Site icon የሕይወት እንጀራ

የሰው ልጅ ስብዕና አወቃቀር (ሥጋ፣ ነፍስና መንፈስ)

ሰው መንፈስ፥ ነፍስና ሥጋ (አካል) እንዲኖረው ሆኖ በእግዚአብሔር የተፈጠረ ልዩ ፍጡር ነው (ዘፍጥረት 1፡27፣ 1ኛ ተሰሎንቄ 5፡23)።

1. ሥጋችን (ውጫዊው ሰው)

ሥጋችን ማለትም “የውጭው ሰው”፥ በምንኖርበት ዓለም ውስጥ አካላዊ መኖሪያችን ነው። ሥጋችን ለመብላት፥ ለመጠጣትና ለመተኛት የሚያስችሉ ውስጣዊ ፍላጎቶችን በማሟላት በዋናነት በአምስቱ የስሜት ሕዋሳት አማካኝነት ይሠራል።

2. ነፍሳችን (የስብዕና ማዕከል)

ነፍሳችን ደግሞ አእምሯችን (ዕውቀታችን)፥ ፈቃዳችን እና ስሜታችን የሚገለጡበት የስብዕናችን ማዕከል ነው።

3. መንፈሳችን (ውስጣዊው ሰው)

መንፈሳችን የውስጡ ሰውነታችን ነው። የእግዚአብሔር መንፈስ የሚናገረውም ለውስጡ ሰውነታችን ነው። እኛም ለእግዚአብሔር የምናቀርበው ትክክለኛ እና እውነተኛ አምልኮ የሚመነጨው ከዚሁ ማንነታችን ውስጥ ነው። ኢየሱስ እንዲህ አለ፦ “እግዚአብሔር መንፈስ ነው፥ የሚሰግዱለትም በመንፈስና በእውነት ሊሰግዱለት ያስፈልጋቸዋል” (ዮሐንስ 4፡24)።

ጳውሎስ በመልዕክቶቹ “የውስጥ ሰውነት” የሚለውን ሐረግ በተደጋጋሚ ተጠቅሟል (2ኛ ቆሮንቶስ 4:16፣ ኤፌሶን 3:16)። ሮሜ 7፡22-23 እንዲህ ይላል፦ “በውስጡ ሰውነቴ በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለኛልና፥ ነገር ግን በብልቶቼ ከአእምሮዬ ሕግ ጋር የሚዋጋውንና በብልቶቼ ባለ በኃጢአት ሕግ የሚማርከኝን ሌላ ሕግ አያለሁ።”

1ኛ ቆሮንቶስ 2፡11 እንዲህ ይላል፦ “በእርሱ ውስጥ ካለው ከሰው መንፈስ በቀር ለሰው ያለውን የሚያውቅ ሰው ማን ነው? እንዲሁም ደግሞ ከእግዚአብሔር መንፈስ በቀር ለእግዚአብሔር ያለውን ማንም አያውቅም።”

Exit mobile version