ “ልዑል አምላክም በሰዎች መንግሥት ላይ እንዲሠለጥን፥ የሚወደውንም እንደሚሾምበት እስኪያውቅ ድረስ” ብሏል (ዳን. 5፡21)። 

በብሉይ ኪዳን፥ መለኮታዊ አገዛዝ ያለበት መንግሥት በዓቢይነት የታየው በሳኦል፥ በዳዊትና በሰሎሞን በተጀመረው የእስራኤል መንግሥት ጊዜ ነበር። የአሕዛብ መሪዎችም በሉዓላዊው የእግዚአብሔር ዓላማ ውስጥ የፖለቲካ አገዛዝ ክልል እንዲይዙ ተፈቅዶላቸው ነበር። የዚህ በእግዚአብሔር ፈቃድ የሚካሄድና የሚመራ አጠቃላይ የመንግሥት ፅንሰ-አሳብ ሮሜ 13፡1 ውስጥ በሐዋርያው ጳውሎስ እንዲህ ተገልጧል፡- ነፍስ ሁሉ በበላይ ላሉት ባለሥልጣኖች ይገዛ። ከእግዚአብሔር ካልተገኘ በቀር ሥልጣን የለምና፤ ያሉትም ባለሥልጣኖች በእግዚአብሔር የተሾሙ ናቸው።›› 

መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ሉዓላዊነት በፖለቲካዊ መንግሥታትና በአዛዛቸው ላይ የሚገለጥ መሆኑን ከማስገንዘቡም ሌላ፥ እግዚአብሔር በሰዎች ልብ አማካይነት ስለሚዛው መንፈሳዊ መንግሥትም ምስክርነቱን ይሰጣል። ይህ ከሰው ዘር ጅማሬ አንሥቶ ሲከናወን የቆየ ነው። መንፈሳዊው መንግሥት በገዛ ፈቃዳቸው ራሳቸውን ለእግዚአብሔር ያስገዙ ሰዎችንም ሆነ መላእክትን ያካትታል። ጳውሎስ ሮሜ 14፡17 ውስጥ ሰለዚሁ መንፈሳዊ መንግሥት የሚከተሰውን በመግለጥ ጽፏል፡- “የእግዚአብሔር መንግሥት ጽድቅና ሠላም ሰመንፈስ ቅዱስም የሆነ ደስታ ናት እንጂ፥ መብልና መጠጥ እይደለችምና።” 

ማቴዎስ ወንጌል ውስጥ፥ የሰማይ መንግሥት» እና «“የእግዚአብሔር መንግሥት”፥ የሚሉ ሐረጎችን በመጠቀም ረገድ ተጨማሪ ልዩነት ተ፪ርጓል። ሌሎቹ ወንጌላት “የእግዚአብሔር መንግሥት” የሚሏቸውን ማቴዎስ በተደጋጋሚ የሰማይ መንግሥት” ስለሚል፥ ብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ተርጓሚዎች ሁለቱም የሚያስተላልፉት ተመሳሳይ መልእክት ነው ብለው ያስባሉ። ሐረጎቹ በጣም የሚመሳሰሉ ቢሆኑም፥ ያጠቃቀማቸው ሁኔታ ሲታይ የሰማይ መንግሥት ከእግዚአብሔር መንግሥት የሚሰፋ ይመስላል። ይሄውም በስንዴና በእንክርዳዱ ምሳሌ ውስጥ መንግሥተ ሰማይ እንክርዳድን፥ የመረቡ ምሳሌ ደግሞ መንግሥተ ሰማይ መልካምና ክፉ ዓሣዎችን ያካተተ ይመስላል (ማቴ. 13፡24-30፥ 36-43፥ 47-50)። 

በሌላ በኩል፥ የእግዚአብሔር መንግሥት ዳግም በመወለድ የሚገቡባት እንጂ በተለምዶ የጌታ ነኝ የሚሉ ሰዎች ስብስብ አይደለችም። ይህም ክርስቶስ ለኒቆዲሞስ በተናገረው እሳብ እንዲህ ተብራርቷል፡- “እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም” ዮሐ. 3፡5)። ይሁን እንጂ፥ አብዛኛዎቹ የመጽሐፍ ቅዱስ ተንታኞች በሁለቱ መንግሥታት መካከል ምንም መሠረታዊ ልዩነት የለም የሚለውን አመለካከት ይመርጣሉ። 

ሆኖም በአሁኑና በሺህ ዓመቱ መንግሥት መካከል ንጽጽር ሲደረግ የጎሳ ልዩነት አለ። የአሁኑ መንግሥት “ምሥጢራት” የተሰኙ ዓበይት ገጽታዎች አሉት፤ “ምስጢራቱ” ሰብሉይ ኪዳን ዘመን ያልተሰጡ መንስጦች ናቸው (ማቴ. 13)። ዳሩ ግን ምሥጢራዊ ያልሆነ መንግሥት ከከርስቶስ ዳግም ምጽአት በኋላ ይመሠረታል። 

በማይታይና በሚታየው መንግሥት መካከል ልዩነትም አለ። የማይታየው መንግሥት በአሁኑ ዘመን እግዚአብሔር በአማኞች ልብ ውስጥ የሚያካሂደው አገዛዝ ሲሆን፥ የሚታየው መንግሥት ከዳግም ምጽአት በኋላ ሰዎች ሁሉ በምድር ላይ የሚመለከቱት የከበረ መንግሥት ነው። የአሁኑን ዘመን መለኮታዊ አገዛዝ ክልል በሺህ ዓመቱ መንግሥት ጊዜ ከሚሆነው ጋር ለማነጻጸር፥ ይህ ልዩነት በጣም አስፈላጊና ወሳኝ ነው። 

የመንግሥትን ፅንሰ-ሃሳብ ከሺህ ዓመቱ መንግሥት ጋር ለማዛመድ በተደረገው ጥረት ሦስት ዓይነት አመለካከቶች ቀርበዋል። የቅድመ ሺህ ዓመታውያን (premillenialism/ ፕሪሚሊኒያሊዝም) አመለካከት፥ መጽሐፍ ቅዱስ የሚያስተምረው፥ መጀመሪያ የክርስቶስ ዳግም ምጽአት እንደሚፈጸምና በኋሳ የሺህ ዓመቱ መንግሥት በምድር ላይ የሚመሠረት መሆኑን ነው፤ ከሺህ ዓመቱ መንግሥት በኋላ ዘላለማዊው አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር ይለጥቃል ይላል። ይህ አመለካከት ቅድመ ሺህ ዓመታዊ የተባለው የክርስቶስ ዳግም ምጽአት ከሺህ ዓመቱ መንግሥት የሚቀድም መሆኑን ስለሚያስተምር ነው። 

ሁለተኛው አመለካከት፥ በምድር ላይ የሺህ ዓመት መንግሥት አይመሠረትም የሚለውና እልሶሺህ ዓመታዊ (amillenialism/ኢሚሊኒያሊዝምን የተሰኘው ነው። ይህ አመለካከት ክርስቶስ ዳግም ሲመለስ ያለ ምንም የሺህ ዓመት መንግሥት ጣልቃ ገብነት አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር የሚመሠረት መሆኑን ያስተምራል። አመለካከቱ ብሉይም ሆነ አዲስ ኪዳን ስለ ሺህ ዓመቱ መንግሥት የሚናገሩትን ምንባቦች ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ በመተርጎም የዚህ መንግሥት ዘመን በቤተ ክርስቲያን አማካይነት በአሁኑ ጊዜ በምድር ወይም በሰማይ በመከናወን ላይ ነው ይላል። 

ሦስተኛው የድህረ-ሺህ ዓመታዊነት (postmillenialism/ፖስትሚሊኒያሊዝም) አመለካከት ነው። ይህ አመለካከት በአሁኑ ጊዜ ወንጌል ዓለምን ሁሉ አሽንፎ ወርቃማ ዘመን የሚያመጣ መሆኑንና ለሺህ ዓመቱ መንግሥት የተተነበየው ሠላምና ጽድቅ በተወሰነ ደረጃ ተፈጻሚ እንደሚሆን ያምናል። አመለካከቱ ይህ ስያሜ የተሰጠው፥ የክርስቶስን ዳግም ምጽአት የወርቃማው ዘመን ጫፍ ወይም የሺህ ዓመቱ መንግሥት ፍጻሜ አድርጎ ስለሚመለከት ነው። አክራሪ የሆኑ የድህረ-ሺህ ዓመታዊ መንግሥት አመለካከት ተከታዮች ክርስቶስ ለሺህ ዓመታት በሰዎች ልብ ውስጥ የሚገዛ መሆኑን ያስተምራሉ። ወደ ለዘብተኛነት የሚያዘመው ድህረ-ሺህ ዓመታዊ አመለካከት ደግሞ፥ ከዘገምተኛ ለውጥ ሂደት አመለካከት ጋር የሚመሳሰል ሲሆን፥ ዓለም ቀስ በቀስ እየተሻሻለች እንደምትሄድና በመጨረሻ ወደ ወርቃማው ዘመን ለመድረስ እንደሚቻል ያምናል። የህያኛው ክፍለ-ዘመን ታሪክ አካሄድ የእግዚአብሔር ዓላማ በሰዎች አማካይነት ውብ እየሆነ በዓለም ያከናወናል የሚለው እምነት ከሚሰጠው መረጃ ደካማነት የተነሣ ተቀባይነት የሌለው ሆኗል። በመሆኑም በአሁኑ ዘመን እብዛኞቹ የመጽሐፍ ቅዱስ ተንታኞች አንድም የሺህ ዓመታት ዘመን እንደሌለ ወይም ክርስቶስ ከሺህ ዓመት በፊት እንደሚመጣ የሚያምኑ ብቻ ናቸው። 

የሺህ ዓመቱ መንግሥት በትክክል በምድር ላይ የሚመሠረት መሆኑን በመደገፍና በመቃወም የሚነሡ በርካታ ሙግቶች ቢኖሩም፥ መፍትሔው የሚገኘው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትንቢቶች በቀጥታ በሚፈቱበት መንገድ ነው። በዚህ ውይይታችን፥ ትንቢት እንደማንኛውም መለኮታዊ መገለጥ በቀጥታ መተርጎም የሚኖርበት መሆኑን እንመለከታለን። በመሆኑም፥ ብዙ የብሉይ ኪዳን ትንቢቶችና አዲስ ኪዳን ውስጥ የራእይ ምዕራፍ ሀያ ዋነኛ እሳብ በቀጥታ የሚናገሩትን መልእክት እንዲያስተላልፉ ሆነው ተተርጉመዋል። በዚሁ መሠረት ከክርስቶስ ጳግም ምጽአት በኋላና፥ አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር ከመፈጠራቸው በፊት የክርስቶስ የሺህ ዓመት መንግሥት ምድር ላይ የሚመሠረት መሆኑን ትንቢቶቹ ያስረዳሉ። 

ለ. የሺህ ዓመቱ መንግሥት፥ የእግዚአብሔር አገዛዝ ሰምድር ላይ 

የእግዚአብሔር መንግሥት በቀዳሚነት በሰዎች ልብ ውስጥ የሚፈጸም መንፈሳዊ አገዛዝ መሆኑን ከሚናገረው እልቦ.ሺህ ዓመታውያን አመለካከት ባሻገር፥ በምድር ላይ ክርስቶስ የሚገዛበት መንግሥት እንደሚመሠረት የሚያመለክተውን ድምዳሜ የሚደግፉ አያሌ የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባቦች አሉ። ክርስቶስ በዚሁ ምድራዊ መንግሥት ላይ ዋነኛው ፖለቲካዊና መንፈሳዊ መሪ ከመሆኑም በላይ፥ አምልኮ የሚቀርብለት ንጉሥም ነው። ይህ ፅንሰ-አሳብ በብሉይም ሆነ በአዲስ ኪዳን ውስጥ በሚገባ ዳብሮ ቀርቧል። 

ሕዝቦች በእግዚአብሔር ላይ ማመፃቸው በተመዘገበበት መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ሁለት ውስጥ፥ ለእግዚአብሔር ልጅ፥ “ለምነኝ አሕዛብን ላርስትህ የምድርንም ዳርቻ ለግዛትህ እሰጥሃለሁ” የሚል ቃል ተገብቶለታል (ቁ. 8)። ይህ መንፈሳዊ አገዛዝ ሳይሆን፥ ፖለቲካዊ መሆኑ በቀጣዩ ቁጥር ውስጥ እንዲህ ተመልክቷል፡- “በብረት በትር ትጠብቃቸዋለህ፥ እንደ ሸከላ ሠሪ ዕቃም ትቀጠቅጣቸዋለህ” (ቁ. 9)። ይህ የሚያመለክተው፥ ቤተ ከርስቲያንን ወይም በሰማይ የሚሆነውን መንፈሳዊ አገዛዝ ሳይሆን ኃጢአተኞችን ወደ ታች ዝቅ አድርጎ የሚገዛ ፍጹማዊ ንጉሥን ነው። 

የመንግሥቱን ምድራዊ ባሕርይ የሚያጎላው ሌላ ምንባብ ኢሳይያስ ምዕራፍ 11 ውስጥ ያለው ነው። በዚህ ስፍራ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ዳዊት ዘር በምድር ላይ በጽድቅ እንደሚፈርድና ክፉዎችን እንደሚቀጣ ተገልጧል። ኢሳይያስ 11፡4፥ ነገር ግን ለድሆች በጽድቅ ይፈርዳል፥ በምድርም የዋሆች በቅንነት ይበይናል፤ በአፉም በትር ምድርን ይመታል፥ በከንፈሩም እስትንፋስ ክፉዎችን ይገድላል” ይላል። እንደ ኢሳይያስ 11፡9 በመሳሰሉት ምንባቦች “ምድር” የሚለው ቃል በተደጋጋሚ ከመጠቀሱም በላይ፣ እግዚአብሔር እስራኤልን ከምድር ሁሉ ለመሰብሰብ በአገሮች ላይ የሚያከናውናቸው ተግባራትም ተገልጠዋል። 

በርከት ያሉ ሌሎች ምንባቦችም መንግሥቱ በምድር ላይ እንደሚሆን ይገልጣሉ ወይም ይጠቁማሉ (ኢሳ. 42፡4፤ ኤር. 23፡3-6፤ ዳን. 2፡35-45፤ ዘካ. 14፡1-9)። በሺህ ዓመቱ ዘመን ክርስቶስ በምድር ላይ እንደሚነግሥ በነዚህ ምንባቦች መገለጡ፥ የአሁኑን ዘመን ወይም መንግሥተ ሰማይን አያመለክትም። ስለሆነም የትኛውም ተገቢ አፈጻጸም የክርስቶስን ዳግም ምጽእት ተከትሎ በምድር ላይ ክርስቶስ የሚገዛበትን ምድራዊ መንግሥት መመሥረትን ይጠይቃል። 

ሐ. በሺህ ዓመቱ መንግሥት ክርስቶስ እንደ ንጉሠ ነገሥት 

ብዙ የብሉይና አዲስ ኪዳን ምንባቦች ክርስቶስ በምድር ላይ የበላይ ገዥ እንደሚሆን ይመሰክራሉ። ክርስቶስ እንደ ዳዊት ልጅነቱ በዳዊት ዙፋን ላይ ይቀመጣል (2ኛ ሳሙ. 7፡16፤ መዝ. 89፡20-37፤ ኢሳ, 11፤ ኤር. 33፡19-21)። ክርስቶስ ሲወለድ መልአኩ ገብርኤል ለማርያም እንደነገራት እንደ ንጉሥ ነበር የመጣው (ሉቃስ 1፡32-33)። እንደ ንጉሥ ተቀባይነትን አጥቷል (ማር. 15፡12-13፤ ሉቃስ 19፡14)። በመስቀል ላይ በተሰቀለ ጊዜ (የአይሁድ ንጉሥ” ተብሉ ነበር የሞተው (ማቴ. 27፡37)። በዳግም ምጽአቱ እንደ “ነገሥታት ንጉሥና የጌቶች ጌታ” እንደሚሆን ተገልጧል (ራእይ 19፡16)። ብሉይ ኪዳን ውስጥ በመቶዎች የሚቆጠሩ ጥቅሶች ክርስቶስ በምድር ላይ እንደሚነግሥ ይገልጣሉ ወይም ይጠቁማሉ። ከነዚህም መካከል አንዳንዶቹ ዋነኛ ጥቅሶች በጣም ግልጥ ናቸው (ኢሳ. 2፡1-4፤ 9፡6-7፤ 11፡1-10፤ 16፡5፤ 24 ፡23፤ 32፡1፤ 40፡1-11፤ 42፡1-4፤ 52፡7-15፤ 55፡4፤ ዳኝ. 2፡44፤ 1፡27፤ ሚክ. 4፡1-8፤ 5፡2-5፤ ዘካ. 9፡9፤ 14፡16-17)። 

ከሺህ ዓመቱ መንግሥት ገጽታዎች አንዱ፥ ዳዊት ከሞት ተነሥቶ በክርስቶስ ሥር እኝደ መስፍን የሚሠራ መሆኑ ነው (ኤር. 30፡9፣ 33፡15-17፤ ሕዝ. 34፡23-24፤ 37፡24-25፤ ሆሴዕ 3፡5)። ይህ ሁኔታ ዛሬ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሌለ በመሆኑ፥ ትንቢቱ ከመፈጸሙ በፊት የክርስቶስን ዳግም ምጽአትና የብሉይ ኪዳን ቅዱሳን ትንሣኤን ይጠይቃል። 

መ. የሺህ ዓመቱ መንግሥት ዓበይት ገጽታዎች 

በምድር ላይ ስለሚሆነው የክርስቶስ የሺህ ዓመት መንግሥት ምድራዊ አገዛዝ መጽሐፍ ቅዱስ ቢያንስ ሦስት ጠቃሚ ገጽታዎችን ያቀርባል። 

1. የክርስቶስ አገዛዝ ምድርን ሁሉ እንደሚያካትት ብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ይመሰክራሉ። ይህም ከማንኛውም ቀደምት ምድራዊ መንግሥት ወይም ከራሱ ከዳዊት የግዛት ወሰን የላቀ ነው። ይህን ዓለም አቀፍ መንግሥት በመመሥረት ነው፥ እግዚአብሔር ሰው ምድርን እንዲገዛት የወጠነውን ዓላማ ከግቡ የሚያደርሰው። ምንም እንኳ አዳም ይህን ዓላማ ለማሳካት ባይችል፥ መዝሙረ ዳዊት 2፡6-9 ውስጥ እንደተመለከተው ሁለተኛው አዳም የሆነው ክርስቶዕ ብቁ ሆኖ ተገኝቷል። ዳንኤል 7: 14 ውስጥ ያለው ቃል እንደሚለው ልጁ፥ “ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩ ቋንቋም የሚናገሩ ሁሉ ይገዙለት ዘንድ ግዛትና ክብር መንግሥትም ተሰጠው፤ ግዛቱም የማያልፍ የዘላለም ግዛት ነው፥ መንግሥቱም የማይጠፋ ነው።” ዳንኤል 2፡44፤ 4፡34፤ 7፡27 ውስጥ ተመሳሳይ አሳብ ተጠቅሷል። የክርስቶስ እገዛዝ ዓለም አቀፋዊነት መዝሙር 72፡8፤ ሚክያስ 4፡1-2፤ ዘካርያስ 9፡10 ውስጥ ተገልጧል። 

2. የክርስቶስ መንግሥት ፍጹም ሥልጣንና ኃይል ያለው ይለናል። ክርስቶስ በብረት በትር ይገዛል (መዝ. 2፡9፤ ራእይ 19፡15)። የሚቃወሙት ሁሉ ይጠፋሉ (መዝ. 2፡9፤ 72፡9-11፤ ኢሳ. 11፡4)። እንዲህ ዓይነቱ ፍጹማዊ አገዛዝ አሁን ክርስቶስ በቤተ ክርስቲያንም ሆነ በዓለም ላይ ያለውን ሥልጣን አያመለክትም። ተፈጻሚነት የሚኖረው ከዳግም ምጽአቱ በኋላ በምድር ላይ ከነገሠ ብቻ ነው። 

3. በሺህ ዓመቱ መንግሥት ወቅት የክርስቶስ አገዝ የጽድቅና የሠላም ይሆናል። እንደ ኢሳይያስ ምዕራፍ 11 እና መዝሙር 72 በመሳሰሉት እስፈላጊ የመጽሐፍ ቅዱስ ኮፍሎች ውስጥ ይህ ተመልክቷል። 

እነዚህ ያልተለመዱ የመንግሥት ባሕርያት ሊከሠቱ የሚችሉት በእስራኤልና በአሕዛብ ላይ ፍርድ በመውረዱ (ባለፈው ምዕራፍ እንደተነጋገርነው)፥ እና ሰይጣን ተግባሩን እንዳያከናውን ሰመታሰሩ ነው። የሚቀረው ብቸኛ የክፋት ምንጭ በሰዎች ልብ የሚገኘው ኃጢአታዊ ተፈጥሮ ብቻ ያያናል። ስንዴው ከእንክርዳዱ (ማቴ. 13፡24-30)፥ ጥሩዎቹ ዓሣዎች ከመጥፎዎቹ መለየታቸው (ማቴ. 13፡47-50ን፥ የክርስቶስ መንግሥት ጅማሬ ዝግጅቶች ናቸው። የሺህ ዓመቱ መንግሥት በሚጀመርበት ጊዜ፥ ጎልማሶች ሁሉ እውነተኛ አማኞች ይሆናሉ። በሺህ ዓመቱ ጊዜ የሚወለዱ ልጆች ለክርስቶስ የጽድቅ መንግሥት የሚገዙ ሲሆን፥ በንጉሡ ላይ ቢያምፁ ግን እስከሞት ድረስ ይቀጣሉ (ኢሳ. 65፡17-20፤ ዘካ. 14፡16-19)። ግልጥ ኃጢአት የሚቀጣ ሲሆን፥ በሺህ ዓመቱ አገዛዝ ውሰጥ ማንም ኃጢእት እንዲሠራ እይፈቀድላትም። 

ሠ. በሺህ ዓመቱ መንግሥት የእስራኤል ልዩ ስፍራ 

በሺህ ዓመቱ መንግሥት ወቅት፥ እስራኤል መልካም ዕድልና ልዩ የበረከት ጊዜ ያጋጥማታል። አይሁዶችና እሕዛብ በተመሳሳይ ስፍራ ሆነው ተመሳሳይ ዕድል ከሚጋሩበት ከእሁኑ የቤተ ክርስቲያን ዘመን ባሻገር፥ ሰሺህ ዓመቱ መንግሥት ወቅት የእስራኤል ሕዝቦች የተስፋይቱን አገር በመውረስ የእግዚአብሔር ልዩ በረከት ተጠቃሚዎች ይሆናሉ። የሺህ ዓመቱ መንግሥት የእስራኤል ሕዝብ ዳግም የሚሰባሰብበት፥ እንደ አገር የሚታነጽበትና የዳዊትን መንግሥት የሚያድስበት ወቅት ነው። በመጨረሻም እስራኤል ምድሪቱን ሙሉ በሙሉ ትወርሳለች። 

በርካታ የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባቦች ስለዚሁ ጉዳይ ይናገራሉ። በሺህ ዓመቱ ጊዜ እስራኤላውያን ወደ ቀድሞ ምድራቸው ዳግም የመሰባሰብና የመታደስ ዕድል ይኖራቸዋል (ኤር. 30፡3፤ 31፡8-9፤ ሕዝ. 39፡25-29፤ አሞፅ 9፡11-15)። እስራኤላውያን ዳግም ወደ ምድራቸው በመመለስ፥ የታደሰውን የዳዊትን መንግሥት ይመሠርታሉ (ኢሳ. 9፡6-7፣ 33፡17፥ 22፤ 44፡6፤ ኤር. 23፡5፤ ዳኝ. 4፡3፤ 7፡14፥ 22፥ 27፤ ሚክ. 4፡2-3፥7)። የተከፈለው የእስራኤልና የይሁዳ መንግሥት እንደገና ይዋሐዳል (ኤር. 3፡18፤ 33፡143 ሕዝ. 20፡40፤ 37፡15-22፤ 39:25፤ ሆሴዕ 1፡11)። እስራኤል እንደ ያህዌ ሚስት (ኢሳ. 54፤ 62፡2-5፤ ሆሴዕ 2፡14-23) ከአሕዛብ አማኞች በላቀ የበረከት ስፍራ ትቀመጣለች (ኢሳ. 14 ፡1-2፤ 49፡22-23፤ 60፡14-17፤ 61፡6-7)። እስራኤል መንፈሳዊ ተሐድሶ እንደምታገኝም ብዙ ምንባቦች ይናገራሉ (ኢሳ. 2፡3፤ 44፡22-24፤ 45፡17፤ ኤር. 23፡3-6፤ 50፡20፤ ሕዝ. 36፡25-26፤ ዘካ. 13፡9፤ ሚልክ. 3፡2-3)። ስለተባረከው የእስራኤል ሁኔታ፥ ስለ መንፈሳዊ ተሐድሷቸውና ከአምላካቸው ጋር ስለሚኖራቸው አስደሳች ኅብረት የሚናገሩ ሌሎች ብዙ ምንባሶች አሉ። 

ምንም እንኳ ለአሕዛብ እንደ እስራኤል የተሰፋይቱ አገር ቃል ኪዳን የተገባላቸው ባይሆኑም፥ ብዙ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት እንደሚናገሩት የተትረፈረፈ በረከት ይጠብቃቸዋል (ኢሳ. 2፡2-4፤ 19፡24 25፤ 49፡6፥ 22፤ 60፡1-3፤ 62፡2፤ 66፡18. ኤር. 3፡17፤ 16፡19)። የመንግሥቱ ክብር ለእስራኤልም ሆነ ለአሕዛብ ዓለም ከዚህ ቀደም ከታየው ሁሉ እጅግ የላቀ ይሆናል። 

ረ. የሺህ ዓመቱ መንግሥት መንፈሳዊ በረከቶች 

ምንም እንኳ የሺህ ዓመቱ መንግሥት ክርስቶስ በምድር ላይ የሚገዛበት ፖለቲካዊ መንግሥት መሆኑ ቢገለጥም፥ የመንግሥቱ ባሕርይ ቀደም ባሉት ሥፍረዘመናት ታይቶ ለማይታወቅ የተትረፈረፈ መንፈሳዊ ሕይወት ምቹ ሁኔታዎችን ይፈጥራል። ይህም ሰይጣን ከመታሰሩ፥ ግልጥ ኃጢአት ፍርድን ከማስከተሉና ምድር ሁሉ እግዚአብሔርን ከማወቋ ጋር የተያያዘ ነው። ኢሳይያስ 11፡9 ውስጥ እንደተጠቀሰው፥ “ውሃ ባሕርን እንደሚከድን ምድር ሁሉ እግዚአብሔርን በማወቅ ትሞላለችና።” 

በትንቢተ ኤርምያስ እንደተገለጠው ኪዳን፥ ብዙ የመንፈሳዊ በረከት ተስፋ ቃላት ተሰጥተዋል። ኤርምያስ 31፡33-34 ውስጥ እንዲህ ተጎልጧል፡“ከእነዚያ ወራት በኋሳ ከእስራኤል ቤት ጋር የምገባው ቃል ኪዳን ይህ ነውና፥ ይላል እግዚአብሔር፤ ሕጌን በልቡናቸው አኖራለሁ፥ በልባቸውም እጽፈዋለሁ፤ እኔም አምላክ እሆናቸዋለሁ፤ እነርሱም ሕዝብ ይሆኑኛል። እያንዳንዱም ሰው ባልንጀራውን፥ እያንዳንዱም ሰው ወንድሙን፡እግዚአብሔርን እወቅ ብሎ አያስተምርም፤ ከታናሹ ጀምሮ እስከ ታላቁ ድረስ ሁሉ ያውቁኛልና፥ ይላል እግዚአብሔር። በደሳቸውን እምራቸዋሳሁና፥ ኃጢአታቸውንም ከእንግዲህ ወዲህ አሳሰብምና።” ይህ ዘመን የጽድቅና(መዝ. 72፡7፤ ኢሳ. 11፡3-5) ዓለም አቀፋዊ የሠላም ጊዜ ይሆናል (መዝ. 72፡7፤ ኢሳ. 2፡4)። መንፈሳዊ ሁኔታዎችም ለእግዚአብሔር ሕዝቦች ልዩ የሆነ ደስታና በረከትን ያስገኛሉ (ኢሳ. 12፡3-4፤ 61፡3፥ 7)። ዛሬ በቤተ ክርስቲያን እንደሚሆነው፥ መንፈስ ቅዱስ ያኔ አማኞችን ወደ መንፈሳዊ አካል የሚያጠምቃቸው መሆኑን የሚያመለክት መረጃ ባይኖርም፥ በሺህ ዓመቱ ዘመን በአማኞች ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ኃይል የሚኖር መሆኑ ግልጥ ነው (ኢሳ. 32፡15፤ 44 ፡3፤ ሕዝ. 39፡29፤ ኢዩ. 2፡28-29)። ልዩ ከሆነው ሁኔታ የተነሣ፥ ከማናቸውም ቀደምት ጊዜያት ሁሉ በላቀ በሺህ ዓመቱ መንግሥት ዘመን በዓለም በአጠቃላይ ከፍተኛ መንፈሳዊ በረከት ይኖራል። 

ሕዝቅኤል 40-46 ውስጥ የሺሀ ዓመቱ መንግሥት ቤተ መቅደስ እንደ አምልኮ ማዕከል ሆኖ ተጠቅሷል። ቤተ መቅደሱ ውስጥ ከሙሴ መሥዋዕት ለየት ያሉ መሥዋዕቶች ይቀርባሉ። የነዚህ መሥዋዕቶች መልእክት በቀጥታ ይወሰድ ወይስ ተምሳሌታዊ ትርጉም ይፈለግላቸው በሚለው አሳብ ዙሪያ የመጽሐፍ ቅዱስ አስተማሪዎች በአመለካከት ይላያያሉ። ይሁንና፥ የመቅደሱንም ሆነ የመሥዋዕት ሥርዓቱን ትንቢት እንዳለ ለመቀበል የማይቻልበት ተጨባጭ ምክንያት የለም። 

ምንም እንኳ የክርስቶስ ሞት የሙሴን ሕግና የመሥዋዕት ሥርዓቶቹን ከፍጻሜ ቢያደርሰው፥ በሕዝቅኤል የተጠቀሰው መሥዋዕት የክርስቶስን መስቀል መታሰቢያ ወደ ኋላ አሻግሮ የሚመለከት ይመስላል። የብሉይ ኪዳን መሥዋዕቶች የክርስቶስን መስቀል ወደ ፊት አሻግረው ይመለከቱ እንደነበረው ማለት ነው። የሺህ ዓመቱ መንግሥት ልዩ የሆነ መንፈሳዊ በረከት ስለሚኖረው፥ የኃጢአትን አስከፊነትና የክርስቶስን መሥዋዕት አሰፈላጊነት መረዳቱ ከማንኛውም ቀደምት ጊዜ በላይ አዳጋች ሳይሆን አይቀርም። ስለሆነም፥ የመሥዋዕት ሥርዓቱ ያስፈለገው ብቻውን ኃጢአት ለማስወገድ የሚችለውን የክርስቶስ መሥዋዕትን አስፈላጊነት ለማስታወስ ይሆናል። የብሉይ ኪዳን መሥዋዕቶች የክርስቶስን ሞት በትክክል ካመለከቱ፥ ሰሺህ ዓመቱ መንግሥትም በተመሳሳይ መንገድ ለመታሰቢያነት ለመጠቀም ይቻላል። 

ምንም ይሁን ምን፥ የሺህ ዓመቱ መንግሥት ግሩም የሆነ መንፈሳዊ በረከት የሚታይበትና ጽድቅ፥ ደስታና ይሳም የምድር መለያዎች የሚሆኑበት ዘመን እንደሚሆን ግልጥ ማረጋገጫ አለ። 

የመንፈሳዊ በረከቶች መትረፍረፍ በበኩሉ ከየትኛውም ቀደምት ዘመናት የተሻለ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገትን ያስከትላል። ሁሉም ፍትሕ የማግኘቱና ትሑቶች ከአደጋ የሚጠበቁበት ዘመን የመሆኑ እውነት ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ እኩልነትን ያስከትላል። ምናልባትም አብዛኛው ሰው ጌታን የሚያውቅ ይሆናል። ከምድርም ላይ ምርትን ያለመስጠት መርገም ይነሣና (ኢሳ. 35፡1-2)፥ ከፍተኛ ዝናብ ስርጭት ይኖራል (ኢሳ. 30፡23፤ 35፡7)። በአጠቃላይ፥ ዓለም ከዚህ በፊት አይታ የማታውቀው ዓይነት ብልጥግና፥ ጤንነት፥ መንፈሳዊና ቁሳዊ በረከት ይኖራታል። 

በተጨማሪም፥ በሺህ ዓመቱ መንግሥት ወቅት በምድር ላይ አስፈላጊ ለውጦች ይኖራሉ። አንዳንዶቹ በታላቁ መከራ ምክንያት የሚከሠቱ ሲሆኑ፥ ሌሎቹ ደግሞ ከክርስቶስ ዳግም ምጽአት ጋር የተያያዙ ናቸው። ያን ጊዜ የፅዮን ተራራ ካለበት ተነሥቶ ወደ ምሥራቅ ኢየሩሳሌም የሚያመራ ትልቅ ሸለቆ ይፈጠራል (ዘካ. 14፡4)። ሌላው አዲስ ነገር ኢየሩሳሌም ሰአካባቢዋ ከሚገኙት ግዛቶች የላቀች ትሆናለች (ዘካ. 14፡10)። ባጠቃላይ የተስፋይቱ ምድር እንደገና የዓለም ምድራዊ ገነት፥ የእግዚአብሔር መንግሥት ማዕከልና ያልተለመደ በረከት የሚታፈስባት ስፍራ ትሆናለች። በብዙ ገጽታዎች የሺህ ዓመቱ መንግሥት፥ ወርቃማው ዘመን፥ የምድር ታሪክ መጨረሻ፥ እግዚአብሔር ልጁን የዓለማት ጠቅላይ ገዥ አድርጎ የሚሾምበት ነው።

ምንጭ፡- “ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ ጭብጦች” መጽሐፍ በዶክተር ሉዊስ ስፔሪ ቼፈር የተጻፈ እና በተክሉ መንገሻ የተተረጎመ ነው፡፡ እግዚአብሔር ስለ እነዚህ ቅዱሳን ድንቅ ስራ የተመሰገነ ይሁን፡፡ ማሳሰቢያ፡- ይህን ጽሁፍ መቀየርም ሆነ ለሽያጭ ማዋል በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡

Exit mobile version