የሕይወት እንጀራ አገልግሎት

በቤተ ክርስቱያን ውስጥ ስለሚመጣው ትንቢት ተጨማሪ አሳቦች

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

መግቢያ

ስለ መንፈስ ቅዱስ ለምን እናጠናለን?

ሥነ መለኮት ምንድን ነው?

መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የምንረዳበት ምንጭ

መንፈስ ቅዱስን ማወቅ

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ስፍራ

የመንፈስ ቅዱስ ዋና ኃላፊነቶች ምንና ምን ናቸው?

የመንፈስ ቅዱስ ስሞች

የመንፈስ ቅዱስ ተምሳሌቶች

እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ማን ነው?

መንፈስ ቅዱስ፤ ሦስተኛው የሥላሴ አካል

መጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ አምላክ መሆኑን ያሳየናልን?

መንፈስ ቅዱስ በብሉይ ኪዳን

የእግዚአብሔርን ሕዝብ ይመሩ ዘንድ መሪዎችን ብቁ በማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል እንዲጽፉ በመምራት የሰጠው አገልግሎት

የብሉይ ኪዳን ነቢያት መሢሑ የሚመጣበትን ወቅትና የመንፈስ ቅዱስ አገልግሉት የሚለወጥበትን ጊዜ እስቀድመው አመልክተው ነበር

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት በወንጌላት

መንፈስ ቅዱስ በጌታ ኢየሱስ ሕይወትና አገልግሎት ውስጥ

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የሰጠው ትምህርት፤ ክፍል 1

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ያስተማረው ትምህርት፤ ክፍል 2

ክርስቲያኖች እንደ መንፈስ ቅዱስ ባሉ መሠረታዊ የክርስትና አስተምህሮዎች ላይ ባላቸው አመለካከት ልዩነት የሚያሳዩት ለምንድን ነው?

መንፈስ ቅዱስን በተመለከተ የተለያዩ መረዳቶች የሚታዩት ለምንድን ነው?

በመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችና በአምልኮ ልምምዶች ውስጥ ያሉ ልዩነቶችን እንዴት መያዝ አለብን?

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 1-2 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 3-8 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 9-28)

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 1

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 2

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 3

የጴንጤቆስጤ ሥነ መለኮት ታሪክ

የጰንጠቆስጤና የአንዳንድ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ዋና ትምህርቶች ምን ምን ናቸው?

ከካሪዝማቲክ ትምህርት ለቤተ ክርስቲያን የተረፉ መልካም ውጤቶች

በካሪዝማቲክ የሥነ መለኮት ትምህርት የሚገኙ ሚዛናዊ ያልሆኑ ነገሮች

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል አንድ)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሁለት)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሦስት)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 1)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 2)

በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና ልሳን በመናገር መካከል ያሉ ግንኙነቶች

የመንፈስ ቅዱስ አማኞችን ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ የመምራት አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ እንድናመልክ ይረዳናል

መንፈስ ቅዱስ የክርስቲያኖች ሕይወት ኢየሱስን እንዲመስል የሚሰጠው አገልግሎት

ሰይጣንን ድል የማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

ስለ መንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች መግቢያ

መንፈሳዊ ስጦታ ምንድን ነው?

መንፈሳዊ ስጦታ (ሮሜ 12፡1-8)

መንፈሳዊ ስጦታ (ኤፌሶን 4፡1-16 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ጴጥሮስ 4፡7-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡1-3)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡4-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡12-31 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 13)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡1-19)

መንፈሳዊ ስጦታዎችና የማያምኑ ሰዎች (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡20-40)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 1)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 2) የተለያዩ ዓይነት ልሳናት አሉን?

በቤተ ክርስቱያን ውስጥ ስለሚመጣው ትንቢት ተጨማሪ አሳቦች

ትንቢት ምንድን ነው? ነቢይስ?

የትንቢት ስጦታ ምንድን ነው?

የእውነተኛና ሐሰተኛ ነቢያት ንጽጽር

የትንቢት ስጦታን ለመጠቀም መመሪያዎቹ ምን ምን ናቸው?

የመፈወስና ተአምራትን የማድረግ ስጦታዎች

የብሉይ ኪዳን ተአምራትና አዲሱን ዘመን በተስፋ መመልከት

ተአምራትና ፈውሶች በአዲስ ኪዳን

እግዚአብሔር ፈውስን የሚሰጥባቸው የተለያዩ አሠራሮች

ስለ ተአምራትና ፈውሶች የሚሰጡ የተሳሳቱ አሳቦች

የመንፈሳዊ ስጦታዎች ትምህርት ማጠቃለያ

በመንፈስ ቅዱስ መሞላት

የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምንድን ነው?

ከኤፌ 5፡18-20 በመንፈስ ቅዱስ ስላ መሞላት ምን ልንመለከት እንችላለን?

በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ማረጋገጫዎች

በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት የሚቀርቡ ቅድመ ሁኔታዎች

በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና መንፈሳዊ ብስለት

የመጀመሪያው የመንፈስ ቅዱስ ዋና ሥራ፡- ዘላለማዊው አምላክ በውስጣችን መኖሩ

የመንፈስ ቅዱስ ሁለተኛ ዋና ተግባሩ፡- ወደ ኢየሱስ ማመልከትና እርሱን እንድንመስል ማድረግ።

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች ክለሳ

ዮሐንስ ጐላ ያላ ድምፅ ማውጣት የሚችል ወጣት ሰው ነበር። አንድ ቀን የጸሎት ስብሰባ ተካፈለ። መሪው ሰዎችን ለበለጠ ጸሎት ያነሣሣል ብሎ በማሰብ የመሰብሰቢያ ክፍሉን መብራት አጠፋው። ወዲያውኑ ሰዎች በከፍተኛ ድምፅ መጸለይ ጀመሩ። አንዳንዶቹ በልሳናት ይጸልዩ ነበር። በድንገት በቡድኑ ውስጥ ከነበሩት ሰዎች አንዱ ወደ ዮሐንስ «መጣና እግዚአብሔር ለአንቺ የሚሆን መልእክት ሰጥቶኛል» አለው። «ማሕፀንሽ አሁን ተስፍቶአልና ልጅ ይኖርሻል» አለው። ዮሐንስ ቀን መለሰና እኔ እኮ ወንድ ነኝ አለው። ሰውዬውም መልሶ «እግዚአብሔር በውስጥህ ያለውን ከፉ መንፈስ ይገስጸው» አለው። 

ትንቢት መናገርና የጌታን ቃል እንደተናገሩ መቁጠር። ከላይ የተመለከትነው ታሪክ መንፈሳዊ ስጦታ ያለአግባብ ሥራ ላይ የዋለበትን አንድ ሁኔታ ብቻ የሚያሳየን ነው። ያ ቃል የማን ነበር! የእግዚአብሔር ቃል እንዳልነበረ ግልጽ ነው። ስለዚህ የሌላ አካል ማለትም የሰው ወይም የክፉ መንፈስ ነው። ይህ የጌታ ቃል አለኝ በማለት የሚናገርን ሰው ሳንመዝነው እንዲናገር የመፍቀድን አደገኛነት የሚያሳየንና የሚያስጠነቅቀን ይሆናል። በዚህ ዘመን በአብያተ ክርስቲያናት አካባቢ የሐሰት ትምህርቶችና ልምምዶች በታላቅ ፍጥነት እያደጉ የመጡበት አንድ ምክንያት የሰማናቸውን መልእክቶች ለመመዘን ባለመቻላችን ነው። ቢሆንም እግዚአብሔር አሁንም መናገሩን አይተውም። ከተዘረዘሩት መንፈሳዊ ስጦታዎች አንዱ የትንቢት ስጦታ ነው። ዛሬ ይህን ስጦታ በመመልከት መጽሐፍ ቅዱስ ስለዚህ ስጦታ የሚያስተምረውን እንመለከታለን። 

ጥያቄ፡- ሀ) አንድ ሰው ከእግዚአብሔር የተሰጠ መልእክት አለኝ ያለበትን ሁኔታ ግለጽ። ከእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠ ቃል ይመስልሃልን? ከእግዚአብሔር መሆኑንና ያለመሆኑን እንዴት ታውቃለህ? ለ) አንድ ሌላ ሰው ደግሞ ከእግዚአብሔር መልእክት አለኝ ብሉ የመጣበትንና አንተ ደግሞ መልእክቱ ከእግዚአብሔር መሆኑን የተጠራጠርክበትን ሌላ ሁኔታ ግላጽ፡ ከእግዚአብሔር እንዳልሆነ ለምን አሰብክ? 

ጥያቄ፡- የሚከተሉትን ጥቅሶች አንብብ። 1ኛ ተሰ. 5፡20፤ 1ኛ ቆሮ. 145 12፡8-14፤ ሮማ 12፡6፤ ኤፌ. 2፡20፤ 4፡11፣ 1ኛ ጢሞ. 18፤ 4፡14። በእነዚህ ጥቅሶች ስለ ትንቢት የተነገሩ የተለያዩ እውነቶችን ዘርዝር። 

በጳውሎስ መልእክቶች ከተዘረዘሩት መንፈሳዊ ስጦታዎች በሙሉ በተደጋጋሚ የተጠቀሰው የትንቢት ስጦታ ነው። ነቢያት በቀደምቷ ቤተ ክርስቲያን እጅግ አስፈላጊዎች ስላነበሩ እንደ ዋና የቤተ ክርስቲያን መሪዎች ሆነው ተመዝግበዋል። ቀደምታ ቤተ ክርስቲያን የተገነባችበት መሠረት አካል ነበሩ (ኤፌ. 2፡20)። ስለዚህ ነቢያትም ሆኑ የትንቢት ስጦቃዎች በቀደምቷ ቤተ ክርስቲያን ዋና ክፍል ነበሩ። 

በልሳናት መናገር መንፈሳዊ ስጦታ እንደሆነው ሁሉ የትንቢት ስጦታም ዛሬ በክርስቲያኖች መካከል አከራካሪ ጉዳይ ነው። ይህ መንፈሳዊ ስጦታና (እግዚአብሔር ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጥ ከልጆቹ ጋር የሚያደርገው ቀጥተኛ ግንኙነት በሙሉ) ከአዲስ ኪዳን መጻፍ በኋላ ቆሟልን? ብዙ ክርስቲያኖች በተለይ ደግሞ በልሳናት የመናገር ስጦታ በዚህም ዘመን መሥራቱን የማይቀበሉ ሁሉ የሚሉት ይህንን ነው። ወይስ የትንቢት ስጦታ ዛሬም ቢሆን የሚሠራ ነው? እግዚአብሔር ዛሬም ቢሆን በሕልም፥ በራእይ፡ በድምፅ፥ ወዘተ… ይናገረናልን? ይህ ከሆነ ይህ ስጦታ ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር ያለው ግንኙነት ምንድን ነው? የትንቢት ቃሎች በአዲስና በብሉይ ኪዳን ካሉ ቃሎች ጋር እኩል ሥልጣን አላቸው? 

ጥያቄ፡– ሀ) ስለትንቢት ምንነት የምታምነውን ጻፍ። ላ) ነቢይ ምንድን ነው? ሐ) የእግዚአብሔርን ቃል በጻፈ የብሉይ ኪዳን ነቢይና በዚህ ዘመን የትንቢት መንፈሳዊ ስጦታ አለኝ በሚል ሰው መካከል ልዩነት ያላ ይመስልሃልን? ካለስ ልዩነቱ ምንድን ነው? 

በትንቢት ምንነትና በነቢይ ማንነት ርእሰ ጉዳይ ላይ በዚህ ዘመን ባለች ቤተ ክርስቲያን ብዙ ውዥንብር አላ። በአንዳንድ አብያተ ክርስቲያናት ሰዎች ይቆሙና ከእግዚአብሔር ዘንድ የተቀበሉት የትንቢት ቃል እንዳላቸው ይናገራሉ። የሚያመጡት መልእክት ግን ለእግዚአብሔር ሕዝብ ምንም ወይም አነስተኛ ዋጋ ብቻ ያለው ይሆናል። አንዳንድ ጊዜ የእግዚአብሔር ቃል ከሚያስተምረው ጋር እንኳ የሚቃረን ይሆናል። አንዳንድ ሰዎችን የትንቢት ቃል ያመጡ ዘንድ እነርሱን የመጠባበቅ ዝንባሌ እየጨመረ መጥቷል። እግዚአብሔር ተናገረኝ ስንል ምን ማለታችን እንደሆነና የትንቢትን ምንነት በሚገባ ካላወቅን እንስታለን።

ምንጭ፡- “የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ”፣ በቲም ፌሎስ ተጽፎ፣ በጌቱ ግዛው የተተረጎመ እና በኤስ አይ ኤም ጽሑፍ ክፍል የተዘጋጀ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 2) የተለያዩ ዓይነት ልሳናት አሉን? ትንቢት ምንድን ነው? ነቢይስ?

የጌታ ጸጋ ከእርስዎ ጋር ይሁን፤ ሀሳብዎን ለመስማት ዝግጁ ነን።

Discover more from የሕይወት እንጀራ አገልግሎት

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading