Site icon የሕይወት እንጀራ

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 9-28)

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

መግቢያ

ስለ መንፈስ ቅዱስ ለምን እናጠናለን?

ሥነ መለኮት ምንድን ነው?

መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የምንረዳበት ምንጭ

መንፈስ ቅዱስን ማወቅ

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ስፍራ

የመንፈስ ቅዱስ ዋና ኃላፊነቶች ምንና ምን ናቸው?

የመንፈስ ቅዱስ ስሞች

የመንፈስ ቅዱስ ተምሳሌቶች

እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ማን ነው?

መንፈስ ቅዱስ፤ ሦስተኛው የሥላሴ አካል

መጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ አምላክ መሆኑን ያሳየናልን?

መንፈስ ቅዱስ በብሉይ ኪዳን

የእግዚአብሔርን ሕዝብ ይመሩ ዘንድ መሪዎችን ብቁ በማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል እንዲጽፉ በመምራት የሰጠው አገልግሎት

የብሉይ ኪዳን ነቢያት መሢሑ የሚመጣበትን ወቅትና የመንፈስ ቅዱስ አገልግሉት የሚለወጥበትን ጊዜ እስቀድመው አመልክተው ነበር

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት በወንጌላት

መንፈስ ቅዱስ በጌታ ኢየሱስ ሕይወትና አገልግሎት ውስጥ

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የሰጠው ትምህርት፤ ክፍል 1

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ያስተማረው ትምህርት፤ ክፍል 2

ክርስቲያኖች እንደ መንፈስ ቅዱስ ባሉ መሠረታዊ የክርስትና አስተምህሮዎች ላይ ባላቸው አመለካከት ልዩነት የሚያሳዩት ለምንድን ነው?

መንፈስ ቅዱስን በተመለከተ የተለያዩ መረዳቶች የሚታዩት ለምንድን ነው?

በመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችና በአምልኮ ልምምዶች ውስጥ ያሉ ልዩነቶችን እንዴት መያዝ አለብን?

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 1-2 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 3-8 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 9-28)

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 1

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 2

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 3

የጴንጤቆስጤ ሥነ መለኮት ታሪክ

የጰንጠቆስጤና የአንዳንድ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ዋና ትምህርቶች ምን ምን ናቸው?

ከካሪዝማቲክ ትምህርት ለቤተ ክርስቲያን የተረፉ መልካም ውጤቶች

በካሪዝማቲክ የሥነ መለኮት ትምህርት የሚገኙ ሚዛናዊ ያልሆኑ ነገሮች

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል አንድ)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሁለት)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሦስት)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 1)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 2)

በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና ልሳን በመናገር መካከል ያሉ ግንኙነቶች

የመንፈስ ቅዱስ አማኞችን ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ የመምራት አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ እንድናመልክ ይረዳናል

መንፈስ ቅዱስ የክርስቲያኖች ሕይወት ኢየሱስን እንዲመስል የሚሰጠው አገልግሎት

ሰይጣንን ድል የማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

ስለ መንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች መግቢያ

መንፈሳዊ ስጦታ ምንድን ነው?

መንፈሳዊ ስጦታ (ሮሜ 12፡1-8)

መንፈሳዊ ስጦታ (ኤፌሶን 4፡1-16 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ጴጥሮስ 4፡7-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡1-3)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡4-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡12-31 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 13)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡1-19)

መንፈሳዊ ስጦታዎችና የማያምኑ ሰዎች (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡20-40)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 1)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 2) የተለያዩ ዓይነት ልሳናት አሉን?

በቤተ ክርስቱያን ውስጥ ስለሚመጣው ትንቢት ተጨማሪ አሳቦች

ትንቢት ምንድን ነው? ነቢይስ?

የትንቢት ስጦታ ምንድን ነው?

የእውነተኛና ሐሰተኛ ነቢያት ንጽጽር

የትንቢት ስጦታን ለመጠቀም መመሪያዎቹ ምን ምን ናቸው?

የመፈወስና ተአምራትን የማድረግ ስጦታዎች

የብሉይ ኪዳን ተአምራትና አዲሱን ዘመን በተስፋ መመልከት

ተአምራትና ፈውሶች በአዲስ ኪዳን

እግዚአብሔር ፈውስን የሚሰጥባቸው የተለያዩ አሠራሮች

ስለ ተአምራትና ፈውሶች የሚሰጡ የተሳሳቱ አሳቦች

የመንፈሳዊ ስጦታዎች ትምህርት ማጠቃለያ

በመንፈስ ቅዱስ መሞላት

የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምንድን ነው?

ከኤፌ 5፡18-20 በመንፈስ ቅዱስ ስላ መሞላት ምን ልንመለከት እንችላለን?

በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ማረጋገጫዎች

በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት የሚቀርቡ ቅድመ ሁኔታዎች

በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና መንፈሳዊ ብስለት

የመጀመሪያው የመንፈስ ቅዱስ ዋና ሥራ፡- ዘላለማዊው አምላክ በውስጣችን መኖሩ

የመንፈስ ቅዱስ ሁለተኛ ዋና ተግባሩ፡- ወደ ኢየሱስ ማመልከትና እርሱን እንድንመስል ማድረግ።

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች ክለሳ

ጥያቄ፡- የሐዋ 9፡5-22፤ 27-28፤ 31፤ 10፡1-48፤ 11፡2-18፣ 22-24፤ 13፡1-3፣ 6-12፣ 52፤ 15፡6-11፣ 27-29፤ 16፡6-10፤ 19፡1-7፤ 20፡22-24፣ 28፤ 21፡4፣ 11 አንብብ። በእነዚህ ጥቅሶች የሚገኙትን የተለያዩ የመንፈስ ቅዱስ እጎልሎች ዘርዝር። 

ሀ. ጳውሎላ በዳነበት ወቅት የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት (የሐዋ. 9)። እግዚአብሔር ጳውሎስን በደማስቆ መንገድ እንዴት እንደተገናኘው የሚናገረውን ታሪክ ሁላችንም እናውቀዋለን። እግዚአብሔር ሐናንያ የተባለን ሰው ጳውሎስ በኢየሱስ ማመኑን እንዲያረጋግጥ ነገረው። ሐናንያ በጳውሎስ ላይ እጁን በመጣን ይህን አጸና። ሐናንያ በጳውሎስ ላይ እጁን በማነ ጊዜ ማየት መቻል ብቻ ሳይሆን በመንፈስ ቅዱስም ተሞላ። ይህ ሙላት በምን እንደተረጋገጠ አልተገለጠልንም። የምንመለከተው ነገር ወዲያውኑ ጳውሎስ መጀመሪያ በደማስቆ ቀጥሎም በኢየሩሳሌም ስለ ኢየሱስ በድፍረት የሚመሰክር ሰው ሆነ። ዛሬ ሰዎች ብዙ ጊዜ ከመንፈስ ቅዱስ ሙላት ጋር የሚያያይዟቸውን በልሳናት መናገርንና የተአምራትን ጉዳይ እዚህ ላይ አናይም። 

ለ. ከታላቁ ልደት በኋላ አማኞችን ያጠነከራቸውና ያበረታታቸው መንፈስ ቅዱስ ነበር። 

ሐ. መንፈስ ቅዱስ በእሕዛብ ላይ ወረደ (ይህንንም ክስተት ወደፊት በሌላ ትምህርት እንመለከታለን።) 

መ. መንፈስ ቅዱስ የቤተ ክርስቲያን መሪዎችን ይመራቸው ነበር። ጴጥሮስን ወደ ቆሮነሌዎለ ቤት መርቶታል። ጳውሎስና በርናባስን ለወንጌል መልእክተኝነት ሥራ በመለየት ወደ መጀመሪያው የወንጌል መልእክት ጉዞአቸው የላካቸው መንፈስ ቅዱስ ነው። አሕዛብ ክመጻናቸው በፊት የብሉይ ኪዳንን ሕዓጋትን በመከተል ወደ አይሁድነት መግባት ይባቸው እንደሆነና እንዳልሆነ በሚወያዩበት ወቅት የቤተ ክርስቲያን መሪዎችን የመራቸው እርሱ ነበር። ጳውሎስ በሁለተኛው ሐዋርያዊ ጉዞው ወቅት መንፈስ ቅዱስ ወደ አንዳንድ ስፍራዎች እንዳይሄድ በመከላከል ወደ ሌሎች ስፍራዎች ቀን እንዲሄድ መርቶታል። በኢየሩሳሌም እስር እንደሚጠብቀው ቢያውቅም እንኳ እንዲሄድ ግድ ያለው መንፈስ ቅዱስ ነበር። ስለዚህ በመጀመሪያይቱ ቤተ ክርስቲያን ከመንፈስ ቅዱስ ዋነኛ አገልሎቶች አንዱ ለክርስቲያኖች በሥራቸው ምሪትን መስጠት ነበር። 

ሠ. አንዳንድ ሰዎች በቤተ ክርስቲያን እረኞችና መሪዎች እንዲሆኑ የሚሾም መንፈስ ቅዱስ ነበር። ጳውሎስ በኤፌሶን ለነበሩ ሽማግሌዎች የመጨረሻ የስንብት ንግግር በሚያደርግላቸው ወቅት እንደ መሪዎች የመረጣቸው መንፈስ ቅዱስ መሆኑን ነግሮአቸው ነበር። ስለዚህ ለራሳቸው ሕይወትና በቤተ ክርስቲያን ላሉ ክርስቲያኖች ሕይወት መጠንቀቅ ነበረባቸው። 

ረ. መንፈስ ቅዱስ አንዳንድ ሰዎች ስለ ወደፊት ጉዳይ ትንቢት እንዲናገሩ አስችሎአል። እነዚህ ሰዎች ጳውሎስ ወደ እስር ቤት እንደሚጣል አውቀው ነበር። ሆኖም ግን የሚናገሩት መልእክት ሁል ጊዜ ከመንፈስ ቅዱስ ለመሆኑ ግልጽ አልነበረም። ምከንያቱም ጳውሎስ መደ ኢየሩሳሌም እንዳይሄድ ግድ ብለውት ነበር። ይህም ጳውሎስ ወደ ኢየሩሳሌም እንዲሄድ መንፈስ ቅዱስ እንዳዘዘው ከተናገረ በኋላ በመሆኑ ጉዳዩን ስናጤነው መንፈስ ቅዱስ በሚፈልገውና ነቢያቱ በሚፈልጉት መካከል የኦሳብ ግጭት ነበር። 

ጥያቄ፡- ሀ) ከእነዚህ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች መካከል ዛሬ በቤተ ክርስቲያንህ የሚያስፈልጉት የትኞቹ ናቸው? ለምን? ለ) የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ እንደሚገልጸው መንፈስ ቅዱስ ለፈጸማቸው ነገሮች ሁሉ የዛሬውን ትምህርት በመከለስ ዝርዝር አዘጋጅ። 

በዚህ ትምህርት የመንፈስ ቅዱስ ጥናታችንን በሐዋርያት ሥራ የተዘገበልንን በማየት ጀምረናል። በእያንዳንዱ ገጽ መንፈስ ቅዱስ ተጠቅሷል። በዓላምና በክርስቲያኖች የሚፈጸሙት ተግባራቱ ኢየሱስ ከጀመረው የአዲስ ኪዳን ዘመን ዋነኛ ምልክቶች አንዱ ነው። ክርስቲያኖች የአሳብ ልዩነት የሚያሳዩባቸውን ሰርካታ ክፍሎች በሌላ ትምህርት እናጠናለን። ነገር ግን የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍን ስቃኘንበት ወቅት ከድነት (ደኅንነት) እስክ ክርስቲያናዊ እውነት ብሎም በቤተ ክርስቲያን እስከማገልገል ድረስ ያለው የማንኛውም ክርስቲያን ልምምድ የሚፈጸመው በመንፈስ ቅዱስ ኃይል መሆኑ ተመልክቷል። ስለ መንፈስ ቅዱስ አወዛጋቢ ጉዳዮች ስናጠና ከመንፈስ ቅዱስ አገልቀሎቶች አብዛኛዎቹ አማኞች ሁሉ የሚስማሙባቸው እንደሆኑ መዘንጋት የለብንም። የሚበጀን የምንለያይባቸውን ነጥቦች እየመዘዙ መጣላት ሳይሆን የምንስማማባቸው ሰፊ ክልሎች እንዳሉ መገንዘብ ነው። በተጨማሪ ልዩነት በምናሳይባቸው ትምህርቶችና ልምምዶች ላይ መጽሐፍ ቅዱስ ምን እንደሚያስተምር ለመረዳት በጥንቃቄ ላማጥናት ቆርጠን እንነሣ። ይህንን በሚቀጥሉት ትምህርቶች እንደግማለን።

ምንጭ፡- “የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ”፣ በቲም ፌሎስ ተጽፎ፣ በጌቱ ግዛው የተተረጎመ እና በኤስ አይ ኤም ጽሑፍ ክፍል የተዘጋጀ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 3-8 ) የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 1
Exit mobile version