የሕይወት እንጀራ

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 1-2 )

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

መግቢያ

ስለ መንፈስ ቅዱስ ለምን እናጠናለን?

ሥነ መለኮት ምንድን ነው?

መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የምንረዳበት ምንጭ

መንፈስ ቅዱስን ማወቅ

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ስፍራ

የመንፈስ ቅዱስ ዋና ኃላፊነቶች ምንና ምን ናቸው?

የመንፈስ ቅዱስ ስሞች

የመንፈስ ቅዱስ ተምሳሌቶች

እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ማን ነው?

መንፈስ ቅዱስ፤ ሦስተኛው የሥላሴ አካል

መጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ አምላክ መሆኑን ያሳየናልን?

መንፈስ ቅዱስ በብሉይ ኪዳን

የእግዚአብሔርን ሕዝብ ይመሩ ዘንድ መሪዎችን ብቁ በማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል እንዲጽፉ በመምራት የሰጠው አገልግሎት

የብሉይ ኪዳን ነቢያት መሢሑ የሚመጣበትን ወቅትና የመንፈስ ቅዱስ አገልግሉት የሚለወጥበትን ጊዜ እስቀድመው አመልክተው ነበር

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት በወንጌላት

መንፈስ ቅዱስ በጌታ ኢየሱስ ሕይወትና አገልግሎት ውስጥ

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የሰጠው ትምህርት፤ ክፍል 1

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ያስተማረው ትምህርት፤ ክፍል 2

ክርስቲያኖች እንደ መንፈስ ቅዱስ ባሉ መሠረታዊ የክርስትና አስተምህሮዎች ላይ ባላቸው አመለካከት ልዩነት የሚያሳዩት ለምንድን ነው?

መንፈስ ቅዱስን በተመለከተ የተለያዩ መረዳቶች የሚታዩት ለምንድን ነው?

በመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችና በአምልኮ ልምምዶች ውስጥ ያሉ ልዩነቶችን እንዴት መያዝ አለብን?

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 1-2 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 3-8 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 9-28)

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 1

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 2

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 3

የጴንጤቆስጤ ሥነ መለኮት ታሪክ

የጰንጠቆስጤና የአንዳንድ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ዋና ትምህርቶች ምን ምን ናቸው?

ከካሪዝማቲክ ትምህርት ለቤተ ክርስቲያን የተረፉ መልካም ውጤቶች

በካሪዝማቲክ የሥነ መለኮት ትምህርት የሚገኙ ሚዛናዊ ያልሆኑ ነገሮች

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል አንድ)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሁለት)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሦስት)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 1)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 2)

በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና ልሳን በመናገር መካከል ያሉ ግንኙነቶች

የመንፈስ ቅዱስ አማኞችን ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ የመምራት አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ እንድናመልክ ይረዳናል

መንፈስ ቅዱስ የክርስቲያኖች ሕይወት ኢየሱስን እንዲመስል የሚሰጠው አገልግሎት

ሰይጣንን ድል የማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

ስለ መንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች መግቢያ

መንፈሳዊ ስጦታ ምንድን ነው?

መንፈሳዊ ስጦታ (ሮሜ 12፡1-8)

መንፈሳዊ ስጦታ (ኤፌሶን 4፡1-16 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ጴጥሮስ 4፡7-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡1-3)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡4-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡12-31 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 13)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡1-19)

መንፈሳዊ ስጦታዎችና የማያምኑ ሰዎች (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡20-40)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 1)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 2) የተለያዩ ዓይነት ልሳናት አሉን?

በቤተ ክርስቱያን ውስጥ ስለሚመጣው ትንቢት ተጨማሪ አሳቦች

ትንቢት ምንድን ነው? ነቢይስ?

የትንቢት ስጦታ ምንድን ነው?

የእውነተኛና ሐሰተኛ ነቢያት ንጽጽር

የትንቢት ስጦታን ለመጠቀም መመሪያዎቹ ምን ምን ናቸው?

የመፈወስና ተአምራትን የማድረግ ስጦታዎች

የብሉይ ኪዳን ተአምራትና አዲሱን ዘመን በተስፋ መመልከት

ተአምራትና ፈውሶች በአዲስ ኪዳን

እግዚአብሔር ፈውስን የሚሰጥባቸው የተለያዩ አሠራሮች

ስለ ተአምራትና ፈውሶች የሚሰጡ የተሳሳቱ አሳቦች

የመንፈሳዊ ስጦታዎች ትምህርት ማጠቃለያ

በመንፈስ ቅዱስ መሞላት

የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምንድን ነው?

ከኤፌ 5፡18-20 በመንፈስ ቅዱስ ስላ መሞላት ምን ልንመለከት እንችላለን?

በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ማረጋገጫዎች

በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት የሚቀርቡ ቅድመ ሁኔታዎች

በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና መንፈሳዊ ብስለት

የመጀመሪያው የመንፈስ ቅዱስ ዋና ሥራ፡- ዘላለማዊው አምላክ በውስጣችን መኖሩ

የመንፈስ ቅዱስ ሁለተኛ ዋና ተግባሩ፡- ወደ ኢየሱስ ማመልከትና እርሱን እንድንመስል ማድረግ።

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች ክለሳ

ኢየሱስ ወደ ሰማይ ካረገበት ቀን ጀምሮ መንፈስ ቅዱስ እሰከወረደበት ቀን ድረስ የነበሩት አምሳ ቀናት ለደቀ መዛሙርት እጅግ በጣም የተራዘሙባቸው ነበሩ። በመቶ ከሚቆጠሩ ዓመታት በፊት በኢዩኤልና በነቢያት የተነገረው፤ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርትን በምድር ትቶ ወደ ሰማይ ከማረጉ ከጥቂት ጊዜ በፊት ያረጋገጠው የተስፋ ቃል ሊፈጸም ተቃርቦ ነበር። ሰማይና ምድር (አዲስ ዘመን) የሚጀመርበትን፥ መንፈስ ቅዱስ ለእግዚአብሔር ልጆች ሁሉ የሚሰጥበትን ቀን በናፍቆት ይጠባበቁ ነበር። በድንገት እንደሚነጥቅ አውሎ ነፋስ ድምፅና በደቀ መዛሙርት ራስ ላይ እንደተቀመጠ ታላቅ የእሳት ልሳን ሆኖ መንፈስ ቅዱስ በዚያ አነስተኛ የአማኞች ጉባኤ ላይ ወረደ። የኢየሱስ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ተወለደች። ደቀ መዛሙርቱም ታሪክን መቀየር ጀመሩ። 

የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ የመጀመሪያቱን ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ይዘግባል። የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ የሚያሳየን መንፈስ ቅዱላ በደቀ መዛሙርት አገልግሎትና በቤተ ክርስቲያን እድገት ምን ያህል አስፈላጊ እንደነበረ ነው። አንዳንድ የሥነ መለኮት ሊቃውንት ይህን መጽሐፍ «የመንፈስ ቅዱስ ሥራ» ብለው የሚጠሩት ለዚህ ነው። የሚያሳዝነው ነገር ዛሬ በሥነ መለኮት «ካሪዝማቲክ» በሆኑ ቡድኖችና «ካሪዝማቲክ ባልሆኑት » መካከል ትልቅ ያለመግባባት እንዲፈጠር ያደረገው የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ መሆኑ ነው። ዛሬ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ስለ መንፈስ ቅዱስ የሚያስተምረውን ነገር በአጭሩ እናያለን። ወደፊ ት በተከታታይ በምናያቸው ትምህርቶች ደግሞ ከፍተኛ ያለመግባባት ያለባቸውን ክፍሎች በጥልቀት እንመለከታለን። 

ጥያቄ፡- ሀ) የሐዋ. 1፡4-8፤ 15-17 አንብብ። ከእነዚህ ጥቅሶች ስለ መንፈስ ቅዱስ ምን እንማራለን? ለ) የሐዋ. 2፡1-21፤ 32-33፤ 38-39 አንብብ። 1) መንፈስ ቅዱስ በደቀ መዛሙርት ላይ በወረደ ጊዜ ምን እንደተፈጸመ በራስህ ቋንቋ ግለጥ። 2) በእነዚህ ክፍሎች ውስጥ የሚገኙ ስላ መንፈስ ቅዱስ የተነገሩ አንኳር እውነቶች ምንድን ናቸው? 

1. መንፈስ ቅዱስ በሐዋ. 1-2 ውስጥ 

ሀ. ስለ መንፈስ ቅዱስ መውረድ የተሰጠው ተስፋ፡- የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ የሚጀምረው ኢየሱስ፤ መንፈስ ቅዱስን ለደቀ መዛሙርት እንደሚል ክ በሰጠው የተስፋ ቃል ነው። መንፈስ ቅዱስ ከእግዚአብሔር አብ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ለደቀ መዛሙርት የተሰጠ «ስጦ ታ» ነው። በዚህ ክፍል ውስጥ በርካታ እውነቶችን ማየት ይቻላል። 

1. መጥምቁ ዮሐንስ ኢየሱስ የሚያጠምቀው በእሳትና በመንፈስ ቅዱስ እንደሆነ የተናገረ ሲሆን፥ ኢየሱስ ግን በመንፈስ ቅዱስ እንደሚያጠምቅ ብቻ ተናገረ። ይህ ምናልባት የእሳቱ ጥዏቀት ኢየሱስ በፍርድ ዳግም ላሚመጣበት ጊዜ የዘገየ በመሆኑ ይሆናል። 

2. የመንፈስ ቅዱስ መምጣት የመንፈስ ቅዱስ «ጥምቀት» ተብሎ ይጠራል። በሐዋርያት ሥራ 2 ላይ በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ እንጂ ተጠመቁ ያለማላቱን ልብ ማለት የሚያስገርም ጉዳይ ነው። ይህ የሚያመላክተው በሁለቱ ቃሎች መካከል ያለውን የቅርብ ግንኙነት ነው። 

«ጥምቀት» የሚለውን ቃል በሁለት መንገዶች ልንጠቀምበት እንችላለን። በመጀመሪያ፥ አማኞች በኢየሱስ ሲያምኑ በውኃ መጠመቃቸውን በቀጥታ እንደሚያመላክት አድርገን ልንወስደው እንችላለን። መጥምቁ ዮሐንስ ያደረገው ይህን ነበር (ማር. 1፡4)፥ ኢየሱስ የተቀበለው ይህን ነበር (ማር. 1፡9-11)፥ ኢየሱስም ደቀ መዛሙርት ለአዲስ አማኞች እንዲያደርጉት የነገራቸውም ይህን ነበር (ማቴ. 28፡19)። 

በሁለተኛ ደረጃ ፥ ቃሉ በምሳሌያዊ አቀራረብ አገልግሎት ላይ ውሎ ሊሆን ይችላል። ዮሐንስ ኢየሱስ መንፈስ ቅዱስን ስላመስጠቱ ለማመልከት ተጠቅሞበታል። አዲስ ኪዳን ጥምቀትን ኈሁለት ምክንያቶች በምሳሌያዊ አቀራረብ ሳይጠቀምበት አልቀረም። በመጀመሪያ፥ ከውኃ ጥምቀት ሥርዓት ጋር በቅርብ የተያያዘ ነበር። በአዲስ ኪዳን አንድ ሰው ኢየሱስን እንደ ግል እዛኙ በሚቀበልበት ጊዜና በውኃ በሚጠመቅበት ጊዜ መካከል ምንም መዘግየት አልነበረም። አንድ ሰው ኢየሱስን ሲያምን ወዲያውኑ ይጠመቅ ነበር። አንድ ሰው ኢየሱስን አምኖ ሊጠመቅ ለዚህ አዲስ ክርስቲያን እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን በስጦታ መልክ ይሰጠው ነበር። ሰው ሰውኃ የሚጠመቀውና መንፈስ ቅዱስን በዚያው ጊዜ የሚቀበለው በአንድ ጊዜ ስለሆነ መንፈስ ቅዱስን መቀበል የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት ተብሎ ተጠርቷል። ስሁለተኛ ደረጃ ፥ የውኃ ጥምቀት ሥርዓት ሰው ሙሉ በሙሉ እራሱን ከኢየሱስ ጋር አንድ የሚያደርግበት ምልክት ነበር። የውኃ ጥምቀት እማኙ ከክርስቶስ ሞት፥ መቀበር ና መነሣት ጋር እራሱን አንድ ማድረጉን በድርጊታዊ መግላጭ የሚያሳይበት ሥርዓት ነበር (ሮሜ. 6)። በተመሳሳይ መንገድ የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት መንፈስ ቅዱስ ከአዲሱ ክርስቲያን ጋር እራሱን አንድ ለማድረግ መኖሪያውን በልቡ ሊያደርግ እና የክርስቶስ አካል ከሆነችው ከቤተ ክርስቲያን ጋር ሊያጣምረው እን ደመጣ የሚያሳይ ነበር (1ኛ ቆሮ. 12፡13)። 

(ማስታወሻ፡- ወደፊት በምንመለከተው አንድ ትምህርት የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትን ከመንፈስ ቅዱስ ሙላት ጋር እናወዳድራለን።) 

3. የመንፈስ ቅዱስ ከደቀ መዛሙርት ጋር የመሆን ጉዳይ ከኃይልና ከምስክርነት ጋር ተቆራኝቶ የቀረበ ነው። በዚህ ስፍራ የተጠቀሰው ኃይል ከተአምራትና ከፈውስ ጋር የተያያዘ ለመሆኑ የምናየው ነገር የለም። ይልቁኑ ትኩረቱ ያረፈው ለምስክርነት የሚሆን ኃይልን በማግኘት ላይ ነው (የሐዋ. 2፡19። በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ተቀዳሚ ትኩረት የተሰጠው የመንፈስ ቅዱስ ሚና ይህ ነበር። ኃይሉ በተአምራቶች ውስጥ የታየ ቢሆንም ወንጌልን ለመስበክ ከሚመጣው ኃይል ጋር ቀጥሎ በሁለተኛ ደረጃ የሚመጣ ነው። 

ለ.የብሉይ ኪዳን መጽሐፍ ሊጻፍ የመንፈስ ቅዱስ ሚና፡- ጴጥሮስ መንፈስ ቅዱስ በዳዊት አፍ (ወይም ቅዱሳት ጽሑፎችን በጻፈበት ብእርቹ)ተጠቅሞ የይሁዳን ጥፋት ስለግመልከቱ (የሐዋ. 1፡16) በተናገረው ንቀር በመንፈስ ቅዱስና በብሉይ ኪዳን ጸሐፊዎች መካከል የነበረውን የቅርብ ግንኙነት አሳይቷል። 

ሐ. በበዓለ ኀምሳ ቀን የመንፈስ ቅዱስ በደቀ መዛሙርት ላይ መውረድ፡- (ወደፊት በምንደርስባቸው ትምህርቶች ይህን በጥልቀት እናጠናላን የሐዋ. 2፡1-4)። 

ጥያቄ፡– እነዚህን ሦስት የመንፈስ ቅዱስ ሥራዎች መረዳት ዛሬ ለእኛ ምን ያህል አስፈላጊ ነው? 

ምንጭ፡- “የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ”፣ በቲም ፌሎስ ተጽፎ፣ በጌቱ ግዛው የተተረጎመ እና በኤስ አይ ኤም ጽሑፍ ክፍል የተዘጋጀ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

በመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችና በአምልኮ ልምምዶች ውስጥ ያሉ ልዩነቶችን እንዴት መያዝ አለብን? በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 3-8 )

የጌታ ጸጋ ከእርስዎ ጋር ይሁን፤ ሀሳብዎን ለመስማት ዝግጁ ነን።

Discover more from የሕይወት እንጀራ

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading