Site icon የሕይወት እንጀራ

“የኢየሱስ ነቢይነት ለእስራኤላውያን ብቻ ነው፡፡”

የኢየሱስ ክርስቶስ አገልግሎት ክርስቲያኖች እንደሚያምኑት ለሰው ዘር ሁሉ ሳይሆን ለእስራኤላውያን ብቻ ነው ሲሉ አንዳንድ ሙስሊሞች ይሟገታሉ፡፡ ከዚህ የመከራከሪያ ነጥብ ላይ በመነሳትም ክርስቲያኖች (እንደ እነሱ እምነት ‹‹ዘመን የማይሽረውና የአለሙ ሁሉ ነቢይ›› የሆነውን) ሙሐመድን እንዲከተሉ ለማሳመን ይጥራሉ፡፡ ይህንን መከራከሪያቸውን በማስረጃ ለማስደገፍም በፍጥነት ከአዲስ ኪዳን የሚከተለውን ጥቅስ ያነሳሉ፡፡

ማቴዎስ 10፡5፣6

ማቴዎስ 15፡24

በመጀመሪያ ደረጃ ኢየሱስ በአብርሃም፣ ይስሃቅና ያዕቆብ ዘር ውስጥ እንደ ተወለደ ማስተዋል ያስፈልጋል፡፡ ኢየሱስ፣ ከብዙ ምእተ ዓመታት በኃላ የተፈፀመውና እግዚአብሔር ለአብርሃም የገባለት ቃል ኪዳን ፍፃሜ ነው፡፡ አብርሃም ለእግዚአብሔር ፈቃድ ባሳየው መታዘዝና ፍፁም መገዛት እግዚአብሔር ሁለት ዘርፍ ያለው ቃል ኪዳን ገብቶለት ነበር፡፡ የቃል ኪዳኑ የመጀመሪያ ዘርፍ፣ እግዚአብሔር የአብርሃምን ዘር ማለትም ይስሃቅን፣ ያዕቆብን (እሥራኤል) እና የእሥራኤልን ዘሮች ሁሉ ለመባረክ ቃል ኪዳን መግባቱ ሲሆን የቃል ኪዳኑ ሁለተኛ ዘርፍ ደግሞ ከዚህ ዘር (ማለትም ከአብርሃም ይስሃቅና ያዕቆብ ዘር) መካከል ለአሕዛብ ሁሉ የሚሆን በረከት እንደሚገኝ ማለትም በዘሩ አሕዛብ ሁሉ እንደሚባረኩ ቃል ኪዳን መግባቱ ነበር (የሐዋሪያት ሥራ 3፡25፣ 26 እና ገላቲያ 3፡8፣14 ይመልከቱ)፡፡

ለአብርሃም በተገባለት ቃል ኪዳን መሠረት የእሥራኤል ዘርና አሕዛብ (እሥራኤላዊ ያልሆነ የሰው ዘር በሞላ) እንደሚባረኩ ማወቅ ይቻላል፡፡ የዚህ ቃል ኪዳን መፈፀም ከብዙ ምዕተ አመት በኃላ በኢየሱስ መወለድ ተረጋግጧል፡፡ ኢየሱስ በተወለደ ጊዜ በእስራኤላውያን ልማድ መሠረት ቤተሰቡ ሃይማኖታዊ የሆነውን ስርአት ለመፈፀም ወደ መቅደስ ይዘውት ሄዱ፡፡ በመቅደስ ይፀልይ የነበረ አንድ ሽማግሌ ሰው በመንፈስ በመረዳት ሕፃኑን በእጆቹ በመያዝ በፀሎቱ ውስጥ የሚከተለውን ለእግዚአብሔር ተናገረ፡-

ሉቃስ 2፡30-32

ከላይ በተመለከትነው ምንባብ መሠረት ኢየሱስ ሁለት ፈርጅ ያለው አገልግሎት እንደ ነበረው መገንዘብ እንችላለን፡፡ በመጀመሪያ፣ እነደ እሥራኤላዊ ሆኖ ስለ ተወለደ የመጀመሪያ ተልዕኮው ራሱንና እግዚአብሔርን ለእስራኤላውያን መግለጥ ነበር፡፡ የአብርሃም፣ ይስሃቅና ያዕቆብ ዘሮች በእግዚአብሔር የተመረጡ ሕዝቦች ነበሩና፡፡ ቁርአን ሳይቀር ስለዚህ ጉዳይ ምስክርነቱን አይሸሽግም፡፡

ሱረቱ ሷድ (38)፡45፣46

And commemorate Our servants Abraham, Isaac, and Jacob, possessors of power and vision. Verily, we did chose them for a special (purpose)– proclaiming the message of the hereafter.

ሱረቱ አል-በቀራህ (2)፡47

Children of Israel, call to mind the (special) favour which I bestowed upon you, and that I preferred you to all others (for My message).

እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን እንዲህ አይነቱን ልዩ ምርጫና ጥሪ ያደረገ ቢሆንም፣ በሚያሳዝን ሁኔታ እስራኤላውያን ለእግዚአብሔር ጥሪ እልኸኞችና ግዴለሾች ሆኑ፡፡ በዚህም ምክንያት ኢየሱስ በእግዚአብሔር የተመረጠውን ሕዝብ ለመቤዠት፣ በእግዚአብሔር የተቀባና የተባረከ፣ እሥራኤልም ለረጅም ዘመናት ይጠብቀው የነበረ መሲህ መሆኑን ለማረጋገጥ በመካከላቸው ድንቅንና ምልክቶችን እያደረገ እንዲያገለግል ግድ ሆነበት፡፡ ይህን የመጀመሪያ ተልዕከኮውን ለመወጣት፣ ኢየሱስ በአገልግሎቱ ወቅት ደቀ መዛሙርቱ ወደ እሥራኤል ልጆች ብቻ እንዲሄዱ አዘዛቸው፡፡ እስራኤላውያን መልዕክቱን በመጀመሪያ መስማት የተገባቸው ነበሩና፡፡ በእግዚአብሔር የበረከት ተስፋ የተገባላቸው የቃል ኪዳን ሕዝቦች ስለ ነበሩ ይህን ልዩ መብትና ጥቅም በመጀመሪያ ሊያጣጥሙ ተገብቷቸዋል፡፡ ከኢየሱስ ሞትና ትንሳኤ በኃላ ከደቀ መዛሙርቱ መካከል አንዱ ለእስራኤላውያን እንዲህ ሲል ንግግር አደረገ፡-

የሐዋሪያት ሥራ 3፡25፣26

የኢየሱስ ተልዕኮ ሁለተኛ ክፍል ከፍተኛ ትርጉም እንዳለው አፅንኦት ሊሰጠው ይገባል፡፡ ይህ ተልዕኮ ነፍሱን ለሰው ዘር ኃጢአት ቤዛ አድርጎ የሰጠበት ነው (1ጢሞቴዎስ 2፡4-6)፡፡ ይህ ነው እንግዲህ ለሰው ልጆች ሁሉ የሆነው የበረከት የምሥራች፡፡ የምሥራቹም፣ ኢየሱስ በመስቀል ላይ ባፈሰሰው ደምና በተቀበለው ስቃይ በሰዎች ላይ የነበረውን የኃጢአት ቅጣት ማስወገዱ ነው፡፡ ማንም ይህንን የድኅነት/የመዳን በረከት ቢቀበል ከእግዚአብሔር ጋር ለዘላለም የመኖር ዋስትና ያገኛል!

ሉቃስ 24፡46፣47

በመሲሁ ኢየሱስ በኩል የሆነው ይህ ድኅነት/መዳን ለአይሁድና ለመላው የዓለም ሕዝብ ሁሉ የተሰጠ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ በግልፅ ይናገራል፡፡ ያስተውሉ፣ ኢየሱስ በምድር ላይ በነበረው አገልግሎቱ ወቅት ደቀ መዛሙርቱ ወደ እሥራኤላውያን ዘንድ ብቻ እንዲሄዱ አዟቸው ነበር፡፡ ነገር ግን በሁለተኛ የአገልግሎት ክፍሉ (መስቀል ላይ ሞት ከተቀበለ በኃላ) ደቀ መዛሙርቱን ምን ብሎ እነዳዘዛቸው ከዚህ በታች በቀረቡ ጥቅሶች ያስተዉሉ፡-

የሐዋሪያት ሥራ1፡8 

ማቴዎስ 28፡19-20 

ዮሐንስ 8፡12

ቁርአን ሳይቀር የኢየሱስን አለማቀፋዊ አገልግሎት በግልፅ ያስቀምጣል፡፡ እስቲ የሚከተሉትን ክፍሎች እንመልከት፡-

ሱረቱ- መርየም (19)፡20፣21

And (We wish) to appoint him (Jeses) as a sign unto men (ayat-al linnasi), and a mercy from Us.

አንዳንድ ሙስሊሞች እንድናምን እንደሚፈልጉት ይህ ክፍል ‹‹ለእስራኤላውያን ብቻ የሆነ ምልክት›› እንደማይል አንባቢ ያስተውል፡፡ እንደውም አረቢኛው ‹‹ለሰው ዘር ሁሉ ምልክት!›› ነው የሚለው፡፡

Exit mobile version