ወደ ገላትያ ሰዎች

በመንፈስ መመላለስ የሚገኝ የመንፈስ ቅዱስ ፍሬ (ገላ. 5፡16-6፡18)።

ከብሉይና አዲስ ኪዳን አስደናቂ ልዩነቶች አንዱ መንፈስ ቅዱስ በአማኞች ሕይወት ውስጥ የሚጫወተው ሚና ነው። በብሉይ ኪዳን፥ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት የተወሰኑ መሪዎች የመሪነትና ጠላቶቻቸውን የማሸነፍ ተግባር እንዲያከናውኑ የሚያስችላቸው የእግዚአብሔር ኃይል ነበር። ስለሆነም፥ መንፈስ ቅዱስ ለጥቂት ሰዎች የሚሰጥ ሲሆን፥ አንዳንድ ጊዜ ከኃጢአት ወይም ከአገልግሎታቸው ፍጻሜ በኋላ መንፈስ ቅዱስ ይለያቸው ነበር። በአዲስ ኪዳን ግን እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን ለልጆቹ …

በመንፈስ መመላለስ የሚገኝ የመንፈስ ቅዱስ ፍሬ (ገላ. 5፡16-6፡18)። Read More »

የእምነት ሕይወት የንጽሕናና ሌሎችን የማገልገል ነጻነት ያመጣል (ገላ. 5፡1-15)

ዘነበ የዩኒቨርስቲ ክርስቲያን ተማሪዎች ኅብረት አባል ነበር። ከሳምንታዊ አምልኳቸው በአንዱ አንድ ግለሰብ በክርስቶስ ስለሚገኝ ነጻነት ሰበከ። ሰባኪው፥ «ከሕግ ነፃ ስለሆናችሁ የፈለጋችሁትን ሁሉ ልታደርጉ ትችላላችሁ። ክርስቶስ ለኃጢአታችሁ እንደ ሞተ እስካመናችሁ ድረስ ምንም ዓይነት ሕግ መጠበቅ አያስፈልጋችሁም። ስለሆነም፥ ‹አትዋሽ፥ አትስረቅ፤ አታመንዝር የሚሉ የእግዚአብሔር ሕግጋት ከእንግዲህ በእኛ ላይ ተፈጻሚነት የላቸውም። እነዚህን ሕግጋት መጠበቅ አያስፈልገንም። በተጨማሪም፥ እግዚአብሔር ደስ የሚሰኘው …

የእምነት ሕይወት የንጽሕናና ሌሎችን የማገልገል ነጻነት ያመጣል (ገላ. 5፡1-15) Read More »

ጳውሎስ ድነት (ደኅንነት) ሕግጋትን በመጠበቅ ሳይሆን በክርስቶስ በማመን እንደሚገኝ አብራራ (ገላ. 3፡1-4፡31)

የውይይት ጥያቄ፡- ገላ. 3-4 አንብብ። ድነት (ደኅንነት) በእምነት ብቻ መሆኑን እንዴት እንደምናውቅ ጳውሎስ ያቀረበውን ክርክር ጠቅለል አድርገህ ግለጽ። ብዙውን ጊዜ በክርስቶስ አዳኝነት ላይ በሚደገፉና ሥራቸው ለደኅንነታቸው አስተዋጽዖ እንዳለው በሚተማመኑ ሰዎች መካከል ያለውን ልዩነት ለማወቅ አስቸጋሪ ነው። ሁለቱም የብሉይ ኪዳን ሕግጋትን ሊጠብቁ ይችላሉ። ሁለቱም መጠጥ ላይጠጡ፥ ተገቢ ልብሶችን ሊለብሱ፥ ግብረገባዊ ሕይወት ሊመሩ፥ ወዘተ… ይችላሉ። በሁለቱ መካከል …

ጳውሎስ ድነት (ደኅንነት) ሕግጋትን በመጠበቅ ሳይሆን በክርስቶስ በማመን እንደሚገኝ አብራራ (ገላ. 3፡1-4፡31) Read More »

ጴጥሮስ በአንጾኪያ የወንጌሉን ግንዛቤ የሚያዛባ ተግባር በመፈጸሙ ጳውሎስ ተጋፈጠው (ገላ. 2፡11-21)።

ጳውሎስ ወደ ሶርያ አንጾኪያ ከተመለሰ በኋላ፥ ጴጥሮስ በዚያ የሚገኙትን አብያተ ክርስቲያናት ለመጎብኘት ወደዚያው ሄደ። በመጀመሪያ ካልተገረዙና «ከረከሱ» አሕዛብ ጋር መብላትን የሚከለክለውን የአይሁዶች ልማድ ጥሶ ጴጥሮስ በብሉይ ኪዳን ያልተፈቀደውን ምግብ በላ። ከዚያ በኋላ ግን አንዳንድ አጥባቂ የአይሁድ ክርስቲያኖች ከኢየሩሳሌም መጥተው አይሁዳውያን ክርስቲያኖች እንዳይረክሱ ከአሕዛብ ጋር ኅብረት እንዳያደርጉ አስተማሩ። ጴጥሮስም ጠቃሚ ሚና ከነበራቸው የኢየሩሳሌም ቤተ ክርስቲያን መሪዎች …

ጴጥሮስ በአንጾኪያ የወንጌሉን ግንዛቤ የሚያዛባ ተግባር በመፈጸሙ ጳውሎስ ተጋፈጠው (ገላ. 2፡11-21)። Read More »

ጳውሎስ ወንጌሉ ከእግዚአብሔር እንደ መጣና በሐዋርያት እንደ ጸደቀ ያሳያል (ገላ. 1፡11-2፡10)።

የሐሰት አስተማሪዎቹ ጳውሎስ እውነተኛ ሐዋርያ እንዳልሆነ፥ መልእክቱም አንድም ራሱ የፈጠረው አሊያም ወደ እርሱ በሚተላለፍበት ጊዜ እንደ ተበረዘ በመግለጽ ይከስሱት ነበር። ምናልባትም ደግሞ በኢየሩሳሌም የሚገኙ ሐዋርያት በማይቀበሉት መንገድ እንደ ለወጠው ገልጸው ነበር። ጳውሎስ ንጹሑን ወንጌል የሚያስተምር እውነተኛ ሐዋርያ መሆኑን በመግለጽ ለዚህ ክስ ምላሽ ለመስጠት ፈለገ። ሐዋርያት እንኳን ትምህርቱን አጽድቀውለት ነበር። ስለሆነም፥ ጳውሎስ እግዚአብሔር ለሐዋርያነት ከጠራው ጊዜ …

ጳውሎስ ወንጌሉ ከእግዚአብሔር እንደ መጣና በሐዋርያት እንደ ጸደቀ ያሳያል (ገላ. 1፡11-2፡10)። Read More »

መግቢያ (ገላ. 1፡1-10)

ጥላሁን ከቤተ ክርስቲያኒቱ ታዋቂ ወጣቶች አንዱ ነበር፡ በሰንበት ትምህርት ቤት መምህርነትና የኳዩር ዝማሬን በመሳሰሉት የተለያዩ አገልግሎቶች ይሳተፍ ነበር። ጥላሁን ይህን ታዋቂነት ስለወደደ ሰዎች ያሚፈልጓቸውን ነገሮች ማድረጉን ቀጠለ። አብዛኞቹ ወጣቶች ስሜታዊ አምልኮን ስለሚወዱ ጥላሁን ፕሮግራም ስሚመራበት ጊዜ ሁሉ ምእመናኑ ጮክ ብሎ ስሜታዊ እንቅስቃሴ እንዲያደርግ ያበረታታል። አንዳንድ አባላት የፈውስ አገልግሎት በመፈለጋቸው ጥላሁን ይህንኑ አዘጋጀ። በሰዎች ዘንድ ማራኪና …

መግቢያ (ገላ. 1፡1-10) Read More »

የገላትያ መልእክት ልዩ ባሕርያት፣ መዋቅር፣ እና አስተዋጽኦ

የገላትያ መልእክት ምናልባትም ጳውሎስ ከጻፋቸው እጅግ ጠንካራና ቁጡ ደብዳቤዎች ሁሉ ሳይልቅ አይቀርም። ጳውሎስ ለገላትያ ሰዎች ወንጌሉን ለመመስከር ሲል በድንጋይ ከተወገረና ከሞት አፋፍ ላይ ከተረፈ በኋላ እውነተኛውን ወንጌል ትተው የሐሰት ትምህርቶችን በመከተል ላይ መሆናቸውን መስማቱ በጥልቀት አቆሰለው። ከሌሎች የጳውሎስ መልእክቶች በተቃራኒ፥ በገላትያ መልእክት ውስጥ ምንም ዓይነት የማበረታቻና የምስጋና ቃላት አልተካተቱም። ጳውሎስ የመልእክቱ ጸሐፊ መሆኑን ከነገራቸው በኋላ …

የገላትያ መልእክት ልዩ ባሕርያት፣ መዋቅር፣ እና አስተዋጽኦ Read More »

የገላትያ መልእክት ዓላማ

የውይይት ጥያቄ፡- ሀ) «ወንጌል» ማለት ምን ማለት እንደሆነ አብራራ። ለ) አንድ ሰው ለመዳን ሰምቶ ስለሚያምነው ወንጌል በምናብራራበት ጊዜ ልናካትታቸው የሚገቡን እውነቶች ምን ምንድን ናቸው? ሐ) ስለ ወንጌሉ ምንነትና ሰዎች ሰምተው ይድኑ ዘንድ ስለሚቀርበው ምስክርነት አንድ ክርስቲያን ጥርት ያለ ግንዛቤ መጨበጥ የሚያስፈልገው ለምን ይመስልሃል? የመጀመሪያው ዓላማ፡ ጳውሎስ ወንጌሉን በርዟል ለሚለው ክስ ምላሽ ለመስጠት። ጳውሎስ የእውነተኛ ወንጌልን …

የገላትያ መልእክት ዓላማ Read More »

የገላትያ መልእክት መግቢያ

በጳውሎስ ዘመን የነበሩ አይሁዳውያን ክርስቲያኖች፥ «ድነትn (ደኅንነት) ለማግኘትና በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነትን ለማግኘት ከፈለግህ መገረዝ አለብህ፥ በክርስቶስ ማመኑ ብቻ በቂ አይደለም» ይሉ ነበር። ዛሬም አንዳንድ ወንጌላውያን፥ «የዘላለምን ሕይወት ለማግኘት ከፈለግህ መጠጥ ማቆምና ሁለተኛ ሚስትህን ማባረር ይኖርብሃል፥ በክርስቶስ ማመኑ ብቻ በቂ አይደለም» ይላሉ። ወንጌል ምንድን ነው? አንድ ሰው በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነትን ለማግኘት ምን ማድረግ ይኖርበታል? ከዳንን በኋላስ …

የገላትያ መልእክት መግቢያ Read More »