የሕይወት እንጀራ

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት በወንጌላት

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

መግቢያ

ስለ መንፈስ ቅዱስ ለምን እናጠናለን?

ሥነ መለኮት ምንድን ነው?

መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የምንረዳበት ምንጭ

መንፈስ ቅዱስን ማወቅ

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ስፍራ

የመንፈስ ቅዱስ ዋና ኃላፊነቶች ምንና ምን ናቸው?

የመንፈስ ቅዱስ ስሞች

የመንፈስ ቅዱስ ተምሳሌቶች

እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ማን ነው?

መንፈስ ቅዱስ፤ ሦስተኛው የሥላሴ አካል

መጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ አምላክ መሆኑን ያሳየናልን?

መንፈስ ቅዱስ በብሉይ ኪዳን

የእግዚአብሔርን ሕዝብ ይመሩ ዘንድ መሪዎችን ብቁ በማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል እንዲጽፉ በመምራት የሰጠው አገልግሎት

የብሉይ ኪዳን ነቢያት መሢሑ የሚመጣበትን ወቅትና የመንፈስ ቅዱስ አገልግሉት የሚለወጥበትን ጊዜ እስቀድመው አመልክተው ነበር

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት በወንጌላት

መንፈስ ቅዱስ በጌታ ኢየሱስ ሕይወትና አገልግሎት ውስጥ

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የሰጠው ትምህርት፤ ክፍል 1

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ያስተማረው ትምህርት፤ ክፍል 2

ክርስቲያኖች እንደ መንፈስ ቅዱስ ባሉ መሠረታዊ የክርስትና አስተምህሮዎች ላይ ባላቸው አመለካከት ልዩነት የሚያሳዩት ለምንድን ነው?

መንፈስ ቅዱስን በተመለከተ የተለያዩ መረዳቶች የሚታዩት ለምንድን ነው?

በመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችና በአምልኮ ልምምዶች ውስጥ ያሉ ልዩነቶችን እንዴት መያዝ አለብን?

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 1-2 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 3-8 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 9-28)

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 1

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 2

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 3

የጴንጤቆስጤ ሥነ መለኮት ታሪክ

የጰንጠቆስጤና የአንዳንድ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ዋና ትምህርቶች ምን ምን ናቸው?

ከካሪዝማቲክ ትምህርት ለቤተ ክርስቲያን የተረፉ መልካም ውጤቶች

በካሪዝማቲክ የሥነ መለኮት ትምህርት የሚገኙ ሚዛናዊ ያልሆኑ ነገሮች

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል አንድ)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሁለት)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሦስት)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 1)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 2)

በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና ልሳን በመናገር መካከል ያሉ ግንኙነቶች

የመንፈስ ቅዱስ አማኞችን ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ የመምራት አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ እንድናመልክ ይረዳናል

መንፈስ ቅዱስ የክርስቲያኖች ሕይወት ኢየሱስን እንዲመስል የሚሰጠው አገልግሎት

ሰይጣንን ድል የማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

ስለ መንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች መግቢያ

መንፈሳዊ ስጦታ ምንድን ነው?

መንፈሳዊ ስጦታ (ሮሜ 12፡1-8)

መንፈሳዊ ስጦታ (ኤፌሶን 4፡1-16 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ጴጥሮስ 4፡7-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡1-3)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡4-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡12-31 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 13)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡1-19)

መንፈሳዊ ስጦታዎችና የማያምኑ ሰዎች (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡20-40)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 1)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 2) የተለያዩ ዓይነት ልሳናት አሉን?

በቤተ ክርስቱያን ውስጥ ስለሚመጣው ትንቢት ተጨማሪ አሳቦች

ትንቢት ምንድን ነው? ነቢይስ?

የትንቢት ስጦታ ምንድን ነው?

የእውነተኛና ሐሰተኛ ነቢያት ንጽጽር

የትንቢት ስጦታን ለመጠቀም መመሪያዎቹ ምን ምን ናቸው?

የመፈወስና ተአምራትን የማድረግ ስጦታዎች

የብሉይ ኪዳን ተአምራትና አዲሱን ዘመን በተስፋ መመልከት

ተአምራትና ፈውሶች በአዲስ ኪዳን

እግዚአብሔር ፈውስን የሚሰጥባቸው የተለያዩ አሠራሮች

ስለ ተአምራትና ፈውሶች የሚሰጡ የተሳሳቱ አሳቦች

የመንፈሳዊ ስጦታዎች ትምህርት ማጠቃለያ

በመንፈስ ቅዱስ መሞላት

የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምንድን ነው?

ከኤፌ 5፡18-20 በመንፈስ ቅዱስ ስላ መሞላት ምን ልንመለከት እንችላለን?

በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ማረጋገጫዎች

በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት የሚቀርቡ ቅድመ ሁኔታዎች

በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና መንፈሳዊ ብስለት

የመጀመሪያው የመንፈስ ቅዱስ ዋና ሥራ፡- ዘላለማዊው አምላክ በውስጣችን መኖሩ

የመንፈስ ቅዱስ ሁለተኛ ዋና ተግባሩ፡- ወደ ኢየሱስ ማመልከትና እርሱን እንድንመስል ማድረግ።

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች ክለሳ

ጥያቄ፡- ዘኁል. 23፡19-20 አንብብ። ሀ) እነዚህ ቁጥሮች እግዚአብሔር ስለሚሰጠን ተስፋዎችና ስለ አፈጻጸማቸው ምን ያስተምሩናል? ለ) ሰዎች ቃል ከገቡላችሁ በኋላ እስከተወሰነ ጊዜ ያልፈጻሙላችሁን ተስፋዎች ዘርዝሩ። እዚህ የተገባላችሁ ተስፋዎች በዘግዩ ጊዜ ምን ተሰማችሁ? ) እግዚአብሔር ተስሩ ከሰጣችሁ በኋላ በፍጥነት የፈጸመላችሁን ዘርዝሩ። መ) ገና ወደፊት የሚፈጽምላችሁ ተስፋዎችስ የትኞቹ ናቸው? እግዚአብሔር እነዚህን ተስፋዎች ሳይፈጽምላችሁ ለረጅም ጊዜ የቆየበት ምክንያት ምን ይመስላችኋል? 

አንድ ሰው ተሉ ሊፈጽምልን የገባውን ቃል ሳይፈጽም ቢዘገይ የሚያስከትለውን ተስፋ መቁረጥ ሁላችንም ተለማምደነዋል። አንዳንድ የሚቀርቡን ሰዎች የገቡልንን አንዳንድ ተስፋዎች ፍጹም ሳያሟሉ ሲቀሩ ይህ በልባችን ከፈጠረው ቅሬታ ጋር ዝም ብለን እንኖራለን። በመጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር የሰጠውን ተስፋ ሁልጊዜ እንደሚፈጽም ተነግሮናል። እኛ በምንፈልገው ፍጥነት ወይም ባሰብነው መንገድ ባይሆንም እንደሚፈጸሙ የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን አለን። 

ባለፈው ሳምንት እግዚአብሔር ለሕዝቡ ለእስራኤል ሁላት ቀና የተስፋ ቃሎችን በነቢያቱ አማካይነት እንደሰጠ ተመልክተናል። የመጀመሪያው አንድ ቀን እንደ ጻዊት ያላ በመንፈስ የተሞላ መሪ በእስራኤል ብቻ ሳይሆን በዓለም ሁሉ ላይ ለመንገሥ ይመጣል የሚል ነበር። ሁለተኛው ደግሞ መንፈሱ በሰዎች ሁሉ ውስጥ የሚኖርበት፥ የእግዚአብሔር ሕግጋት በልባቸው የሚጻፍበት፥ ሰዎች ከእግዚአብሔር ዘንድ እንዳይባዝኑ ከእርሱ የሚማሩበትና እርሱን በመታዘዝ የሚመላለሱበት አዲስ ዘመን በመላው ዓላም እንደሚመጣ እግዚአብሔር ቃል መግባቱ ነው። 

እግዚአብሔር እነዚህን የተስፋ ቃሎች ከሰጠ በኋላ አይሁዶች አስቸጋሪ ጊዜ ገጠማቸው። በመጀመሪያ ወደ ባቢሎን ተማርከው ተወሰዱ። አይሁዶች እንደ አንድ ሕዝብ በዓለም ሁሉ ከተበተኑ በኋላ አንዳንዶቹ ተመልሰው በከነዓን መኖር ጀመሩ። ቢሆንም እንደ አንድ ሕዝብ ሁልጊዜ በማያቋርጥ የአሕዛብ መንግሥታት ተጽእኖ ሥር ወደቁ። በመጀመሪያ ባቢሎን፥ ቀጥሎ ፋርስ፥ ቀጥሎም ግሪክ፥ በመጨረሻም ሮም ተፈራርቀው ገዟቸው። የመጨረሻው የብሉይ ኪዳን ነቢይ ሚልክያስ በ400 ዓ.ዓ. ስለ መሢሑ መምጣት የማጠቃለያ አመልካች ትንቢት እስካመጣበት ጊዜ ድረስ የእግዚአብሔር አፍ ሆነው ለሕዝቡ የሚናገሩ ነቢያት ተመናምነው ነበር። ከዚያ በኋላ እግዚአብሔር ለሕዝቡ ያስተላልፍ የነበረው ትንቢታዊ መልእክት ቆመ። ከዚያ ጊዜ ወዲህ ለ400 ዓመታት እግዚአብሔር ቃሉን ለሕዝቡ እንዲናገር የላከው ነቢይ አልነበረም። ይህ ዘመን «400 የፀጥታ ዓመታት» በመባል ይታወቃል። 

ጊዜው እየረዘመ ሲሄድ የእግዚአብሔር ሕዝብ ስለ መሢሑ መምጣት ሁለት የተለያዩ አቋሞችን ያዙ። ብዙዎቹ እግዚአብሔር የሰጠውን የተስፋ ቃል ለመፈጸም አይችልም ብለው ተስፋ ቆረጡ። እግዚአብሔርን የሚያመልኩት ጥልቅ ትርጉም አግኝተውበት ሳይሆን በዘልማድ ብቻ ሆነ። በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር የት ነበር? ስለ መሢሑና ስለ አዲሱ ዘመን የተገቡት ተስፋዎች የሚፈጸሙት መቼ ነበር? ከዚህ በመነሣት እግዚአብሔር ሕዝቡን ትቶታል፥ ከእንግዲህ ወዲህ ለሕዝቡ የሚገደውም አይደለም አሉ። 

ጥያቄ፡- ሀ) እግዚአብሔር ለሕይወትህ የገባው ቃል ተሎ በማይፈጸምበት ጊዜ እንደዚህ ዓይነት ስሜት ተሰምቶህ ያውቃልን? ስለ ሁኔታውና እግዚአብሔር በሁኔታው ውስጥ ስላስተማረህ ነገር አብራራ። ለ የገባልህ ቃል በመጨረሻ እንዴት ተፈጸመ? 

ሌሎች ግን ስለ አዲሱ ዘመንና ስለ መሢሑ መምጣት የነበራቸው ጉጉት በጣም ጽኑ ነበር። ከፖለቲካ ባርነት ነክ የሚወጡባትን ቀን ናፈቁ። ነገር ግን ከመንፈሳዊ ባርነት ነፃ ወጥተው ሙሉ ለሙሉ እግዚአብሔርን መታዘዝ የሚያስችላቸውን የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ላመታጠቅ የጓጉ ጥቂቶች ብቻ ነበሩ። 

ከ400 ዓመታት የፀጥታ ዘመን በኋላ በድንገት የእግዚአብሔር መንፈስ መንቀሳቀስ ጀመረ። መሢሑ የሚነግሥስት የተለሩው ፍጻሜና መንፈስ ቅዱስ ከሰው ልጅ ጋር በሚያደርገው ግንኙነት አዲስ ዘመን የሚያመጣበት ጊዜ ደረሰ። ነገር ግን ይህ የተከናወነው ሰዎች ከጠበቁት በተለየ መንገድ ስለነበረ የመንፈስ ቅዱስን ሥራ ልብ ለማለት አልቻሉም። እንዲያውም የብሉይ ኪዳን ነቢያት የተናገሩለትን መሢሑን ሰቅለው ገደሉት። የእግዚአብሔር መንገዶች ከሰው መንገዶች በጣም የተለዩ ናቸው። ደግሞም የመንፈስ ቅዱስ ሥራ አስቀድመን የምንገምተው አይደለም። 

የመሢሑን ታሪክ በምንመለከትባቸው አራት ወንጌላት የመንፈስ ቅዱስን ሥራ በሁለት ዋና ገጽታዎች እንመለከታለን። በመጀመሪያ መንፈስ ቅዱስ ክመሢሑ ከኢየሱስ ጋር የተቆራኘና በአገልግሎቶቹ ሁሉ ውስጥ ዋና ተሳታፊ ነበር። ሁለተኛው መንፈስ ቅዱስ በኋላ ከሚከናወነው የደቀ 

መዛሙርት ሥራ ጋርም ጥብቅ ቁርኝት ነበረው። መንፈስ ቅዱስ በእግዚአብሔር ልጆች ሁሉ ውስጥ የሚኖርበትን ዘመን ኢየሱስ ባያስጀምርም እንኳ ይህ ዘመን እርሱ ደቀ መዛሙርትን በምድር ትቶ ወደ ሰማይ ስሚሄድበት ጊዜ እንደሚሆን በአጽንኦት ተናግሮ ነበር። 

ጥያቄ፡- የሚከተሉትን ጥቅሶች አንብብ። ማቴ. 3፡11፤ 3፡16፤12፡18፤ ማር. 1፡12፤ ሉቃስ 1፡35፤ 4፡14፤ ዮሐ 3፡34፤ 15፡26፤ 20፡22፤ የሐዋ. 1፡2፤ 10፡38፤ ሮሜ 8፡11፤ ዕብ. 9፡14፤ 1ኛ ጴጥ. 3፡18። እነዚህ ጥቅሶች በመንፈስ ቅዱስና በኢየሱስ ክርስቶስ መካከል ስላለው ግንኙነት ምን ያስተምሩናል?

ምንጭ፡- “የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ”፣ በቲም ፌሎስ ተጽፎ፣ በጌቱ ግዛው የተተረጎመ እና በኤስ አይ ኤም ጽሑፍ ክፍል የተዘጋጀ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

የብሉይ ኪዳን ነቢያት መሢሑ የሚመጣበትን ወቅትና የመንፈስ ቅዱስ አገልግሉት የሚለወጥበትን ጊዜ እስቀድመው አመልክተው ነበር መንፈስ ቅዱስ በጌታ ኢየሱስ ሕይወትና አገልግሎት ውስጥ

የጌታ ጸጋ ከእርስዎ ጋር ይሁን፤ ሀሳብዎን ለመስማት ዝግጁ ነን።

Discover more from የሕይወት እንጀራ

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading