ሀ) የእግዚአብሔር መልካምነት ማቴ 19፡16-17
ለ) የእግዚአብሔር ምህረትና ጭከና ሮሜ 11፡22
ሐ) ቅዱስ ራዕ 4፡8
– እንደእግዚአብሔር ያለ ቅዱስ የለም 1ሳሙ 2፡2፤ ራዕ 15፡4
– እግዚአብሔር ቅዱስ፣ ፍጹም ነው ሌዋ 19፡2፤ ማቴ 5፡48
– ከቅድስናው ተካፋዩ ልንሆን ይገባል ዕብ 12፡10፣ 14፤ 1ጴጥ 1፡16
– መንፈስ ቅዱስ ሊቀድሰን ይመጣል ሮሜ 15፡16
– ቅድስና ውብ ነው 2ዜና 20፡21፤ መዝ 29፡2
– ቅድስና-ንጽሕና የሚለውን ርዕስ በተጨማሪ ይመልከቱ ክፍል ሠ11
መ) ጻድቅና ትክክል ራዕ 16፡15፤ 19፡2
– እግዚአብሔር ኅጢአትን ይጸየፋል ዕብ 1፡8-9
– በመንግስቱ ክፋት አያድርም 1ቆሮ 6፡9-10
– በተጨማሪ እነዚህን ጥቅሶች ይመልከቱ ኢዮብ 34፡12፤ መዝ 7፡9፤ 116፡5፤ 119፡137
– ጽድቁን ልንካፈል ይገባል 1ዮሐ 3፡7 – ኃጢአትን ልንጠላ ይገባል ዕብ 12፡4፤ 1ዮሐ 3፡8-9
ሠ) አፍቃሪና ርኅሩኅ ዮሐ 3፡16፤ መዝ 69፡16፤ ሰ.አር 3፡22-23
– እግዚአብሔር ፍቅር ነው 1ዮሐ 4፡8፤ ቲቶ 3፡4-5
– ፍቅሩን ልንካፈል ይገባል ዘሌ 19፡18፤ ሉቃስ 10፡27፤ ሮሜ 13፡9፤ ገላ 5፡14
– እግዚአብሔርን ለእኛ ያለው ፍጹም ፍቅር ፍርሃታችንን አስወግዶ ይጥላል 1ዮሐ 4፡18
– ወደ እግዚአብሔር በድፍረት መግባት ሆኖልናል ዕብ 4፡16
– ከእግዚአብሔር ፍቅር የሚለየን የለም ሮሜ 8፡38-39
– ከፍቅር ጋር በተያያዘ ለትምህርት የሚሆን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል 1ቆሮ 13፡4-7
ረ) ታማኝና እውነተኛ ኢሳ 25፡1፤ ራዕ 3፡14፤ 19፡11
– ሰው ሃሰተኛ ቢሆንም እንኳ እግዚአብሔር ታማኝ ሆኖ ይኖራል ሮሜ 3፡4፤ ዮሐ 17፡3
– ተስፋን የሰጠው አምላክ የታመነ ነው ዕብ 10፡23፤ 11፡11
– ለመታደስ እርሱን ተስፋ እናደርጋለን 1ተሰ 5፡23-24፤ 2ጢሞ 1፡12
– ከኃጢአት ሊያስመልጠን እርሱ የታመነ ነው 1ቆሮ 10፡13
– ታማኝ የሆኑ ሰዎችን ማግኘት አስቸጋሪ ነው ምሳሌ 20፡6
– እግዚአብሔር እንደ እርሱ ታማኝ የሆኑ ሰዎችን ይፈልጋል (ራዕ 2፡10፤ 17፡14፤ 2ጢሞ 2፡2) ሙሴ – ዘኁ 12፡7፣ ዳንኤል – ዳን 6፡4፣ ኤጳፍራ፣ ቲኪቆስ፣ አናሲስም – ቆላ 1፡7፤ 4፡7፣ 9፣ ዳዊት – 1ሳሙ 22፡14፣ ኢየሱስ – ራዕ 19፡11
– እግዚአብሔር ታማኞችን ይጠብቃል – መዝ 31፡23
– የእግዚአብሔር አይኖች በታማኞች ላይ ነው – መዝ 101፡6
– እግዚአብሔር ታማኝ ባሪያን ይሸልማል – ማቴ 25፡21
ሰ) ለጋስ
– እግዚአብሔር ይሰጣል
ቅዱሳት መጻሕፍትን – 2ጢሞ 3፡16
አንድያ ልጁን – ዮሐ 3፡16፤ ሮሜ 8፡32
መንፈስ ቅዱስን – ሉቃስ 11፡13፤ 1ተሰ4፡8፤ ሮሜ 5፡5 ንስሃን – 2ጢሞ 2፡25
የዘላለም ህይወት ስጦታን – ሮሜ 6፡23፤ 1ዮሐ 5፡11
ለትሁታን ጸጋን – 1ጴጥ 5፡5፤ ያዕ 1፡5
ለደካማው እረፍትን – ማቴ 11፡28
ጥበብን – ዳን 2፡23፤ ያዕ 1፡5
በክርስቶስ ኢየሱስ ለእኛ ድልን – 1ቆሮ 15፡57
የማገልገል ብቃትን – 1ጴጥ 4፡11፤ ኤፌ 3፡7
ለፍጥረት ሁሉ ምግብን – መዝ 136፡25 ኅ
ብት የማፍራት ችሎታን – ዘዳ 8፡18
ለምድራዊ ገዢዎች ስልጣንን – ዳን 2፡37
– ከእግዚአብሔር የልግስና ባሕሪ ልንካፈል ይገባል። መስጠት የሚለውን ክፍል በተጨማሪ ይመልከቱ – ክፍል ሰ8
ሸ) የእግዚአብሔር ታላቅነት
ሁሉን አዋቂ – በሁሉ ስፍራ የሚገኝ – ሁሉን ማድረግ የሚችል – ዘላለማዊ – የማይለወጥ
ቀ) እግዚአብሔር ጠቢብ፣ ሁሉን አዋቂ ነው – ሮሜ 16፡27
– እግዚአብሔር አዋቂ ጌታ ነው – 1ሳሙ 2፡3
– ጥበቡ ጥልቅ ናት – ኢዮብ 9፡4
– ከሰው መረዳት በላይ ነው – መዝ 139፡4-6፤ ሮሜ 11፡33
– የእግዚአብሔር ጥበብ ባሕርይ – ያዕ 3፡17
ንጹሕ – ከሃሰት ጋር የማይቀየጥ
ሰላማዊ – ጠብን የማይጭር
ጨዋ – አስቸጋሪ/የማይመች ወይም ግትር ያልሆነ
መኀሪ – ሕግን ሳይሆን የእግዚአብሔርን ፍቅር የሚገልጥ
የማያዳላ – ለራስ ወይም ለወገኔ ይጠቅማል በሚል የማይሰራ
ግብዝነት የሌለበት – የሚለውን የሆነ
– እግዚአብሔርዊ ያልሆነ ጥበብ ባሕሪይ
አለማዊ፣ ሥጋዊ፣ የአጋንንት ጥበብ – ያዕ 3፡14-16
ለእግዚአብሔር ሞኝነት የሆነ – 1ቆሮ 3፡18-20
– ለአማኞች ጥበብ ተዘጋጅቷል – ያዕ 1፡5-7፤ ቆላ 1፡9፤ ኤፌ 1፡17
ክርስቶስ ጥበባችን ነው – 1ቆሮ 1፡24፤ ቆላ 2፡2
የክርስቶ ቃል ጥበባችን ነው – ቆላ 3፡16
– የጥበብ ቃል መንፈሳዊ ስጦታ – ክፍል ረ11
በ) እግዚአብሔር በሁሉ ቦታ በአንድ ጊዜ ይገኛል – መዝ 139፡7-12
– ስለዚህ በየትኛውም ስፍራ ብንጸልይ እርሱ ይሰማናል፡፡
– ሁሉን ነገር በሁሉ ረገድ ይሞላል – ኤፌ 1፡22-23
– ከማናችንም ሩቅ አይደለም – ሐዋ 17፡27-28፤ ኤር 23፡23
– በሲኦል፣ በሰማይ – መዝ 139፡8፤ ዓሞጽ 9፡2-3
– ከእርሱ ልንደበቅ አንችልም – ኤር 23፡24
– ይህ ማለት እግዚአብሔር በሁሉም ነገር ውስጥ አለበት ማለት አይደለም፡፡ እግዚአብሔር ሰዎች በሚከተሉት ነገሮች ሲወቅሳቸው እናነባለን፡
ጣኦትንና ዲያብሎስን ሲያመልኩ – ኢሳ 2፡8-11፤ 20-21፤ ራዕ 9፡20
የተፈጠሩትን ሲያመልኩ – ሮሜ 1፡25
መላዕክትን ሲያመልኩ – ቆላ 2፡18፤ ራዕ 22፡8-9
የሙታን መናፍስትን ሲያመልኩ – ዘሌ 20፡6፤ ዘጻ 18፡9-11፤ ኢሳ 8፡19
– ማስታወሻ፡ በድፍረት መጸለይ እንችላለን – ኤር 33፡3
ተ) እግዚአብሔር ሁሉን ቻይ ነው
– እርሱ የሰማያትና የምድር ፈጣሪ ነው – ዘፍ 1፡1
– ሁሉም ነገር በአንድ ላይ ተያይዞ የጸናው በእርሱ ነው – ቆላ 1፡17
– ሃይሉ ታላቅ ነው – ኢዮብ 9፡4
– ስለዚህ ሊያድንና ሊታደግ ይችላል – ኢሳ 50፡2
– ሁሉ ለእግዚአብሔር ይቻላል – ማቴ 19፡26፤ ኤር 32፡17
– ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር አለን? – ኤር 32፡27
– የእግዚአብሔር ድካም ከሰዎች ብርታት ይበረታል – 1ቆሮ 1፡25
– ሃይሉን ልንካፈል ይገባል – ኢዮ 3፡10፤ 2ቆሮ 12፡10፤ ዕብ 11፡34
– በእግዚአብሔር ጸጋ ልንበረታ ይገባል – 2ጢሞ 2፡1
– በሃይ ልንበረታ ይገባል – ኤፌ 6፡10
– ሰይጣንን ለመርታት ልንበረታ ይገባል – 2ቆሮ 10፡3-5
– በእምነት ልንበረታ ይገባል – ሮሜ 4፡20
– ለመበርታትና ለመበዝበዝ – ዳን 11፡32
ቸ) እግዚአብሔር ዘላለማዊ ነው – 1ዮሐ 5፡20
– ከዘላለም እስከዘላለም – መዝ 90፡1-2
– መጀመሪያና መጨረሻ – ራዕ 22፡13
– ያለ፣ የነበረና፣ የሚመጣው – ራዕ 1፡8
– ከእርሱ በፊትና በኃላ ምንም የለም – ኢሳ 43፡10
– ዘላለማዊ ሕይወቱን መካፈል እንችላለን – ዮሐ 3፡15-16፤ ሮሜ 6፡23፤ 1ዮሐ 5፡11-13
– የሰጠነውን አደራ ይጠብቃል – 2ጢሞ 1፡12
ነ) እግዚአብሔር አይለወጥም – ሚል 3፡6
– ስለዚህ የፍቅር ስጦታው ሊታመን ይችላል፡፡
– ኢየሱስ ክርስቶስ ትላንትና፣ ዛሬ፣ ወደፊት ያው ነው – ዕብ 13፡8
– በእርሱ ዘንድ መለዋወጥ የለም – ዕብ 1፡17
– እርሱን ለመምሰል መለወጥ አለብን – 1ዮሐ 3፡2፤ 1ቆሮ 15፡51-53
በዚህ ድረ ገጽ ውስጥ በአዘጋጁ የተጻፉ እና የተተረጎሙ እንዲሁም በተለያዩ አገልጋዮች የተዘጋጁ የድነት ትምሕርቶች፣ የደቀ መዝሙር ትምሕርቶች፣ የአዲስ ኪዳን እና ብሉይ ኪዳን ማጥኛዎችን ጨምሮ በርካታ መንፈሳዊ ጽሑፎችን ያገኛሉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ከኤስ አይ ኤም ጋር በመተባበር የተዘጋጀ በአንድሮይድ ስልክ ላይ የሚጫን በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ ማብራሪያ መተግበሪያ (Amharic Bible Commentary App) ያገኛሉ፡፡ የወንጌል በድረ-ገጽ አገልግሎት ዌብ ሣይት (https://ethiopiansite.com/) የፊት ገጽ ግርጌ ላይ በመሄድ፣ በስተቀኝ ባልው ክፍት ሣጥን ውስጥ የኢ-ሜይል አድራሻዎን በመጻፍና “ድረ-ገጹን ይከታተሉ” የሚለውን ቁልፍ በመጫን የዌብ ሣይቱ ተከታይ (follower) እንዲሆኑ ተጋብዘዋል፡፡ ይህን ሲያደርጉ በዌብ ሣይቱ ላይ አዳዲስ ጽሑፎች ሲጫኑ፣ በኢ-ሜይል አድራሻዎ የማስታወሻ መልእክት (notification) የሚያገኙ ይሆናል፡፡