የሕይወት እንጀራ

በመንፈስ ቅዱስ መሞላት

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

መግቢያ

ስለ መንፈስ ቅዱስ ለምን እናጠናለን?

ሥነ መለኮት ምንድን ነው?

መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የምንረዳበት ምንጭ

መንፈስ ቅዱስን ማወቅ

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ስፍራ

የመንፈስ ቅዱስ ዋና ኃላፊነቶች ምንና ምን ናቸው?

የመንፈስ ቅዱስ ስሞች

የመንፈስ ቅዱስ ተምሳሌቶች

እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ማን ነው?

መንፈስ ቅዱስ፤ ሦስተኛው የሥላሴ አካል

መጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ አምላክ መሆኑን ያሳየናልን?

መንፈስ ቅዱስ በብሉይ ኪዳን

የእግዚአብሔርን ሕዝብ ይመሩ ዘንድ መሪዎችን ብቁ በማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል እንዲጽፉ በመምራት የሰጠው አገልግሎት

የብሉይ ኪዳን ነቢያት መሢሑ የሚመጣበትን ወቅትና የመንፈስ ቅዱስ አገልግሉት የሚለወጥበትን ጊዜ እስቀድመው አመልክተው ነበር

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት በወንጌላት

መንፈስ ቅዱስ በጌታ ኢየሱስ ሕይወትና አገልግሎት ውስጥ

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የሰጠው ትምህርት፤ ክፍል 1

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ያስተማረው ትምህርት፤ ክፍል 2

ክርስቲያኖች እንደ መንፈስ ቅዱስ ባሉ መሠረታዊ የክርስትና አስተምህሮዎች ላይ ባላቸው አመለካከት ልዩነት የሚያሳዩት ለምንድን ነው?

መንፈስ ቅዱስን በተመለከተ የተለያዩ መረዳቶች የሚታዩት ለምንድን ነው?

በመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችና በአምልኮ ልምምዶች ውስጥ ያሉ ልዩነቶችን እንዴት መያዝ አለብን?

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 1-2 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 3-8 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 9-28)

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 1

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 2

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 3

የጴንጤቆስጤ ሥነ መለኮት ታሪክ

የጰንጠቆስጤና የአንዳንድ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ዋና ትምህርቶች ምን ምን ናቸው?

ከካሪዝማቲክ ትምህርት ለቤተ ክርስቲያን የተረፉ መልካም ውጤቶች

በካሪዝማቲክ የሥነ መለኮት ትምህርት የሚገኙ ሚዛናዊ ያልሆኑ ነገሮች

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል አንድ)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሁለት)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሦስት)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 1)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 2)

በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና ልሳን በመናገር መካከል ያሉ ግንኙነቶች

የመንፈስ ቅዱስ አማኞችን ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ የመምራት አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ እንድናመልክ ይረዳናል

መንፈስ ቅዱስ የክርስቲያኖች ሕይወት ኢየሱስን እንዲመስል የሚሰጠው አገልግሎት

ሰይጣንን ድል የማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

ስለ መንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች መግቢያ

መንፈሳዊ ስጦታ ምንድን ነው?

መንፈሳዊ ስጦታ (ሮሜ 12፡1-8)

መንፈሳዊ ስጦታ (ኤፌሶን 4፡1-16 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ጴጥሮስ 4፡7-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡1-3)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡4-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡12-31 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 13)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡1-19)

መንፈሳዊ ስጦታዎችና የማያምኑ ሰዎች (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡20-40)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 1)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 2) የተለያዩ ዓይነት ልሳናት አሉን?

በቤተ ክርስቱያን ውስጥ ስለሚመጣው ትንቢት ተጨማሪ አሳቦች

ትንቢት ምንድን ነው? ነቢይስ?

የትንቢት ስጦታ ምንድን ነው?

የእውነተኛና ሐሰተኛ ነቢያት ንጽጽር

የትንቢት ስጦታን ለመጠቀም መመሪያዎቹ ምን ምን ናቸው?

የመፈወስና ተአምራትን የማድረግ ስጦታዎች

የብሉይ ኪዳን ተአምራትና አዲሱን ዘመን በተስፋ መመልከት

ተአምራትና ፈውሶች በአዲስ ኪዳን

እግዚአብሔር ፈውስን የሚሰጥባቸው የተለያዩ አሠራሮች

ስለ ተአምራትና ፈውሶች የሚሰጡ የተሳሳቱ አሳቦች

የመንፈሳዊ ስጦታዎች ትምህርት ማጠቃለያ

በመንፈስ ቅዱስ መሞላት

የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምንድን ነው?

ከኤፌ 5፡18-20 በመንፈስ ቅዱስ ስላ መሞላት ምን ልንመለከት እንችላለን?

በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ማረጋገጫዎች

በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት የሚቀርቡ ቅድመ ሁኔታዎች

በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና መንፈሳዊ ብስለት

የመጀመሪያው የመንፈስ ቅዱስ ዋና ሥራ፡- ዘላለማዊው አምላክ በውስጣችን መኖሩ

የመንፈስ ቅዱስ ሁለተኛ ዋና ተግባሩ፡- ወደ ኢየሱስ ማመልከትና እርሱን እንድንመስል ማድረግ።

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች ክለሳ

«ጌታ ሆይ፥ ሕይወቴ እጅግ ደርቋል። ከአንተ እጅግ እንደራቅሁ ይሰማኛል። እባክህን ድንጋይ ልቤን ለውጥ። የአንተ ህልውና እንዲሰማኝ እድርገኝ። ድምፅህን እንድሰማ እርዳኝ» እያልክ በመጸለይ ላይ ሳለህ ልብህ በድንገት እንግዳ በሆነ ሁኔታ ይሟሟቃል። እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ባለህበት ክፍል እንዳለ ይሰማሃል። ልብህን ደስታ ይሞላውና እግዚአብሔርን ማመስገን ትጀምራለህ። 

«ጌታ ሆይ፥ በሕይወቴ ኃጢአት አለ። የምችለውን ሁሉ ላደርግ ብጥር እንኳ ላሸንፈው አልቻልኩም። እባክህን ይህን ኃጢአት እንዳሽንፍ ኃይልህን ስጠኝ» ብለህ ከጸላይክ ጥቂት ጊዜያት ካለፉ በኋላ የሚያስቸግርህ ኃጢአት ክአንተ መወገዱን ታያለህ። 

«ጌታ ሆይ፥ በቤተ ክርስቲያን እንድሰብክ ተጠይቄአለሁ። ለማጥናትና ራሴን ለማሰናዳት ሞክሬአለሁ ነገር ግን እንደተዘጋጀሁ አይሰማኝም። ምን ብዩ እንደምናገር እንኳ እንደማላውቅ ነው የሚሰማኝ። ጌታ ሆይ፥ ቃላትን ለመደጋገም አልፈልግም። ነገር ግን የአንተን መልእክት ለማስተላለፍ እሻለሁ። ጌታ ሆይ፥ አሁን ለመናገር እቆማለሁ። እባክህን በእኔ ውስጥ ተናገር» ብለህ በመጸለይ በሕዝቡ ፊት ትቆማለህ። በድንገት ፍርሃትህ ይሸሻል። አስተሳሰብህ ግልጽ ይሆናል። ከዚህ ቀደም አስበሃቸው የማታውቃቸው ቃሎች፥ አሳቦችና መግለጫዎች በአእምሮህ ውስጥ ይፈስሳሉ። ቃሎችህ ልባቸውን እየሰነጠቁ ሲገቡ ከአድማጮችህ ፊት ልታነብብ ትችላለህ። ሰዎች ንስሐ ገቡ። ሌሎች ጌታን ለመከተል ወሰኑ። 

ጥያቄ፡- ሀ) እላይ የተጠቀሱትን የሚመስሉ ነገሮች የተለማመድከው (እንዴት ነው? ለ) የሚከተሉትን ጥቅሶች ተመልከት። ዘፀአ 33፡18-23፤ መዝ| (42)፡1-2፤ ኤር. 29፡12-13፤ ፊልጵ. 3፡1-11። የእነዚህ ሰዎች ጸሎቶች ወይም ፍላጐቶች ምን ነበሩ? ሐ) እዚህ ጸሎቶች ልንጸልያቸው ከምንችላቸው ታላላቅ ጸሎቶች አንዱ ዓይነት የሚሆኑት ለምንድን ነው? 

ክርስቲያኖች ዛሬ የሚያስፈልጋቸው ብቸኛ ታላቅ ነገር በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ሥር የሆነ ሕይወትን መኖር ነው። ሕይወታቸው ኃይል አልባ የሆኑ በርካታ ክርስቲያኖች አሉ። በኃጢአት ተሸንፈው ይኖራሉ። ከእግዚአብሔር ጋር ያላቸው ግንኙነት ሰልምድ የሚፈጸም ሥርዓት ብቻ ነው። የእግዚአብሔርን ቃል መስማት አቁመዋል። ሰልባቸው ህልውናው አይሰማቸውም። በየሳምንቱ የሚሰብኩት ስብከታቸው ግን ኃይል አልባ ስለሆነ የሰዎችን ሕይወት ፈጽሞ መለወጥ የማይችል የሆነባቸው ብዙ መሪዎች አሉ። እነርሱም ወጥ የሆነ፥ የመንፈስ ቅዱስ ፍሬ የሚታይበትና (ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ በጐነት፥ እምነት፥ የዋህነት፥ ቸርነት ትዕግሥት፥ ራስን መግዛት) ሰዎች በሕይወታቸው ያለውን ለውጥ የሚገነዘቡበት ሕይወት እንዲኖራቸው በመንፈስ ቅዱስ መሞላት ያስፈልጋቸዋል። 

ላለፉት ሁለት ሳምንታት የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎችን ስናጠና ቆይተናል። እነዚህ መንፈሳዊ ስጦታዎች አስፈላጊ ቢሆኑም እንኳ በመጨረሻ በየዕለቱ እናንተም ሆናችሁ እኔ እንዴት እንደምንኖር በሕይወታችን ተጽዕኖ የሚያደርግ ከሁሉ የላቀው የመንፈስ ቅዱስ ሥራ «በመንፈስ ቅዱስ መሞላት ነው።» እግዚአብሔርን ደስ በሚያሰኝ መንገድ እንድንኖርና እንድናገለግል የሚያደርገን የመንፈስ ቅዱስ እገልግሎት ይህ ነው። በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ሥር በምንመላለስበት ወቅት በየዕለቱ በመንፈሳዊ ብስለት እያደግንና ኢየሱስን እየመሰልን እንሄዳለን። በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ሥር ሆነን እንደ ኢየሱስ እናስባለን፥ እንደ ኢየሱስ እንኖራለን፥ ለእርሱ ክብር የእርሱን ተግባራት እንፈጽማለን። 

ጥያቄ፡- በመንፈስ ቅዱስ የተሞሉ ክርስቲያኖች በቤተ ክርስቲያኖቻችን ውስጥ መኖራቸው ጠቃሚ የሚሆነው ለምንድን ነው? 

በክርስትና ታሪክ ሁሉ ውስጥ ከማንኛውም ተራ ክርስቲያኖች የተለዩ ክርስቲያኖች ነበሩ። ለእግዚአብሔር ያላቸው ቅናት እጅግ የሚቀጣጠል ከመሆኑ የተነሣ ሕይወታቸው እግዚአብሔርን የበለጠ ለማወቅ የሚያጓጓ ነው። ወይም በእግዚአብሔር ላይ የነበራቸው እምነት ታላቅ ስለሆነ ለእግዚአብሔር አስደናቂ ነገሮችን ለማድረግ የሚችሉ ነበሩ። አንዳንዶቹ እጅግ ልዩ ከመሆናቸው የተነሣ እነርሱ ባሉበት መሆን በእግዚአብሔር ፊት እንደ መገኘት ነበር። እነዚህን ክርስቲያኖች ልዩ ያደረጋቸው ምንድን ነው? ይህ የሕይወት ደረጃ ለተመረጡ ጥቂቶች ብቻ የተሰጠ ነውን? እንደ እነርሱ ለመሆን ምን ማድረግ አለብን? 

የእነዚህን ታላላቅ ክርስቲያኖች ሕይወት ስናጠና ሁላቸውም በሕይወታቸው ሰቆቃ የነበረባቸው ወቅት ነበር። ይህ ጊዜ እግዚአብሔርን በዚያ ሁኔታ ውስጥ እጅግ የፈለጉበትና እግዚአብሔርም በእስደናቂ መንገድ የመለሰላቸው ጊዜ ነበር። እንደዚህ ዓይነቱ ልምምድ ስእነዚህ ትላልቅ ቅዱሳን ሕይወት በተደጋጋሚ በመከሰቱ በመንፈሳዊ ሕይወታቸው የሚታየው እድገት ከአንድ ኮረብታ ወደ ሌላ ከፍተኛ ኮረብታ የመዝለል ያህል ነበር። እነዚህ የቀድሞ ትላልቅ ክርስቲያኖች ከእግዚአብሔር ጋር የነበራቸውን ግንኙነት ለመግለጽ በተለያዩ ቃላት ተጠቅመዋል። አንዳንዶች በመንፈስ ቅዱስ መጠመቅ ብለውታል። ሌሎች በመንፈስ ቅዱስ መቀባት ብለውታል። አሁንም ሌሎች የጠለቀ ሕይወት ወይም ደግሞ በረከት ብለውታል። ወይም በመንፈስ ቅዱስ መሞላት የሚሉም አሉ። ስለ ልምምዶች ምንነት የተሳሳተ መረዳትን ሊሰጡ የሚችሉ ቢሆኑም፥ ልምምዳቸውን ለመግለጽ የተጠቀሙባቸው ቃላት በራሳቸው ጠቃሚ አይደሉም። ዋናው አስፈላጊ ነገር ልምምዳቸው ነው። የእግዚአብሔር ፍላጐት ሁላችንም ይህ ልዩ የሆነ ጥልቅ ግንኙነት ከእርሱ ጋር እንዲኖረን ነው። አጥብቀን ከልባችን ብንፈልግ እንደምናገኘው ተስፋ ሰጥቶናል (ኤር 29፡12-13)። በሕይወታችን የእግዚአብሔርን ክብር ከሁሉ በላቀ መንገድ ለማየት ከፈለግን (ዘፀአ 33፡18-23) እግዚአብሔር እራሱን ይገልጥልናል። እግዚአብሔር በጥልቀት እንድንላማመድ ያላስቻለን ነገር እግዚአብሔር ሌሎች ምርጦች ስላሉትና እኛን በተመሳሳይ መንገድ ሊባርከን ስለማይፈልግ ሳይሆን ነገር ግን የእነርሱን ያህል ጥረት ስለማናደርግ ነው። እግዚአብሔር ማንነቱን በጥልቀት የሚገልጸው በሙሉ ልባቸው ለሚፈልጉት ነው። ክርስቲያን ከእግዚአብሔር ጋር የሚያድግ ኅብረት እንዲለማመዱ በመጀመሪያ ፍላጐት እንዲኖረው ከማድረግ ጀምሮ በመርዳት የሚሠራ መንፈስ ቅዱስ ነው።

ምንጭ፡- “የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ”፣ በቲም ፌሎስ ተጽፎ፣ በጌቱ ግዛው የተተረጎመ እና በኤስ አይ ኤም ጽሑፍ ክፍል የተዘጋጀ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

የመንፈሳዊ ስጦታዎች ትምህርት ማጠቃለያ የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምንድን ነው?

የጌታ ጸጋ ከእርስዎ ጋር ይሁን፤ ሀሳብዎን ለመስማት ዝግጁ ነን።

Discover more from የሕይወት እንጀራ

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading