የሕይወት እንጀራ

የብሉይ ኪዳን ነቢያት መሢሑ የሚመጣበትን ወቅትና የመንፈስ ቅዱስ አገልግሉት የሚለወጥበትን ጊዜ እስቀድመው አመልክተው ነበር

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

መግቢያ

ስለ መንፈስ ቅዱስ ለምን እናጠናለን?

ሥነ መለኮት ምንድን ነው?

መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የምንረዳበት ምንጭ

መንፈስ ቅዱስን ማወቅ

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ስፍራ

የመንፈስ ቅዱስ ዋና ኃላፊነቶች ምንና ምን ናቸው?

የመንፈስ ቅዱስ ስሞች

የመንፈስ ቅዱስ ተምሳሌቶች

እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ማን ነው?

መንፈስ ቅዱስ፤ ሦስተኛው የሥላሴ አካል

መጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ አምላክ መሆኑን ያሳየናልን?

መንፈስ ቅዱስ በብሉይ ኪዳን

የእግዚአብሔርን ሕዝብ ይመሩ ዘንድ መሪዎችን ብቁ በማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል እንዲጽፉ በመምራት የሰጠው አገልግሎት

የብሉይ ኪዳን ነቢያት መሢሑ የሚመጣበትን ወቅትና የመንፈስ ቅዱስ አገልግሉት የሚለወጥበትን ጊዜ እስቀድመው አመልክተው ነበር

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት በወንጌላት

መንፈስ ቅዱስ በጌታ ኢየሱስ ሕይወትና አገልግሎት ውስጥ

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የሰጠው ትምህርት፤ ክፍል 1

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ያስተማረው ትምህርት፤ ክፍል 2

ክርስቲያኖች እንደ መንፈስ ቅዱስ ባሉ መሠረታዊ የክርስትና አስተምህሮዎች ላይ ባላቸው አመለካከት ልዩነት የሚያሳዩት ለምንድን ነው?

መንፈስ ቅዱስን በተመለከተ የተለያዩ መረዳቶች የሚታዩት ለምንድን ነው?

በመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችና በአምልኮ ልምምዶች ውስጥ ያሉ ልዩነቶችን እንዴት መያዝ አለብን?

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 1-2 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 3-8 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 9-28)

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 1

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 2

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 3

የጴንጤቆስጤ ሥነ መለኮት ታሪክ

የጰንጠቆስጤና የአንዳንድ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ዋና ትምህርቶች ምን ምን ናቸው?

ከካሪዝማቲክ ትምህርት ለቤተ ክርስቲያን የተረፉ መልካም ውጤቶች

በካሪዝማቲክ የሥነ መለኮት ትምህርት የሚገኙ ሚዛናዊ ያልሆኑ ነገሮች

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል አንድ)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሁለት)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሦስት)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 1)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 2)

በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና ልሳን በመናገር መካከል ያሉ ግንኙነቶች

የመንፈስ ቅዱስ አማኞችን ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ የመምራት አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ እንድናመልክ ይረዳናል

መንፈስ ቅዱስ የክርስቲያኖች ሕይወት ኢየሱስን እንዲመስል የሚሰጠው አገልግሎት

ሰይጣንን ድል የማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

ስለ መንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች መግቢያ

መንፈሳዊ ስጦታ ምንድን ነው?

መንፈሳዊ ስጦታ (ሮሜ 12፡1-8)

መንፈሳዊ ስጦታ (ኤፌሶን 4፡1-16 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ጴጥሮስ 4፡7-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡1-3)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡4-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡12-31 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 13)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡1-19)

መንፈሳዊ ስጦታዎችና የማያምኑ ሰዎች (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡20-40)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 1)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 2) የተለያዩ ዓይነት ልሳናት አሉን?

በቤተ ክርስቱያን ውስጥ ስለሚመጣው ትንቢት ተጨማሪ አሳቦች

ትንቢት ምንድን ነው? ነቢይስ?

የትንቢት ስጦታ ምንድን ነው?

የእውነተኛና ሐሰተኛ ነቢያት ንጽጽር

የትንቢት ስጦታን ለመጠቀም መመሪያዎቹ ምን ምን ናቸው?

የመፈወስና ተአምራትን የማድረግ ስጦታዎች

የብሉይ ኪዳን ተአምራትና አዲሱን ዘመን በተስፋ መመልከት

ተአምራትና ፈውሶች በአዲስ ኪዳን

እግዚአብሔር ፈውስን የሚሰጥባቸው የተለያዩ አሠራሮች

ስለ ተአምራትና ፈውሶች የሚሰጡ የተሳሳቱ አሳቦች

የመንፈሳዊ ስጦታዎች ትምህርት ማጠቃለያ

በመንፈስ ቅዱስ መሞላት

የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምንድን ነው?

ከኤፌ 5፡18-20 በመንፈስ ቅዱስ ስላ መሞላት ምን ልንመለከት እንችላለን?

በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ማረጋገጫዎች

በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት የሚቀርቡ ቅድመ ሁኔታዎች

በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና መንፈሳዊ ብስለት

የመጀመሪያው የመንፈስ ቅዱስ ዋና ሥራ፡- ዘላለማዊው አምላክ በውስጣችን መኖሩ

የመንፈስ ቅዱስ ሁለተኛ ዋና ተግባሩ፡- ወደ ኢየሱስ ማመልከትና እርሱን እንድንመስል ማድረግ።

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች ክለሳ

ጥያቄ፡ ኢሳ 1-5፤ 42፡1-4፤ 61፡1-3 አንብብ። ሀ) እነዚህ ጥቅሶች በሚመጣው መሣሕ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት ምን እንደሆነ ያስተምሩናል? ለ) ይህ አገልግሎት በኢየሱስ የተፈጸመው እንዴት ነበር? ኢሳ 44፡3፤ 59፡21 ሕዝ 11፡9፤ 36፡27 ና 37፡14፤ 39፡29፤ ኢዩ፤ 2፡28-29። ሐ) እዚህ ጥቅሶች ስለ መጨረሻዎቹ ቀናት የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት ምን ያላተምሩናል? 

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት በብሉይ ኪዳን ዘመን ታላቅ እንደነበር ሁሉ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት የሚለወጥበት አዲስ ዘመን እንደሚመጣም ነቢያት ተገንዝበው ነበር። በመጀመሪያ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ልዩ ግንኙነት ያለው ሰው እንደሚመጣ ነበር። ይህ ሰው ከዳዊት ዘር የሚመጣው ንጉሥ መሢሑ ነበር (ኢሳ. 11፡23 42፡1)። ላለ መሢሑ በተነገረበት በእነዚህ የብሉይ ኪዳን ትንቢቶች ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት ተቀዳሚ ትኩረት እግዚአብሔርን በሚያስከበር መንገድ የእግዚአብሔርን ሕዝብ እንዲመራ መሢሑን በማስቻል ላይ ነበር። ከሌሎች መሪዎች በተለየ መንገድ በጥበብና በእውቀት የተሞላ ሆኖ ጌታን በመፍራት ይኖራል። በምድር ላይ ጽድቅን ያመጣል። የታሠሩትን ነፃ ሚያወጣና ልባቸው የተሠበረባቸውን የሚፈውስ የምሥራች ቃል ይሰብካል። 

ሁለተኛ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት ለሁሉም የሚዳረስ ስለመሆኑ ነበር። በእግዚአብሔር ሕዝብ መካከል ያለውን በእግዚአብሔር ላይ የማመጽ ዝንባሌ ማለትም የድንጋዩን ልብ ይወለድና በሚታዘዝ ልብ ይቀይራል። መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል በሕዝቡ ፊት ያላማቋረጥ እንዲገኝ ያደርጋል። መንፈስ ቅዱስ ልዩ አገልግሎት በሚሰጡ በጥቂት ነቢያትና የፖለቲካ መሪዎች ላይ ብቻ መሆኑ ይቀርና የዕድሜና የዘር ልዩነት ሳያደርግ አሕዛብም ሲሆኑ አይሁድ በሁሉም የእግዚአብሔር ሕዝቦች ላይ ይወርዳል። በእነዚህ ምርጥ ሰዎች ላይ ለተወሰነ ጊዜ ይወርድ እንደነበረው ሳይሆን መንፈስ ቅዱስ በእግዚአብሔር ሰዎች ሕይወት ውስጥ ይኖራል። የትንቢት ስጦታ ለፖለቲካ መሪዎች ወይም ነቢያት ብቻ የሚታደል መሆኑ ቀርቶ ይህ ለመንፈስ ቅዱስ ህውና ምልክት (ማስረጃ ) የሆነው ስጦታ ለሰዎች ሁሉ ይሰጣል። 

ጥያቄ፡- መንፈስ ቅዱስ በብሉይ ኪዳን ዘመን የሰጠውን አገልግሎት ክልስ። ሀ) በዚያ ዘመን የመንፈስ ቅዱስ ተቀዳሚ ሚና ምን ይመስል ነበር? ላ) ዛሬ መንፈስ ቅዱስ ከሚሠራባቸው መንገዶች ጋር ምን ተመሳሳይነት [አላው? ሐ) ዛሬ መንፈስ ቅዱስ ከሚሠራባቸው መንገዶች ጋር ልዩነቶቹስ ምን ምን ናቸው? መ) ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ስላለን ንኙነት በብሉይ ኪዳን ከነበረው አገልግሎቱ ልንማራቸው የምንችላቸው ነገሮች ምን ምን ናቸው? 

ብዙ ጊዜ ስለ መንፈስ ቅዱስ ሥራ ስናስብ አንዳንድ ጊዜ ከሚያደርጋቸው ድንቅ ነገሮች አኳያ ብቻ እንመለከተዋለን፤ ወይም በአንድ የአገልግሎት ገጽታው ላይ ብቻ በማተኮር ስለ መንፈስ ቅዱስ ያለን ሥነ መለኮታዊ መረዳት ሚዛናዊነትን ያጣል። መንፈስ ቅዱስ ግን መጠነ-ሰፊ በሆኑ ጉዳዮች ውስጥ ይሠራል። ከእዚህም ብዙዎቹ የማይታዩና በሚሩጸሙበት ጊዜ እንኳ የማናስተውላቸው ናቸው። የሕይውት መገኝትም ሆነ ዘላቂነቱ በመንፈስ ቅዱስ ላይ የተደገፈ ነው። እግዚአብሔር ሕይወታችንን የሚያስተምርበትም ሆነ የሚመራበት አገልግሎት በመንፈስ ቅዱስ ላይ የተመሠረተ ነው። በብሉይ ኪዳን የምንመለከተው የመንፈስ ቅዱስ ተቀጻሚ አገልግሎት ቀን እግዚአብሔር የመረጣቸው መሪዎች ሕዝቡን እንዲመሩ ማድረግ ነበር። ይህ ችሎታ አንዳንድ ጊዜ እንደ ሳምሶን ብርታትና እንደ ሳኦል ትንቢት ተአምራዊ ተግባራትን ያካተተ ቢሆንም ብዙ ጊዜ ግን የመንፈስ ቅዱስ ህልውና የሚታየው በመሪዎች ጥበባዊ አመራር፥ ከጠላት የመታደግና ሕዝቡን በእግዚአብሔር ፊት የተቀደሰ ኑሮ እንዲኖሩ በማስቻል በማድረግ) ችሎታቸው ውስጥ ነው። 

የብሉይ ኪዳን ዘመን ሲፈጸም እግዚአብሔር ለሕዝቡ አዲስ ሥራን ሲሠራ መንፈስ ቅዱስ በእግዚአብሔር ሕዝብ መካከል የሠራበትን መንገድ እንደሚለውጥ ተነግሮናል። አገልግሎቱ ምን ይመስል ነበር? በብሉይ ኪዳንና በአዲስ ኪዳን ዘመናት መካከል ያለው ልዩነት ምን ይሆናል? በሚቀጥለው ሳምንት መንፈስ ቅዱስ በወንጌላት ውስጥ ስለ ሰጠው አገልግሎት በተለይ ደግሞ በኢየሱስ ሕይወትና ትምህርት ውስጥ ስለነበረው አገልግሎት እንመለከታለን።

ምንጭ፡- “የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ”፣ በቲም ፌሎስ ተጽፎ፣ በጌቱ ግዛው የተተረጎመ እና በኤስ አይ ኤም ጽሑፍ ክፍል የተዘጋጀ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

መንፈስ ቅዱስ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል እንዲጽፉ በመምራት የሰጠው አገልግሎት የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት በወንጌላት

የጌታ ጸጋ ከእርስዎ ጋር ይሁን፤ ሀሳብዎን ለመስማት ዝግጁ ነን።

Discover more from የሕይወት እንጀራ

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading