የሕይወት እንጀራ አገልግሎት

ሥነ መለኮት ምንድን ነው?

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

መግቢያ

ስለ መንፈስ ቅዱስ ለምን እናጠናለን?

ሥነ መለኮት ምንድን ነው?

መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የምንረዳበት ምንጭ

መንፈስ ቅዱስን ማወቅ

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ስፍራ

የመንፈስ ቅዱስ ዋና ኃላፊነቶች ምንና ምን ናቸው?

የመንፈስ ቅዱስ ስሞች

የመንፈስ ቅዱስ ተምሳሌቶች

እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ማን ነው?

መንፈስ ቅዱስ፤ ሦስተኛው የሥላሴ አካል

መጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ አምላክ መሆኑን ያሳየናልን?

መንፈስ ቅዱስ በብሉይ ኪዳን

የእግዚአብሔርን ሕዝብ ይመሩ ዘንድ መሪዎችን ብቁ በማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል እንዲጽፉ በመምራት የሰጠው አገልግሎት

የብሉይ ኪዳን ነቢያት መሢሑ የሚመጣበትን ወቅትና የመንፈስ ቅዱስ አገልግሉት የሚለወጥበትን ጊዜ እስቀድመው አመልክተው ነበር

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት በወንጌላት

መንፈስ ቅዱስ በጌታ ኢየሱስ ሕይወትና አገልግሎት ውስጥ

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የሰጠው ትምህርት፤ ክፍል 1

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ያስተማረው ትምህርት፤ ክፍል 2

ክርስቲያኖች እንደ መንፈስ ቅዱስ ባሉ መሠረታዊ የክርስትና አስተምህሮዎች ላይ ባላቸው አመለካከት ልዩነት የሚያሳዩት ለምንድን ነው?

መንፈስ ቅዱስን በተመለከተ የተለያዩ መረዳቶች የሚታዩት ለምንድን ነው?

በመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችና በአምልኮ ልምምዶች ውስጥ ያሉ ልዩነቶችን እንዴት መያዝ አለብን?

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 1-2 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 3-8 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 9-28)

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 1

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 2

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 3

የጴንጤቆስጤ ሥነ መለኮት ታሪክ

የጰንጠቆስጤና የአንዳንድ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ዋና ትምህርቶች ምን ምን ናቸው?

ከካሪዝማቲክ ትምህርት ለቤተ ክርስቲያን የተረፉ መልካም ውጤቶች

በካሪዝማቲክ የሥነ መለኮት ትምህርት የሚገኙ ሚዛናዊ ያልሆኑ ነገሮች

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል አንድ)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሁለት)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሦስት)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 1)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 2)

በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና ልሳን በመናገር መካከል ያሉ ግንኙነቶች

የመንፈስ ቅዱስ አማኞችን ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ የመምራት አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ እንድናመልክ ይረዳናል

መንፈስ ቅዱስ የክርስቲያኖች ሕይወት ኢየሱስን እንዲመስል የሚሰጠው አገልግሎት

ሰይጣንን ድል የማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

ስለ መንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች መግቢያ

መንፈሳዊ ስጦታ ምንድን ነው?

መንፈሳዊ ስጦታ (ሮሜ 12፡1-8)

መንፈሳዊ ስጦታ (ኤፌሶን 4፡1-16 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ጴጥሮስ 4፡7-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡1-3)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡4-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡12-31 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 13)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡1-19)

መንፈሳዊ ስጦታዎችና የማያምኑ ሰዎች (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡20-40)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 1)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 2) የተለያዩ ዓይነት ልሳናት አሉን?

በቤተ ክርስቱያን ውስጥ ስለሚመጣው ትንቢት ተጨማሪ አሳቦች

ትንቢት ምንድን ነው? ነቢይስ?

የትንቢት ስጦታ ምንድን ነው?

የእውነተኛና ሐሰተኛ ነቢያት ንጽጽር

የትንቢት ስጦታን ለመጠቀም መመሪያዎቹ ምን ምን ናቸው?

የመፈወስና ተአምራትን የማድረግ ስጦታዎች

የብሉይ ኪዳን ተአምራትና አዲሱን ዘመን በተስፋ መመልከት

ተአምራትና ፈውሶች በአዲስ ኪዳን

እግዚአብሔር ፈውስን የሚሰጥባቸው የተለያዩ አሠራሮች

ስለ ተአምራትና ፈውሶች የሚሰጡ የተሳሳቱ አሳቦች

የመንፈሳዊ ስጦታዎች ትምህርት ማጠቃለያ

በመንፈስ ቅዱስ መሞላት

የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምንድን ነው?

ከኤፌ 5፡18-20 በመንፈስ ቅዱስ ስላ መሞላት ምን ልንመለከት እንችላለን?

በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ማረጋገጫዎች

በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት የሚቀርቡ ቅድመ ሁኔታዎች

በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና መንፈሳዊ ብስለት

የመጀመሪያው የመንፈስ ቅዱስ ዋና ሥራ፡- ዘላለማዊው አምላክ በውስጣችን መኖሩ

የመንፈስ ቅዱስ ሁለተኛ ዋና ተግባሩ፡- ወደ ኢየሱስ ማመልከትና እርሱን እንድንመስል ማድረግ።

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች ክለሳ

በዚህ የትመማ መጽሐፍ የመንፈስ ቅዱስን ሥነ መለኮት እናጠናለን። ሥነ መለኮትን ስለ ማጥናት ስንነጋገር ስለ ሁለት ነገሮች መናገራችን ነው። 

አንደኛ፥ ስለ አንድ ርእሰ ጉዳይ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያሉ እውነቶችን በሙሉ በአንድነት ለማሰባሰብ መፈለጋችንን ያመለክታል። መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው እውነተችን (ርእሰ-ጉዳዮችን) በየመስካቸው ከፋፍሎ በሚያስቀምጥ መንገድ አይደለም። ይልቁንም መጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን፥ ትረካዎችን ደብዳቤዎችን የያዘ ሲሆን እነዚህም እግዚአብሔር ምን እንድናውቅ እንደሚፈልግ ያስተምሩናል። በእያንዳንዱ ትረካ ወይም ደብዳቤ ውስጥ በርካታ እውነቶች ወይም ርእሰ ጉዳዮች ተጠቅሰዋል። ስለ እግዚአብሔር፥ ስለ ድነት (ድነት (ደኅንነት)) ወይም ስለ መንፈስ ቅዱስ ያሉትን እውነቶች በሙሉ በአንድ ስፍራ እጢቃልሉ የያዘ ክፍል በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የለም። ስለሆነም፥ ስለ መንፈስ ቅዱስ ሥነ መለኮት እናጠናለን ስንል መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የሚያስተምራቸውን እውነቶች በአንድነት በማድረግ በሥርዓት እናጠናቸዋለን ማለታችን ነው። 

ሁለተኛ፥ ሥነ መለኮት እናጠናለን ስንል የመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችን እንዴት እንደምንረጻ እንመለከታለን ማለታችን ነው። የሥነ መለኮት ትምህርትን የመረዳታችን መጠን ሁልጊዜ ውሱን ነው። መረዳቶቻችንን ሁልጊዜ ከመጽሐፍ ቅዱስ ሥልጣን ያነሱ አድርገን ልንመለከት ይገባል። ሥልጣን ያለው መጽሐፍ ቅዱስ እንጂ የእኛ መረዳት አይደለም። የመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችን በሙላት በትክክል የመረዳት ችሎታ ማናችንም የለንም። እውነትን የማወቃችን ችሉታ ውስን የሆነው በባሕላዊ መረዳሞቻችን፥ በማንነታችን ወይም በቤተ ክርስቲያን ልማዳችን እንኳ ተጽእኖ ስለሚደርስበት ነው። የመንፈስ ቅዱስን ሥነ መለኮት እናጠናለን ስንል የእግዚአብሔር ቃል ስለ መንፈስ ቅዱስ ምን እንደሚያስተምረን ያለንን መረጻት ሥርዓት ባለው የአጠናን ዘዴ እንመለከተዋለን ማለታችን ነው። 

ስለ እግዚአብሔርና ስለ ቃሉ ያለን መረዳት ውሱንና ከፊል እንደሆነ ሁልጊዜ መዘንጋት የለብንም። ቢሆንም እንኳ መረዳታችንን ለማሳደግ የእግዚአብሔርን ቃል ያለማቋረጥ ማጥናት ኃላፊነታችን ነው። ይሁንና፥ ከእኛ በተለየ ሁኔታ እውነትን ከሚረዱ ሌሎች ክርስቲያኖች የአመለካከት አቅጣጫ ሆነን ለማየትም ጥረት ማድረግ ይገባናል። በዚህ የጥናት መጽሐፍ የመጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ምን እንደሚያስተምር እንመለከታለን። በተጨማሪ ሌሎች ክርስቲያኖች በዚህ ጉዳይ ላይ ያላቸውን የተለየ አቋም በመመልከት ያንን አቋም ለምን እንደምንቀበል ወይም እንደማንቀበልም እንገልጻለን። ይህንን የምናደርገው በፍቅርና በዚህ ጉዳይ ላይ ለሁሉም ነገር መልስ እንደ ሌለን በማመንም ጭምር ነው። ትልቁ ፍላህታችን በአንድነት ወደ መጽሐፍ ቅዱስ በመመልከት «መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ምን ያስተምረናል?» የሚለውን ጥያቄ እንድናነሣ ነው። 

ጥያቄ፡- እንደ መንፈስ ቅዱስ ያሉ ጉዳዮችን ማጥናት አስፈላጊ ነው ብለህ የምታስበው ለምንድን ነው?

ምንጭ፡- “የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ”፣ በቲም ፌሎስ ተጽፎ፣ በጌቱ ግዛው የተተረጎመ እና በኤስ አይ ኤም ጽሑፍ ክፍል የተዘጋጀ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

ስለ መንፈስ ቅዱስ ለምን እናጠናለን? መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የምንረዳበት ምንጭ

የጌታ ጸጋ ከእርስዎ ጋር ይሁን፤ ሀሳብዎን ለመስማት ዝግጁ ነን።

Discover more from የሕይወት እንጀራ አገልግሎት

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading