በርካታ ሰዎች ኢየሱስ በስጋ የተገለጠ አምላክ መሆኑን በመካድ ሃሰተኛ ሃይማኖትን መስርተው ከእዉነት መንገድ ሸሽተዋል። በተጨማሪ ሃሰተኛ ወንጌሎች የሚለውን ይመልቱ።
ሀ) ኢየሱስ ስለራሱ ምን ይላል?
– ከሰማይ መጥቷል በሰማይም ይኖራል – ዮሐ 3፡13
– በሁሉም ስፍራ ይኖራል – ማቴ 18፡20
– የሰንበት ጌታ እንኳ ሳይቀር እንደሆነ ተናግሯል – ማር 2፡27-28 ይህ በእግዚአብሔር ነገር ሁሉ ላይ ስልጣኑን ያሳያል
– እግዚአብሔርን አባቴ ብሎ ይጠራል – ዮሐ 5፡17-18 ትርጓሜውም ከእግዚአብሔር ጋር እኩል እንደሆነ ያሳያል – ዮሐ 5፡ 17-18
– ከአባቱ ጋር አንድ ነው፣ ስለዚህም እግዚአብሔር ነው – ዮሐ 5፡30-33
– ኢየሱስ በአባቱ ስም መምጣቱን ተናገሯል – ዮሐ 5፡43
– እርሱን ማየትና መወቅ አብን ማየትና ማወቅ ነው – ዮሐ 14፡7-11
– በመጽሐፍ ቅዱስ ስልጣን ያወራል – ማቴ 5፡21-22፣ 27-28
– “እኔ ነኝ” የሚል ስያሜን ለራሱ ይጠቀማል – ዮሐ 18፡5-8። “እኔ ነኝ” የሚለው ስያሜ የእግዚአብሔር ስያሜ ነው – ዘጻ 3፡ 14
– ከአብርሃም በፊት መኖሩን ተናግሯል – ዮሐ 8፡58
– ንጉስና ፈራጅ እንደሆነ ተናግሯል – ማቴ 25፡31-46። ብሉይ ኪዳን ያህዊን እንደፈራጅ ያሳየናል – ዘፍ 18፡25፤ ኢዮ 3፡18
– ስልጣን በሰማይና በምድር የእርሱ መሆኑን ይናገራል – ማቴ 28፡18-20
ለ) ሌሎች ስለ ኢየሱስ ምን አሉ?
– ‹‹ከሁሉ በላይ ሆኖ ለዘላለም የተባረከ አምላክ ነው›› ብሎ ጳውሎስ ፅፏል – ሮሜ 9፡5
– የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ብሏል ብለው አይሁድ ተናግረዋል – ዮሐ 19፡7
– ራሱን ከእግዚአብሔር ጋር አስተካክሏል ብሎ ዮሐንስ ተናግራል – ዮሐ 5፡18
– ጻፎች እግዚአብሔር ብቻ የሚያደርገውን ያደርጋል ብለውታል – ማር 2፡5-7
– ዘላለማዊ፣ ፈጣሪ፣ እግዚአብሔር መሆኑ ተፅፎለታል – ዮሐ 1፡1-5 – ቶማስ ‹‹ጌታዬና አምላኬ›› ብሎታል – ዮሐ 20፡28
– አለማት በእርሱ ተፈጠሩ – ዕብ 1፡2፤ ዮሐ 1፡3፤ ቆላ 1፡16
– ኢየሱስ የእግዚአብሔር ፍፁም ምሳሌ ነው – ዕብ 1፡3
– ፍጥረት ሁሉ በኢየሱስ ተጋጥሟል – ዕብ 1፡3፤ ቆላ 1፡17
– ኢየሱስ በመላዕክት አምልኮ ቀርቦለታል – ዕብ 1፡6
– ወልድ “እግዚአብሔር” ተብሏል – ዕብ 1፡8 – ዘላለማዊ ነው – ዕብ 1፡12
– እርሱ መልአክ ሳይሆን ከመላዕክት በላይነው – ዕብ 1፡4፤ 1ጴጥ 3፡22
– ከሙሴ በላይ ነው – ዕብ 3፡1-6
– ከብሉይ ኪዳን ሊቀካህናት በላይ ነው – ዕብ 4፡14-5፡10
– የእግዚአብሔር ባሕሪይ ባሕሪዩ ነው – ፊል 2፡6-11
– የማይታየው አምላክ አምሳል ነው – ቆላ 1፡15-20
– የመለኮት ሙላት በክርስቶስ አካል ውስጥ ይኖራል – ቆላ 1፡15-20
-‹‹ጌታ›› የሚለው ስያሜ ለአብና ወልድ ጥቅም ላይ ውሏል
አብ – ማቴ 1፡20፤ 9፡38፤ 11፡25፤ ሐዋ 17፡24፤ ራዕ 4፡11
ወልድ – ሉቃስ 2፡11፤ ዮሐ 20፡28፤ ሐዋ 10፡36፤ 1ቆሮ 2፡8፤ ራዕ 19፡16
ሐ) አምላካዊ አምልኮን ተቀብሏል
– የጥበብ ሰዎች አምልከውታል – ማቴ 2፡11
– ደቀ መዛሙርት አምልከውታል – ማቴ 14፡3
– ከነናዊቷ ሴት አምልካዋለች – ማቴ 15፡25
– የተፈወሰው ሰው አምልኮታል – ዮሐ 9፡38
– ሁለቱ ማርያሞች አምልከውታል – ማቴ 28፡9
– ከእርገቱ በኋላ ደቀ መዛሙርት አምልከውታል – ሉቃስ 24፡52
– የእግዚአብሔር መላእክት አምልከውታል – ዕብ 1፡6
– አራቱ ሕያዋን ፍጡራን እና ሃያ አራቱ ሽማግሌዎች አምልከውታል – ራዕ 5፡8
መ) እግዚአብሔር አብ ስለእርሱ ምን ይላል?
– የአባትና – ልጅ ግንኙነት – ማቴ 3፡17፤ ማቴ 17፡5፤ ዮሐ 8፡16-19፤ 1ዮሐ 5፡9
ይህ ግንኙነት ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን እኩልነት ያመለክታል – ዮሐ 5፡17-18
በዚህ ድረ ገጽ ውስጥ በአዘጋጁ የተጻፉ እና የተተረጎሙ እንዲሁም በተለያዩ አገልጋዮች የተዘጋጁ የድነት ትምሕርቶች፣ የደቀ መዝሙር ትምሕርቶች፣ የአዲስ ኪዳን እና ብሉይ ኪዳን ማጥኛዎችን ጨምሮ በርካታ መንፈሳዊ ጽሑፎችን ያገኛሉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ከኤስ አይ ኤም ጋር በመተባበር የተዘጋጀ በአንድሮይድ ስልክ ላይ የሚጫን በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ ማብራሪያ መተግበሪያ (Amharic Bible Commentary App) ያገኛሉ፡፡ የወንጌል በድረ-ገጽ አገልግሎት ዌብ ሣይት (https://ethiopiansite.com/) የፊት ገጽ ግርጌ ላይ በመሄድ፣ በስተቀኝ ባልው ክፍት ሣጥን ውስጥ የኢ-ሜይል አድራሻዎን በመጻፍና “ድረ-ገጹን ይከታተሉ” የሚለውን ቁልፍ በመጫን የዌብ ሣይቱ ተከታይ (follower) እንዲሆኑ ተጋብዘዋል፡፡ ይህን ሲያደርጉ በዌብ ሣይቱ ላይ አዳዲስ ጽሑፎች ሲጫኑ፣ በኢ-ሜይል አድራሻዎ የማስታወሻ መልእክት (notification) የሚያገኙ ይሆናል፡፡