Site icon

ቤተ ክርስቲያን ከሚሄዱ ክርስቲያኖች መካከል ከ 80% በላይ የሚሆኑት መጽሐፍ ቅዱሳቸውን በየቀኑ አያነቡም

የክርስቲያን አገር እየተባልች በምትጠራው ሰሜን አሜሪካ ውስጥ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2012ዓ.ም. በተደረገው ጥናት መሰረት ወደ ቤተ ክርስቲያን ከሚሄዱ ክርስቲያኖች መካከል ከ 80% በላይ የሚሆኑት መጽሐፍ ቅዱሳቸውን በየቀኑ እንደማያነቡ ገልጿል። እንግዲህ በጥናቱ መሰረት አዘውትረው ወደ ቤተ ክርስቲያን ከሚሄዱት 100 ክርስቲያኖች መካከል መጽሐፍ ቅዱሳቸውን በየእለቱ የሚያነቡት ከ20 የሚያንሱ ናቸው። እርሶ ከየትኛው ጎራ ነዎት? ከሚያነቡቱ ከሆኑ እሰየሁ፣ በዚሁ ይቀጥሉ። ከማያነቡቱ ወገን ከሆኑ ከዚህ በታች ያሉትን ጥቂት ማነሳሻ ሃሳቦች ይመልከቱና የመጽሐፍ ቅዱስ እውቀቶን ይመዝኑ የሚለውን ሊንክ በመጫን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናትዎን እንዲጀመሩ እናበረታታዎታለን።

የእግዚአብሔር ቃል የክርስቲያን ሁሉ ነገሩ ነው። የሰው ልጅ ያለምግብ ስጋው መኖር እንደማይችል ሁሉ መንፈሱ ደግሞ ያለ እግዚአብሔር ቃል ሕያው ሊሆን አይችልም። ለዚህ ነው ጌታችንና መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፣ “ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም” ሲል የተናገረው (ማቴ. 4:4)። የመጽሐፍ ቅዱስ እውቀቶን ይመዝኑ የሚለውን ሊንክ በመጫን በጥያቄና መልስ እየታገዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናትዎን እንዲጀመሩን መንፈስዎን ያለማቋረጥ እንዲመግቡ እናበረታታዎታለን።

 

Exit mobile version