ሀ) መጽሐፍ ቅዱስ ስለ እግዚአብሔር ያስተምረናል
የእግዚአብሔር ቃል እምነት ሊጣልበት የሚችል መሆኑ – ሉቃስ 21፡33
የእግዚአብሔርና የቃሉ ስልጣን – ማቴ 4፡4፤ ዮሐ 10፡35
መጽሐፍ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ የተደረሰ መጽሐፍ ነው – 2ጢሞ 3፡16
መጽሐፍ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ ምሪት የተጻፈ ነው – 2ጴጥ 1፡21
ለ) መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔርን ለእኛ ለመግለጽ ሰዋዊ የሆኑ መግለጫዎችን ይጠቀማል
ክንድና እጅ – ዘጸ 3፡20፤ ዘዳ 4፡34፤ ዘጸ 5፡15
ፊት – ዘፍ 4፡14፤ 33፡10፤ ኢሳ 59፡2
አይኖችና ጆሮዎች – ኢሳ 37፡17፤ መዝ 11፡4፤ 34፡15፤ መሳ 15፡3፤ ዘካ 4፡10
መሄድና መምጣት – ዘፍ 11፡5፤ ኢሳ 64፡1-3፤ መዝ 18፡9-19
የእግዚአብሔር ድምጽ ለአዳምና ለሙሴ ተሰማ – ዘፍ 3፡9፣ 10፤ ዘዳ 4፡12
የእግዚአብሔርን ድምጽ መስማት እንችላለን – ዘዳ 5፡24፤ ሐዋ 22፡14
ሐ) እግዚአብሔር፣ ሰዎች ሊረዱት በሚችሉት መንገድ ይገለጣል
በራዕይ – ዳን 7፡9፣ 13፤ ራዕ 4፡3፤ 5፡7
በቀጥታ – አዳም – ዘፍ 3፡8-10 – ያዕቆብ – ዘፍ 32፡24-30 – አብርሃም – ዘፍ 18 ኢያሱ – ኢያሱ 5፡13-15 – ዳንኤል – ዳን 3፡ 25
እግዚአብሔር በኢየሱ በኩል – ማቴ፣ ማር፣ ሉቃ እና ዮሐ
መ) የፈጠራቸውን ነገሮች በመመልከት (ተፈጥሮን)
በ (ሮሜ 1፡18-25) የተጠቀሰውን ትምህርት ይመልከቱ።
ሰማያት የእግዚአብሔር ክብር ይናገራሉ – መዝ 19፡1
ተፈጥሮ የእርሱን ዘላለማዊ ሃይልና መለኮትነት ያበስራል – ሮሜ 1፡20
ህሊናችንና/ልባችን የእግዚአብሔርን ሕግ ያውቃል – ሮሜ 2፡14-16
የምድር በረከት ምስክር ነው – ሐዋ 14፡15-17
የእግዚአብሔር እውቀትና ጥበብ – መዝ 19፡1-6፤ 104
የእግዚአብሔር ሃይልና ግርማ ሞገስ – መዝ 18፡7-15፤ 29፤ 66፡1-7
ሠ) እግዚአብሔርን በተፈጥሮ ውስጥ ብቻ የማወቅ ጎዶሎ ጎኖች
ተፈጥሮ ሙሉዉን ድነት ለመረዳት በቂ አይደለም።
የማያምኑ ሰዎች አእምሮ በሰይጣን ታውሯል – 2ቆላ 4፡4
ሰባኪ ያስፈልጋል – ሮሜ 10፡14
የአዳም መውደቅ በተፈጥሮ ውስጥ የነበረውን የእግዚአብሔር ምስል በክሎታል። ለአብነት – በምጥ ጊዜ ያለ ህመም – ዘፍ 3፡16፤ አድካሚ ስራ፤ እሾህና አሜኬላ – ዘፍ 3፡17-18፤ ፍጥረት ሁሉ ለመታደስ በመጠባበቅ ላይ ይገኛል – ሮሜ 8፡18-25
ረ) እግዚአብሔር በክርስቶስ ኢየሱስ በሙላት ተገልጧል
ወልድ ለሚወደው ሁሉ አብን ይገልጥለታል – ማቴ 11፡27፤ ሉቃስ 10፡22
እኔን ያየ አብን አየ – ዮሐ 14፡6-7፤ 10፡30
ቃልም እግዚአብሔር ነበረ…ቃልም ሥጋ ሆነ – ዮሐ 1፡1-14
ሰ) እግዚአብሔር መንፈስ ነው (ዮሐ 4፡24)
ስለዚህ እራሱን ሊገልጥልን ይገባል – 1ሳሙ 3፡21
አንዳንድ ነገሮች ምስጢር እንደሆኑ ይቆያሉ – ዘዳ 29፡29
አንዳንድ ነገሮችን ለሰው ልጅ ይገልጻል – ዓሞጽ 3፡7፤ ኤፌ 3፡5
ሙሴ የእግዚአብሔርን ድምጽ ሰማ ነገር ግን እግዚአብሔርን አልተመለከተውም – ዘጸ 4፡12
ሰው እግዚአብሔርን አይቶ በሕይወት መቆየት አይችልም – ዘጸ 33፡20
ማስታወሻ፡- እግዚአብሔር መንፈስ ስለሆነ ራሱን ሊገልጥልን ይገባል፡፡
ሸ) እግዚአብሔር ለሰዎች ራሱን ለምን ይገልጣል?
በመከራ ጊዜያቸው ወቅት ሊያድናቸው – 2ሳሙ 22፡7፤ መዝ18፡6
ኖሕ ከጥፋት ውሃ ዳነ – ዘፍ 6፡1 – 9፡17
አብርሃም ከ ጣኦት አምልኮ ዳነ – ዘፍ 12፡1 – 22፡19
ሙሴ ከባርነት ነጻ ለመውጣት – ዘጸ 3፡-14፡
ድነትን ለመስጠት – ማቴ 1፡21
የሰይጣንን ስራ ለማፍረስ – 1ዮሐ 3፡8
ስለመጻኢ ጊዚያት ለማስጠንቀቅ – ዓሞጽ 3፡7፤ ራዕ 1፡-22
በዚህ ድረ ገጽ ውስጥ በአዘጋጁ የተጻፉ እና የተተረጎሙ እንዲሁም በተለያዩ አገልጋዮች የተዘጋጁ የድነት ትምሕርቶች፣ የደቀ መዝሙር ትምሕርቶች፣ የአዲስ ኪዳን እና ብሉይ ኪዳን ማጥኛዎችን ጨምሮ በርካታ መንፈሳዊ ጽሑፎችን ያገኛሉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ከኤስ አይ ኤም ጋር በመተባበር የተዘጋጀ በአንድሮይድ ስልክ ላይ የሚጫን በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ ማብራሪያ መተግበሪያ (Amharic Bible Commentary App) ያገኛሉ፡፡ የወንጌል በድረ-ገጽ አገልግሎት ዌብ ሣይት (https://ethiopiansite.com/) የፊት ገጽ ግርጌ ላይ በመሄድ፣ በስተቀኝ ባልው ክፍት ሣጥን ውስጥ የኢ-ሜይል አድራሻዎን በመጻፍና “ድረ-ገጹን ይከታተሉ” የሚለውን ቁልፍ በመጫን የዌብ ሣይቱ ተከታይ (follower) እንዲሆኑ ተጋብዘዋል፡፡ ይህን ሲያደርጉ በዌብ ሣይቱ ላይ አዳዲስ ጽሑፎች ሲጫኑ፣ በኢ-ሜይል አድራሻዎ የማስታወሻ መልእክት (notification) የሚያገኙ ይሆናል፡፡