ሌሎች ትምሕርቶች

የመጽሐፍ ቅዱስ ማብራሪያ መተግበሪያ  (Amharic Bible Commentary App)

ከዚህ በታች ያለው የመጽሐፍ ቅዱስ ማብራሪያ መተግበሪያን ማውረድ እና መጠቀም የሚችሉት የአንድሮይድ ሞባይል ስልክ ተጠቃሚዎች ብቻ መሆናቸውን አስቀድመን ማሳወቅ እንፈልጋለን፡፡ መተግበሪያውን በስልክዎ ላይ ለማውረድ የሚከተለውን ቅደም ተከተል ተግባራዊ ያድርጉ፡፡ በመጀመሪያ፣ ከዚሀ በታች ያለውን “የመጽሐፍ ቅዱስ ማብራሪያ መተግበሪያውን ያውርዱ” የሚለውን ሊንክ ተጭነው ለአንድ ሰከንድ ይቆዩ፤ በመቀጠል ከቀረቡት አማራጮች መካከል “Download link ” የሚለውን በመምረጥ መተግበሪያውን ያውርዱ …

የመጽሐፍ ቅዱስ ማብራሪያ መተግበሪያ  (Amharic Bible Commentary App) Read More »

ሰዎች የክርስቶስን መልእክት ሳይሰሙ ሊድኑ ይችላሉ? 

እንግዲህ ዛሬ ስለ ደኅንነት ከሚነሡ ከባድ ከሆኑ ጥያቄዎች አንዱን ለመመለስ እንሞክራለን። ስለ ክርስቶስ ስፍጹም ሰምተው የማያውቁ አንዳንድ ሰዎች በእግዚአብሔር በማመናቸው ይድናሉ?  ከአንድ መቶ ዓመት በፊት አካባቢ፥ በደቡብ ኢትዮጵያ ኢሳ የተባለ ነቢይ ተነሥቶ ነበር። ይህ ነቢይ በሕይወቱ ዘመን በአብዛኛው በኢትዮጵያ ደቡባዊው ክፍል እየተዘዋወረ፥ ሰዎች ለርኩስ መናፍስት መስገዳቸውን ትተው አንዱን በሰማይ የሚኖር እውነተኛ አምላክ እንዲያመልኩ ያስተምራቸውና ያሳስባቸው …

ሰዎች የክርስቶስን መልእክት ሳይሰሙ ሊድኑ ይችላሉ?  Read More »

ለመሆኑ በመጨረሻው ሰዎች ሁሉ ይድናሉ ወይ? 

ሰዎች በክርስቶስ ሥራ ብቻ እንደሚድኑ ተመልክተናል (ትምህርት 13 እና 14)። እንደዚሁም እግዚአብሔር ወደ ራሱ የጠራቸው የሚያምኑና ንስሐ የሚገቡ፥ ኋላም ወደ እግዚአብሔር የሚመለሱ፥ በመጨረሻ የደኅንነትን በረከቶች እንደሚያገኙ ተገንዝበናል (ትምህርት 5 እና 16)። ስለዚህ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደተረጋገጠው፥ በክርስቶስ ውስጥ እምነታቸው የተረጋገጠላቸው ብቻ ይድናሉ። በተጨማሪም፥ እግዚአብሔር ክርስቶስን ንቀው ሳይቀበሉት የሚቀሩትን ለዘላለም እንደሚቀጣቸው የሚያስተምሩን ብዙ ጥቅሶች አሉ።  ጥያቄ- …

ለመሆኑ በመጨረሻው ሰዎች ሁሉ ይድናሉ ወይ?  Read More »

የሚሞቱ ሕፃናት ይድናሉ? 

ሕፃናት በሚሞቱበት ጊዜ የሚድኑ ወይም የማይድኑ ስለመሆናቸው ብዙ ሰዎች ጥያቄዎችን ይሰነዝራሉ። ይህ ጥያቄ ሕፃናት ለሚሞቱባቸው ክርስቲያን ለሆኑ ወላጆች በተለይ ጠቃሚ ነው። ሕፃናት የሚሞቱባቸው ወላጆች በጣም ያዝናሉ። ከዚህም በላይ የሚያስጨንቃቸው ጥያቄ፡- «ልጄን በሰማይ አገኘዋለሁን?» የሚለው ነው።  የሚሞቱ ሕፃናት በቀጥታ ወደ ሰማይ ይሂዱ ወይም ይቅሩ መጽሐፍ ቅዱስ በቀጥታ መልስ አይሰጥም። ሆኖም፣ ለዚህ ጥያቄ መልስ እንድናገኝ የሚረዱን ጥቂት …

የሚሞቱ ሕፃናት ይድናሉ?  Read More »

ቅዱስ ቁርባንን መቀበል፥ ደኅንነት ያስገኛል? 

ጥያቄ፡- ዮሐ 6፡53-54 እንብብ። ሀ) ጌታ ኢየሱስ፥ አንድ ሰው ሕይወትን ማግኘት ከፈለገ ምን ያድርግ ይላል? ለ) ጌታ ኢየሱስ አንድ ሰው ሥጋውን ቢበላና ደሙን ቢጠጣ ምንን ያገኛል አለ?  ጥያቄ ዮሐ. 6፡35 አንብብ። ጌታ ኢየሱስ አንድ ሰው እንዳይራብ ወይም እንዳይጠማ ምን ያድር አለ?  ብዙ ሰዎች የእግዚአብሔርን ጸጋ ተቀብለው ለመዳን ሲሉ ቅዱስ ቁርባንን መቀበል ይፈልጋሉ። ሌሎች ደግሞ ካልቀረቡ …

ቅዱስ ቁርባንን መቀበል፥ ደኅንነት ያስገኛል?  Read More »

ደኅንነትን የመቀበል ጥያቄ፣ እምነትና ጥምቀት  

በትምህርት 16 ውስጥ፥ ክርስቶስ በመስቀል ላይና በትንሣኤው የሰጠንን ደኅንነት እንዴት ሰዎች በየግላቸው ሊያገኙ እንደሚችሉ ተምረን ነበር። በዚህም ለደኅንነት መሠረታዊ የሆነ አንድ ዋና ነገር፥ በሦስት የተለያዩ መንገዶች መገለጣቸውን ተመልክተናል። እነዚህም ሦስቱ ንስሐ፥ እምነትና ወደ እግዚአብሔር መመለስ ናቸው። ሰዎች ኃጢአታቸው ከእግዚአብሔር ለይቶአቸው እንደ ነበረ መገንዘብና ከእግዚአብሔር ጋር ለመታረቅ በራሳቸው ሥራና በሌላም ነገር መታመን እንደሌለባቸው አውቀው፥ በአኳያው በጌታ …

ደኅንነትን የመቀበል ጥያቄ፣ እምነትና ጥምቀት   Read More »

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 3 

ባለፉት ሁለት ቀናት ውስጥ በተከታተልነው ትምህርት ላይ፥ መጽሐፍ ቅዱስ በእውነት ዳግም የተወለዱ ክርስቲያኖች ለዘላለም ዋስትናቸው የተጠበቀ መሆኑን እንደሚያስተምር ተገንዝበናል። እግዚአብሔር እነርሱን የማዳኑን ተግባር እነርሱ ከእርሱ ጋር የታረቁ መሆናቸውን በማሳወቅ ጀምሮአል፤ ይህንንም የጀመረውን የማዳን ተግባር በታማኝነት ከግብ ያደርሳል። በዚሁ መሠረት የመጨረሻው የደኅንነታቸው ዋስትና እንዲሆንም የራሱን መንፈስ ቅዱስ ሰጥቶአቸዋል፤ ይህንንም ሲያደርግ ማንም ከፍቅሩ ሊለያቸው እንደማይችል ተስፋውን አክሎ …

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 3  Read More »

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 2 

በትናቱ ዕለት ትምህርታችን ስለ አማኞች ዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጥ ወይም ጥበቃ ማጥናት ጀምረናል። በዚህ ትምህርት ላይም፥ አማኞች በደኅንነታቸው ረገድ ሁኔታው ዋስትና እንዳለውና የተጠበቀላቸው መሆኑን ተመልክተናል። ይህ ሊሆን የቻለበትም ምክንያት፥ ከእግዚአብሔር ጋር በመታረቃቸውና ሰላምንም በመመሥረታቸው ምክንያትና እንደዚሁም እግዚአብሔር ሁልጊዜ የጀመረውን ሥራ ስለሚፈጽም ነው። ከዚህም ጋር መንፈስ ቅዱስን የተቀበሉ በመሆናቸውና ኢየሱስ ራሱ ስለሚጠብቃቸው፥ ከዚህም የተነሣ አዲስ ሰዎች ስለሆኑ …

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 2  Read More »

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫ እና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 1 

በክርስቲያኖች መካከል የሚነግ አንደኛው አስቸጋሪና አከራካሪ የሆነ ርእሰ ጉዳይ፥ እውነተኛና ዳግም የተወለዱ አማኞች ደኅንነታቸውን ይዘውት ይቆያሉ ወይስ ያገኙትን የሚያጡበት ሁኔታ ይኖራል? የሚለው ነው። / ማንኛውም ክርስቲያን በአንድ ወቅት ክርስቶስን አምነው የተቀበሉና ኋላ ግን ይህን እምነታቸውን የተዉ ሰዎችን የሚያውቅ ይመስለኛል። አብዛኛዎቹ እማኞች አንድ ጊዜ መልካም የክርስትና አካሄድ የነበራቸውና ኋላ ላይ በኃጢአት ውስጥ ከመውደቃቸው የተነሣ ያንን የመልካም …

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫ እና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 1  Read More »

የደኅንነት በረከቶች – እንከብራለን ሲባል ምን ማለት ነው?  

ሰዎች ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ አዳኛቸው አምነው በሚቀበሉበት ጊዜ፥ እግዚአብሔር አስደናቂና የተትረፈረፉ የደኅነት በረከቶችን በላያቸው ላይ ያፈስሳል። በዚህም አዲስ ሕይወትን ይሰጣቸዋል፥ ከክርስቶስ ጋር ኅብረት እንዲኖራቸው በማድረግ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር ይላቸዋል፣ ከዚያም ከእርሱ ጋር መታረቃቸውን በማሳወቅ፥ የቤተሰቡ አካል ያደርጋቸውና በፊቱ ቅዱሳን ሆነው እንዲገኙ በሕይወታቸው ውስጥ ይሠራል። ሆኖም፣ እያንዳንዱን አማኝ ወደፊት የሚጠብቀው በረከት አለ፣ ይህም የክብር በረከት ነው። …

የደኅንነት በረከቶች – እንከብራለን ሲባል ምን ማለት ነው?   Read More »