የሕይወት እንጀራ አገልግሎት

የብሉይ ኪዳን ተአምራትና አዲሱን ዘመን በተስፋ መመልከት

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

መግቢያ

ስለ መንፈስ ቅዱስ ለምን እናጠናለን?

ሥነ መለኮት ምንድን ነው?

መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የምንረዳበት ምንጭ

መንፈስ ቅዱስን ማወቅ

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ስፍራ

የመንፈስ ቅዱስ ዋና ኃላፊነቶች ምንና ምን ናቸው?

የመንፈስ ቅዱስ ስሞች

የመንፈስ ቅዱስ ተምሳሌቶች

እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ማን ነው?

መንፈስ ቅዱስ፤ ሦስተኛው የሥላሴ አካል

መጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ አምላክ መሆኑን ያሳየናልን?

መንፈስ ቅዱስ በብሉይ ኪዳን

የእግዚአብሔርን ሕዝብ ይመሩ ዘንድ መሪዎችን ብቁ በማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል እንዲጽፉ በመምራት የሰጠው አገልግሎት

የብሉይ ኪዳን ነቢያት መሢሑ የሚመጣበትን ወቅትና የመንፈስ ቅዱስ አገልግሉት የሚለወጥበትን ጊዜ እስቀድመው አመልክተው ነበር

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት በወንጌላት

መንፈስ ቅዱስ በጌታ ኢየሱስ ሕይወትና አገልግሎት ውስጥ

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የሰጠው ትምህርት፤ ክፍል 1

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ያስተማረው ትምህርት፤ ክፍል 2

ክርስቲያኖች እንደ መንፈስ ቅዱስ ባሉ መሠረታዊ የክርስትና አስተምህሮዎች ላይ ባላቸው አመለካከት ልዩነት የሚያሳዩት ለምንድን ነው?

መንፈስ ቅዱስን በተመለከተ የተለያዩ መረዳቶች የሚታዩት ለምንድን ነው?

በመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችና በአምልኮ ልምምዶች ውስጥ ያሉ ልዩነቶችን እንዴት መያዝ አለብን?

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 1-2 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 3-8 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 9-28)

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 1

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 2

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 3

የጴንጤቆስጤ ሥነ መለኮት ታሪክ

የጰንጠቆስጤና የአንዳንድ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ዋና ትምህርቶች ምን ምን ናቸው?

ከካሪዝማቲክ ትምህርት ለቤተ ክርስቲያን የተረፉ መልካም ውጤቶች

በካሪዝማቲክ የሥነ መለኮት ትምህርት የሚገኙ ሚዛናዊ ያልሆኑ ነገሮች

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል አንድ)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሁለት)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሦስት)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 1)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 2)

በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና ልሳን በመናገር መካከል ያሉ ግንኙነቶች

የመንፈስ ቅዱስ አማኞችን ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ የመምራት አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ እንድናመልክ ይረዳናል

መንፈስ ቅዱስ የክርስቲያኖች ሕይወት ኢየሱስን እንዲመስል የሚሰጠው አገልግሎት

ሰይጣንን ድል የማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

ስለ መንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች መግቢያ

መንፈሳዊ ስጦታ ምንድን ነው?

መንፈሳዊ ስጦታ (ሮሜ 12፡1-8)

መንፈሳዊ ስጦታ (ኤፌሶን 4፡1-16 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ጴጥሮስ 4፡7-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡1-3)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡4-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡12-31 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 13)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡1-19)

መንፈሳዊ ስጦታዎችና የማያምኑ ሰዎች (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡20-40)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 1)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 2) የተለያዩ ዓይነት ልሳናት አሉን?

በቤተ ክርስቱያን ውስጥ ስለሚመጣው ትንቢት ተጨማሪ አሳቦች

ትንቢት ምንድን ነው? ነቢይስ?

የትንቢት ስጦታ ምንድን ነው?

የእውነተኛና ሐሰተኛ ነቢያት ንጽጽር

የትንቢት ስጦታን ለመጠቀም መመሪያዎቹ ምን ምን ናቸው?

የመፈወስና ተአምራትን የማድረግ ስጦታዎች

የብሉይ ኪዳን ተአምራትና አዲሱን ዘመን በተስፋ መመልከት

ተአምራትና ፈውሶች በአዲስ ኪዳን

እግዚአብሔር ፈውስን የሚሰጥባቸው የተለያዩ አሠራሮች

ስለ ተአምራትና ፈውሶች የሚሰጡ የተሳሳቱ አሳቦች

የመንፈሳዊ ስጦታዎች ትምህርት ማጠቃለያ

በመንፈስ ቅዱስ መሞላት

የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምንድን ነው?

ከኤፌ 5፡18-20 በመንፈስ ቅዱስ ስላ መሞላት ምን ልንመለከት እንችላለን?

በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ማረጋገጫዎች

በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት የሚቀርቡ ቅድመ ሁኔታዎች

በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና መንፈሳዊ ብስለት

የመጀመሪያው የመንፈስ ቅዱስ ዋና ሥራ፡- ዘላለማዊው አምላክ በውስጣችን መኖሩ

የመንፈስ ቅዱስ ሁለተኛ ዋና ተግባሩ፡- ወደ ኢየሱስ ማመልከትና እርሱን እንድንመስል ማድረግ።

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች ክለሳ

2ኛ ጥያቄ፡- የሚከተሉትን ጥቅሶች ተመልከት። ዘጸአ 14፡5-22፤ ኢያሱ 10፡11-14 1ኛ ሳሙ. 12፡18፤ 1ኛ ነገ 18፡30-38፤ 2ኛ ነገ. 4፡32-35። የእግዚአብሔር በብሉይ ኪዳን ሰዎች አማካኝነት የሠራቸውን ተአምራት ዘርዝር። 

በብሉይ ኪዳን የተዘረዘሩ ተአምራት በርካታ ናቸው። ከብሉይ ኪዳን የምንማረው ነገር ቢኖር እግዚአብሔር ታላቅና ኃያል፥ ተአምራትን ማድረግ የሚችል ለሕዝቡም ይህንን በተደጋጋሚ ያደረገ መሆኑን ነው። ቀይ ባሕርን መክፈል፥ የኢያሪኮን ግንብ መጣል በሽተኞችን መፈወስ፥ ሙታንን ማስነሣት እነዚህ ሁሉ እግዚአብሔር በብሉይ ኪዳን የፈጸማቸው ተአምራት ናቸው።  

ነገር ግን የብሉይ ኪዳን ተአምራት አስገራሚ የሆነ የአፈጻጸም ሂደት አላቸው። ተአምራቱ ደረጃ በደረጃ የሚፈጸሙ ይመስላሉ። እግዚአብሔር በርካታ ተአምራት ያደረገባቸው ጊዜያት ነበሩ። እጅግ በጣም ጥቂት ተአምራት የፈፀመባቸው ረጅም ጊዜያትም ነበሩ። እግዚአብሔር ምንም ተአምራት ያላደረገበት ወቅት የሕዝቡን መንፈሳዊ ሕይወት እጅግ ዝቅተኛ የነበረበት ወቅት እንደሆነ ልናስብ እንችላለን። ነገር ግን እንደዚያ አልነበረም። የእስራኤል ሕዝብ መንፈሳዊ ሕይወት ከፍተኛ የነበረበት የዳዊት አመራር ዘመን አንዳችም ተአምራት አልተደረገም ለማለት የሚያስችል ነበር። 

የብሉይ ኪዳን ታሪክ እንደሚያመላክተን ተአምራት እጅግ ቶሎ ይፈጸሙ የነበሩበት ዘመን የነበረ ቢሆንም የእስራኤል ሕዝብ አብዛኛው ታሪከ ግን በቁጥር እጅግ አነስተኛ ተአምራት የተፈጸመበት ጊዜ ነበር። ተአምራት የተዘወተረባቸው ሦስት ዘመናት ነበሩ። 

1. እግዚአብሔር ነገሮችን ሁሉ በሠራበት የፍጥረት ዘመን። 

2. እግዚአብሔር እስራኤላውያን ከባርነት ነፃ በማውጣት በምድረ በዳ ውስጥ መርቶ በተስፋይቱ ምድር ያሳረፋቸው ዘመን። 

3. ኤልያስና ኤልሳዕ ነቢያት የነበሩበት ዘመን። 

ይህ ማለት እግዚአብሔር በሌሎች ዘመናት ተአምራትን አላደረገም ማለት አይደለም። ወይም ደግሞ እግዚአብሔር በሁሉም ዘመናት ተአምራትን ሊያደርግ አይችልም ማለት አይደለም። ይልቁኑ ይህ የሚያሳየው በእግዚአብሔር አሠራር ውስጥ እግዚአብሔር ለአንድ በግልጽ ተለይቶ ለታወቀ ዓላማ ተአምራትን ለመሥራት የሚፈልግበትና ብዙ ተአምራትን ለመሥራት የማይመርጥበት ጊዜ መኖሩን ነው። 

ከብሉይ ኪዳን የምንመለከተው ሌላው አስገራሚ ነገር ተአምራት በሚፈጸሙበት ወቅት ተአምራቱ ለእግዚአብሔር ስም ክብርን የሚያመጡ በሰዎች ዘንድ ፈሪሃ እግዚአብሔርን የሚያሳድሩ ቢሆንም እንኳ ብዙ ጊዜ ሰዎች በእግዚአብሔር ላይ ያላቸው እምነት እንዲጨምር አያደርጉም ነበር። በሙሴና በኢያሱ ዘመን እግዚአብሔር በርካታ ተአምራት ቢያደርግም እንኳ የእስራኤል ሕዝብ እምነት አልነበራቸውም፥ ያጉረመርሙ ነበር፡ ስለሆነም እግዚአብሔር አብዛኛዎቹን አጠፋቸው። በተመሳሳይ መንገድ በኤልያስና በኤልሳዕ ዘመን በርካታ ተአምራት የነበሩ ቢሆንም፥ እግዚአብሔር የበዓልን ነቢያት ለማሸነፍ በርካታ ተአምራት ቢያሳይም (1ኛ ነገ. 18፡30-38)፥ እስራኤላውያን ሕይወታቸውን ለውጠው በእውነተኛ ልብ እግዚአብሔርን አልተከተሉም ነበር። በተቃራኒው እጅግ ጥቂት ተአምራት ብቻ በተደረገባቸው በዳዊትና በሰለሞን ዘመናት ሕዝቡ ጤነኛ መንፈሳዊ ሕይወት ነበራቸው። 

ስለዚህ ከብሉይ ኪዳን ታሪኮች ልንገነዘባቸው የሚገቡ ሦስት ዋና ትምህርቶች 

ሀ) እግዚአብሔር ለሕዝቡ ተአምራትን የሚያደርግ ኃይል የተሞላ አምላክ መሆኑን 

ለ) እግዚአብሔር በዘመናት ሁሉ ተአምራት የሚያደርግበት ድግግሞሽ በየጊዜያቱ እኩል ያለመሆኑንና 

ሐ) ተአምራት በራሳቸው የእግዚአብሔርን ኃይል የሚገልጡ ቢሆንም ብዙ ጊዜ ግን የእግዚአብሔርን ሕዝብ መንፈሳዊ ብስለት ሲጨምሩ አለመታየታቸው ናቸው። 

ጥያቄ፡- ሀ) እግዚአብሔር ልዩ የሆነ ተአምር አድርጐልህ ለማየት ተመኝተህ ታውቃለህ? ምን ዓይነት ተአምራት እንዲያደርግልህ ነበር የፈለግኸው? ለ) እግዚአብሔር ይህን ተአምር እንዲያደርግልህ የፈለግኸው ለምን ነበር? ሐ) ይህ ነገር ስለ እምነት ምን ያሳያል? እምነትህ ደካማ ወይስ ብርቱ ነበር? መ) እግዚአብሔር ተአምራት እንዲያደርግ ሁልጊዜ የሚጠብቁ ሰዎች እምነት ምን ዓይነት ነው ብለህ ታምናለህ? ብርቱ ወይስ ደካማ? ይህን ለምን አልክ? 

ብሉይ ኪዳን ወደ መጠቃለል በቀረበበት ወቅት እግዚአብሔር ከሕዝቡ ጋር ልዩ የሆነ ግንኙነት የሚያደርግበት አስደናቂ አዲስ ዘመን እንደሚመጣ በነቢያቱ በኩል መናገር ጀመረ። በአዲሱ ዘመን መሢሑና መንፈስ ቅዱስ ልዩ ስፍራ ይኖራቸዋል። ከዚህ ቀደም ትንቢትን የመናገር ስጦታ ለብዙዎች እንደሚሰጥ በኢዩኤል መጽሐፍ ተመልክተናል። ነገር ግን እግዚአብሔር ለሕዝቡ እንደገና ተአምራትን የሚያደርግበትን ዘመን እንደሚያመጣና መሢሑን እንደሚያስነሣ የሚያመላክት ነገር አለ። መሢሑ ለታሠሩ መፈታትን፥ ለታወሩት ብርሃንን ያወጣል (ኢሳ.6፡1-2)። እንዲሁም ሕዝቡን ከበሽታቸው ይፈውሳቸዋል (ኢሳ. 3፡5)። 

ኢሳ 53፡5 በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ውዝግብን የፈጠረ ክፍል ነው። እግዚአብሔር፥ ኢየሱስ በሽታዎቻችንን «ሁሉ» እንደሚፈውስ ቃል መግባቱ ነበርን? እንደዚያ ከሆነ ብዙ ክርስቲያኖች ለምን ይታመማሉ? ኃጢአት በሕይወታቸው ስላለ ወይም በቂ እምነት ስለሌላቸው ነው? ብዙ ሰዎች ለክርስቲያኖች ሕመም የሚሰጡት ምክንያት ይህ ነው። ለነገሩ እግዚአብሔር ኃያል አምላክ ነውና ሁሉንም መፈወስ ይችላል። አፍቃሪ ስለሆነ ልጆቹ ሲሰቃዩ ማየት አይፈቅድም፤ እግዚአብሔር ከማንኛውም በሽታ እንደሚፈውሰን ቃል ገብቶልናል። ስለዚህ ካልተፈወስን በኃጢአት ወይም በቂ እምነት በማጣት ምክንያት ነው ይላሉ። 

ጥያቄ፡- በክርስቲያኖች መካከል እንደዚህ ዓይነት አስተሳሰብ ሲንጸባረቅ ሰምተህ ታውቃለህን? ከሰማህ ምን ምላሽ ትሰጣቸዋለህ? 

የሚያሳዝነው ነገር ይህ ዓይነት መረዳት ኢሳ. 53፡5 በተሳሳተ መንገድ በመተርጐሙ የመጣ መሆኑ ነው። ይህ ጥቅስ የሚናገረው በእርግጥ ስላ ሥጋዊ ፈውስ ነውን? በአይሁዳውያን አስተሳሰብ “ፈውስ” የሚለው ቃል ምሉዕነትን ያመለክታል። ብዙ ጊዜ የሥጋዊ አካል ምሉዕነትን ቢያመለክትም ቅሉ መንፈሳዊ ምሉዕነትንም ያመለክታል። አንድ ሰው ከኃጢአቱ በሚድንበት ጊዜ ይፈወሳል። ኢየሱስ የሚለውንና «እዳኝ» የሚል ትርጓሜ ያለውን ስም ያገኘነው ከዚህ ነው። ምሉዕ የሚያደርገን እርሱ ነው። ስለዚህ በኢሳ. 53፡5 የምናገኘው «ተፈወሳችሁ» የሚለው ቃል የግድ ሥጋዊ ሕመምን የሚያመለክት አይደለም። በዙሪያው ያሉትን አሳቦች ስንመላክት እግዚአብሔር በዚህ ቦታ የሚያመለክተው በተቀዳሚ ሥጋዊ ምሉዕነትን ሳይሆን መንፈሳዊ ምሉዕነትን ነው። ሌሎች ጥቅሶች የሚናገሩት ለለ መተላለፍ፥ ስለ በደልና፥ ስለ ሰላም ወዘተ… ነው። ስለዚህ በዚህ ጥቅስ አሳብ ላይ መሢሑ ፈውስን እንደሚያመጣ (በማቴ. 8፡16-17 የተተረጐመው በዚህ መንገድ ነው) የሚያመላክት አሳብ ሊገኝ ቢችልም ተቀዳሚ መረዳታችን ሊሆን የሚገባው ኢየሱስ ከኃጢአታችን እንደሚያድነን የሚናገር ስለመሆኑ ነው። የአዲስ ኪዳንን አጠቃላይ አሳብ በቅርብ በምንመረምርበት ወቅት እግዚአብሔር ለክርስቲያኖች ሁሉ ሙሉ የሆነ አካላዊ ፈውስን አልሰጠም። ጳውሎስ ይሰቃይ ነበር፥ ከእርሱ ጋር ይሠራ የነበረው አፍሮዲጡ አብሮት ሳለ እስከ ሞት ድረስ ታሞ ነበር (ገላ. 4፡13-14፤ ፊልጵ. 2፡27)። በሺህ የሚቆጠሩ መንፈሳዊ ክርስቲያኖች እግዚአብሔር ሌሎችን ለመፈወስ የሚጠቀምባቸው እንኳ ይታመማሉ። ስለዚህ እነዚህን ጥቅሶች ሰው ከሥጋዊ በሽታዎቹ ሁል ጊዜ ይፈወሳል ለማለት ልንጠቀምባቸው አንችልም።

ምንጭ፡- “የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ”፣ በቲም ፌሎስ ተጽፎ፣ በጌቱ ግዛው የተተረጎመ እና በኤስ አይ ኤም ጽሑፍ ክፍል የተዘጋጀ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

የመፈወስና ተአምራትን የማድረግ ስጦታዎች ተአምራትና ፈውሶች በአዲስ ኪዳን

የጌታ ጸጋ ከእርስዎ ጋር ይሁን፤ ሀሳብዎን ለመስማት ዝግጁ ነን።

Discover more from የሕይወት እንጀራ አገልግሎት

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading