የሕይወት እንጀራ

ከኤፌ 5፡18-20 በመንፈስ ቅዱስ ስላ መሞላት ምን ልንመለከት እንችላለን?

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

መግቢያ

ስለ መንፈስ ቅዱስ ለምን እናጠናለን?

ሥነ መለኮት ምንድን ነው?

መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የምንረዳበት ምንጭ

መንፈስ ቅዱስን ማወቅ

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ስፍራ

የመንፈስ ቅዱስ ዋና ኃላፊነቶች ምንና ምን ናቸው?

የመንፈስ ቅዱስ ስሞች

የመንፈስ ቅዱስ ተምሳሌቶች

እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ማን ነው?

መንፈስ ቅዱስ፤ ሦስተኛው የሥላሴ አካል

መጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ አምላክ መሆኑን ያሳየናልን?

መንፈስ ቅዱስ በብሉይ ኪዳን

የእግዚአብሔርን ሕዝብ ይመሩ ዘንድ መሪዎችን ብቁ በማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል እንዲጽፉ በመምራት የሰጠው አገልግሎት

የብሉይ ኪዳን ነቢያት መሢሑ የሚመጣበትን ወቅትና የመንፈስ ቅዱስ አገልግሉት የሚለወጥበትን ጊዜ እስቀድመው አመልክተው ነበር

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት በወንጌላት

መንፈስ ቅዱስ በጌታ ኢየሱስ ሕይወትና አገልግሎት ውስጥ

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የሰጠው ትምህርት፤ ክፍል 1

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ያስተማረው ትምህርት፤ ክፍል 2

ክርስቲያኖች እንደ መንፈስ ቅዱስ ባሉ መሠረታዊ የክርስትና አስተምህሮዎች ላይ ባላቸው አመለካከት ልዩነት የሚያሳዩት ለምንድን ነው?

መንፈስ ቅዱስን በተመለከተ የተለያዩ መረዳቶች የሚታዩት ለምንድን ነው?

በመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችና በአምልኮ ልምምዶች ውስጥ ያሉ ልዩነቶችን እንዴት መያዝ አለብን?

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 1-2 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 3-8 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 9-28)

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 1

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 2

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 3

የጴንጤቆስጤ ሥነ መለኮት ታሪክ

የጰንጠቆስጤና የአንዳንድ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ዋና ትምህርቶች ምን ምን ናቸው?

ከካሪዝማቲክ ትምህርት ለቤተ ክርስቲያን የተረፉ መልካም ውጤቶች

በካሪዝማቲክ የሥነ መለኮት ትምህርት የሚገኙ ሚዛናዊ ያልሆኑ ነገሮች

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል አንድ)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሁለት)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሦስት)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 1)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 2)

በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና ልሳን በመናገር መካከል ያሉ ግንኙነቶች

የመንፈስ ቅዱስ አማኞችን ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ የመምራት አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ እንድናመልክ ይረዳናል

መንፈስ ቅዱስ የክርስቲያኖች ሕይወት ኢየሱስን እንዲመስል የሚሰጠው አገልግሎት

ሰይጣንን ድል የማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

ስለ መንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች መግቢያ

መንፈሳዊ ስጦታ ምንድን ነው?

መንፈሳዊ ስጦታ (ሮሜ 12፡1-8)

መንፈሳዊ ስጦታ (ኤፌሶን 4፡1-16 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ጴጥሮስ 4፡7-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡1-3)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡4-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡12-31 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 13)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡1-19)

መንፈሳዊ ስጦታዎችና የማያምኑ ሰዎች (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡20-40)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 1)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 2) የተለያዩ ዓይነት ልሳናት አሉን?

በቤተ ክርስቱያን ውስጥ ስለሚመጣው ትንቢት ተጨማሪ አሳቦች

ትንቢት ምንድን ነው? ነቢይስ?

የትንቢት ስጦታ ምንድን ነው?

የእውነተኛና ሐሰተኛ ነቢያት ንጽጽር

የትንቢት ስጦታን ለመጠቀም መመሪያዎቹ ምን ምን ናቸው?

የመፈወስና ተአምራትን የማድረግ ስጦታዎች

የብሉይ ኪዳን ተአምራትና አዲሱን ዘመን በተስፋ መመልከት

ተአምራትና ፈውሶች በአዲስ ኪዳን

እግዚአብሔር ፈውስን የሚሰጥባቸው የተለያዩ አሠራሮች

ስለ ተአምራትና ፈውሶች የሚሰጡ የተሳሳቱ አሳቦች

የመንፈሳዊ ስጦታዎች ትምህርት ማጠቃለያ

በመንፈስ ቅዱስ መሞላት

የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምንድን ነው?

ከኤፌ 5፡18-20 በመንፈስ ቅዱስ ስላ መሞላት ምን ልንመለከት እንችላለን?

በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ማረጋገጫዎች

በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት የሚቀርቡ ቅድመ ሁኔታዎች

በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና መንፈሳዊ ብስለት

የመጀመሪያው የመንፈስ ቅዱስ ዋና ሥራ፡- ዘላለማዊው አምላክ በውስጣችን መኖሩ

የመንፈስ ቅዱስ ሁለተኛ ዋና ተግባሩ፡- ወደ ኢየሱስ ማመልከትና እርሱን እንድንመስል ማድረግ።

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች ክለሳ

1. ትእዛዝ ነው። በመንፈስ ቅዱስ መሞላት እንዳለብን ተነግሮናል። ይህ ሁለት ነገሮችን ያመለክታል። በመጀመሪያ ለመታዘዝ ወይም ላለመታዘዝ ምርግ እንዳለን ነው። በመንፈስ ቅዱስ እንሞላ ዘንድ በእግዚአብሔር ጋር ለመሥራት እንችላለን። ወይም በመንፈስ ቅዱስ ከመሞላት የሚያግደንን ኦኗኗር መኖር እንችላለን። ሁለተኛ በዚህ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት በአንድ ወይም በሌላ መንገድ ተሳታፊዎች መሆናችንን ያመለክታል። እግዚአብሔር የማንሳተፍበትን ነገር እንድናደርግ አያዘንም። ስለዚህ በመንፈስ ቅዱስ እንሞላ ዘንድ ከእግዚአብሔር ጋር ለመሥራት የምንችልበት መንገድ አለ። የእግዚአብሔር ሉዓላዊ ዕቅድ የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ከግለሰቡ ፈቃድ ጋር የሚሄድ እንዲሆን አድርጐታል። መንፈስ ቅዱስ በሕይወታችን እንዲሞላና እንዲጠቀምብን ማድረግ ወይም በከፊልም ቢሆን ይህ እንዳይሆን መከላከል እንችላለን። 

2. በተደጋጋሚ የሚፈጸም ተግባር ነው። በግሪክ ቋንቋ በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ትእዛዝ የአሁን ጊዜን በሚያመለክት ግሥ ነው የተጻፈው። ይህ ማለት በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላታችን ሁልጊዜ እርግጠኞች መሆን አለብን ማለት ነው። ይህ ማለት በመንፈስ ቅዱስ ልንሞላ፥ በሆነ ምክንያት ደግሞ ይህን ሙላት ልናጣና እንደገና መሞላት ሊያስፈልገን ይችላል ማለት ነው። ይህ እውነት በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ተመልክቷል። የመጀመሪያዎቹ ደቀ መዛሙርት በበዓለ ኀምሣ ቀን በመንፈስ ቅዱስ ተሞልተው ነበር (የሐዋ. 2፡4)። ቆይቶ ጴጥሮስ በካህናት ጉባኤ የፍርድ ወንበር ፊት በቀረበ ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ እንደተሞላ ተጽፏል (የሐዋ. 4፡31)። 

3. የመንፈስ ቅዱስ ሙላት በጣም በተላመደ ነገር ግን ኃይል በሞላበት መንገድ ተገልጧል። በግሪኩ ቋንቋ ኤፌ. 5፡18-21 ያለው ቃል አንድ ዐረፍተ ነገር ነው። አንድ ትእዛዝ ማላትም በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ» የሚለውን ይዟል። ይህ አንዱ ትእዛዝ በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት ምልክት የሚሆኑ አራት ቅድመ-ሁኔታዎችን ያስከትላል። እነርሱም መናገር (ቁጥር 19)፥ መዝሙር (ቁጥር 19)፥ ምስጋና ማቅረብ (ቁጥር 20) እና ለሌሎች መገዛት (ቁጥር 2) ናቸው። 

በመንፈስ ቅዱስ በምንሞላበት ጊዜ መሞላታችን የሚረጋገጠው እንዴት ነው? በመንፈስ ቅዱስ መሞላት ክአስደናቂ ድርጊቶች ጋር እንደሚያያዝ እናስብ ይሆናል። ምናልባት የሆነ ታላቅ ተአምር ወይም ልዕለ-ተፈጥሮአዊ ምልክቶች እንደሚያጅቡት እናስብ ይሆናል። ጳውሎስ በእነዚህ ጥቅሶች የሚናገረው ነገር ይህን አይደለም። የመንፈስ ቅዱስ መሞላት በሁለት ዋና መንገዶች ራሱን ይገልጻል። በመጀመሪያ፥ አመላለካችን ይቀየራል። ልባችን በመዝሙርና በምስጋና ይጥለቀለቃል። 

በሁለተኛ ደረጃ ፥ በመንፈስ ቅዱስ መሞላታችን ከሌሎች ጋር ያላንን ግንኙነት ይቀይራል። ተፈጥሮአችን የሆነውን የለለታምነታችንን ዝንባሌ ቀይረን በትሕትና ዝቅ ብለን ለሌሎች እራሳችንን እንድናስገዛ ያስችለናል። በዕድሜ የገፉ ለወጣቶች ፍላጐት እንደዚህም ወጣቶች በዕድሜ የገፉ ሰዎች ፍላጐት ይገዛሉ። ወንዶች ለሴቶች ሴቶችም ላወንዶች አመለካከት ይገዛሉ። ባሎች ለሚስቶች፥ ሚስቶች ደግሞ ለባሎች ይገዛሉ። ሀብታሞች ለድሆች፥ የተማሩት ላልተማሩት ወዘተ… ይገዛሉ። ሰዎች እግዚአብሔር በሰውዩው ሕይወት ኃይለኛ ነገር እየሠራ እንደሆነ ለማየት እስከሚገደዱ ድረስ ግንኙነቶች ይቀየራሉ። 

ጥያቄ፡- ሀ) በመንፈስ ቅዱስ ስለ መሞላት ይህ የተመለከትነው መረዳት እኛ ብዙ ጊዜ ካለን አመለካከት የተለየ የሚሆነው እንዴት ነው? ለ) መንፈስ ቅቶስ ለእግዚአብሔር ክብር የሆነውን ነገር በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያደርግ ዘንድ ሥርዓት የሞላበት አምልኮና መልካም ግንኙነቶች ከሁሉ በላይ አስፈላጊ ነገሮች የሚሆኑት ለምንድን ነው? 

የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ከሕይወታችን የሚቋረጥበት ተቀዳሚ ምክንያት የራሳችንን ሕይወት ኃጢአት በሞላበት መንገድ ልንቆጣጠር በምንሞክርበት ጊዜ ነው። የራሳችንን ሕይወት ልንቆጣጠር በምንወስንበት ወቅት መንፈስ ቅዱስ እኛን መቆጣጠሩን ያቆማል። ነገር ግን ንስሐ በምንገባበትና እግዚአብሔር ሕይወታችንን በሙላት እንዲቆጣጠር በምንጠይቅበት ወቅት መንፈስ ቅዱስ እንደገና ይሞላናል። 

በክርስቲያኖች ሕይወት ብዙ ጊዜ ከደኅንነታቸው በኋላ ቀውስ የተፈጠረባቸው ወቅቶች ይኖራሉ። ውስጣዊ የሆነ ጥልቅ ሕይወታቸውን ለመቆጣጠር የሚካሄድ ትግል አለ። መንፈስ ቅዱስ በሕይወታችን ዙፋን ላይ በመቀመጥ የምንፈልገውን፥ የምናደርገውንና የምንናገረውን ሁሉ ላመቆጣጠር ይፈልጋል። በሕይወት ዘመናችን ሁሉ ግን የኖርነው እራሳችንን በመቆጣጠር ነው። ስለዚህ ታላቅ ጦርነት ይካሄዳል። በመጨረሻ ይህ ራስ ወዳድ የሆነው መንፈሳችን ይሰበራል። ለእግዚአብሔር ቁጥጥር እራሳችንን እሳልፈን እንሰጣለን። ትልቁ ጦርነት ከተጠናቀቀ በኋላ በሕይወታችን ታላቅ ለውጥ ይከናወናል። ታላቅ ደስታና ሰላም ይሆናል። አገልግሎታችን ኃይልን ይቀዳጃል። ከእግዚአብሔር ጋር የምናደርገው ጉዞ ጣፋጭና በጥብቅ ቁርኝት የሚካሄድ ይሆናል። ሕይወታችንን ለመቆጣጠር የሚደረጉ እነስተኛ ውጊያዎች ይኖራሉ። ለኃጢአታዊ ተፈጥሮአችን እራሳችንን የምናስገዛበትና እግዚአብሔር በላያችን ላይ እንዳይሠለጥን የምናደርግባቸው ጊዜያት ይኖራሉ። የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ወይም ቁጥጥር በዚያ ነጥብ ላይ ይጠፋል። ነገር ግን ለመንፈስ ቅዱስ ድምፅ ንቁ የመሆን ልምምድ በሕይወታችን ስለሚኖር ወዲያውኑ ወደ ጸጋ ዙፋኑ ፊት በመቅረብና ይቅርታን በመጠየቅ በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ሥር ወደ መኖሩ እንመለሳለን። ከዚያም እንደገና በመንፈስ ቅዱስ እንሞላና በመንፈሳዊ ሕይወታችን እንደገና እንቀጥላለን። ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ በሰው ሕይወት ውስጥ ከሚሠራቸው ሥራዎች አንዱ የበላይነት አግኝቶ ይቆጣጣር ዘንድ ወሳኙን ጦርነት ማካሄድ ነው። ከዚያም በክርስቲያን ሕይወት ዘመን ሁሉ የሕይወቱን እያንዳንዱን ክፍል የበለጠ በበላይነት ይቆጣጠር ዘንድ መንፈስ ቅዱስ ትናንሽ ጦርነቶችን ያካሄዳል። በመንፈሳዊ ሕይወት ማደግ ማለት ሕይወታችን ለዘላቄታው በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ሥር እንዲሆን መፍቀድን እንደሚያካትት እናያለን። 

ጥያቄ፡- ሀ) ስለ ራስህ ሕይወት አስብ። የእግዚአብሔር መንፈስ ሕይወትህን እንዳይቆጣጠር የታገልክባቸው ጊዜያት በእርግጥ ነበሩን? ያንን ልምምድህን ግላጽ። ለ) እንደዚህ ዓይነት አስቸጋሪ ልምምድ ካልነበረህ መንፈስ ቅዱስ ከዚህ ቀደም እንደሞላብህ እሁንም ሕይወትህን እያገዘ ለመሆኑ ምን ማስረጃ አለህ? ሐ) መንፈስ ቅዱስ ሙሉ በሙሉ በሥልጣን እንዲገዛህ ያልፈቀድክባቸውን የሕይወትህን ክፍሎች እንዲያሳይህ በጸሎት ትጠይቀው ዘንድ አሁን ጊዜ ውሰድ። ስለ እነዚያ ሁኔታዎች ንስሐ ግባ። መንፈስ ቅዱስ እንደ አዲስ እንዲሞላህና ኢየሱስን እንድትመስል እንዲረዳህ ጸልይ። 

እንግዲያውስ በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ትርጉሙ ምንድን ነው? በመንፈስ ቅዱስ መሞላት ክርስቲያን ሕይወቱን ለመንፈስ ቅዱስ በማስገዛት በባሕርይና በተግባር የበለጠ ኢየሱስን እየመሰላ እንዲሄድ መንፈስ ቅዱስ ሕይወቱን እንዲሠራ የሚፈቅድበት ተደጋጋሚ ልምምድ ነው።

ምንጭ፡- “የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ”፣ በቲም ፌሎስ ተጽፎ፣ በጌቱ ግዛው የተተረጎመ እና በኤስ አይ ኤም ጽሑፍ ክፍል የተዘጋጀ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምንድን ነው? በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ማረጋገጫዎች

የጌታ ጸጋ ከእርስዎ ጋር ይሁን፤ ሀሳብዎን ለመስማት ዝግጁ ነን።

Discover more from የሕይወት እንጀራ

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading