የመጽሐፎችና የስልጠና ማኑዋሎች ማህደር
በዚህ ገጽ ላይ አማኞችን ለተለያዩ የአገልግሎት ዘርፎች የሚያበቁ እና በመንፈሳዊ እውቀት የሚያሳድጉ ጠንካራ የትምህርት ግባቶችን በፒዲኤፍ (PDF) ፎርማት አዘጋጅተን አቅርበናል። ጽሁፎቹ በቀላሉ ዳውንሎድ (Download) ተደርገው ለግል ጥናት፣ ለቡድን ውይይትና ለቤተክርስቲያን ስልጠና እንዲውሉ ታስበው የተሰናዱ ናቸው።
የስልጠና ማኑዋሎች (Training Manuals) አማኞች በደቀመዝሙርነት ጉዞ፣ በመሪነት፣ በወንጌል ስርጭት፣ እንዲሁም በመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎችና አሰራሮች ዙሪያ፣ ወዘተ ተግባራዊና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ስልጠናን እንዲያገኙ የሚያስችሉ ቅደም ተከተላዊ መመሪያዎች ናቸው። እያንዳንዱ አማኝ ለቤተክርስቲያን ማነጽ መንፈሳዊ ስጦታውን ለሁሉም ጥቅም በታማኝነት ሊጠቀምበት ይገባል (1 ቆሮ 12:7)። እነዚህ ማኑዋሎች ይህንን የአገልግሎት አቅም ለማዳበር ይረዳሉ።
የአዲስ ኪዳን መጽሐፎች የጥናት መምሪያና ማብራሪያ (New Testament Books Study Guide and Commentary)፦ ከማቴዎስ ወንጌል እስከ ራእይ ድረስ ያሉትን የእያንዳንዱን መጽሐፍ ዋና ዓላማ፣ ታሪካዊ ዳራ፣ ማዕከላዊ መልእክት እና ቲዮሎጂያዊ አስተምህሮ በግልጽ የሚያብራሩ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ ናቸው። እነዚህ ማብራሪያዎች የክርስቶስን ወንጌል አውድና ጥልቀት በትክክል ተረድታችሁ በዕለት ተዕለት ሕይወታችሁ ተግባራዊ እንድታደርጉ ይረዷችኋል።
ጥልቅ የመጽሐፍ ቅዱስ ትንተናዎች (In-Depth Biblical Analyses) በተለያዩ መለኮታዊና ወቅታዊ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥኑ፣ የእግዚአብሔርን ቃል ታሪካዊ፣ ቋንቋዊና መንፈሳዊ አውድ በጠበቀ መልኩ የሚተነትኑ ሰፊ ጽሁፎችን ይዟል። አማኞች መልካሙንና ክፉውን ለመለየት ቸውን በማሰልጠን ወደ ጠንካራ መንፈሳዊ ምግብና ብስለት ሊሸጋገሩ ይገባል (ዕብ 5:14)። እነዚህ የትንተና ጽሁፎች ከስህተት ትምህርት ተጠብቃችሁ በጤናማው ትምህርት ጸንታችሁ እንድትቆሙ ያግዟችኋል።
መጽሐፎቹን እንዴት መጠቀም ይችላሉ?
ለግል ጥናት፡ የሚፈልጉትን ርዕስ በመምረጥ የፒዲኤፍ ፋይሉን ወደ ስልክዎ፣ ታብሌትዎ ወይም ኮምፒውተርዎ ዳውንሎድ በማድረግ በጸሎትና በመንፈስ ቅዱስ ምሪት በጥልቀት ያጠኑት።
ለአነስተኛ ቡድኖችና ለሴል አገልግሎት፡ ማኑዋሎቹን በህብረት ጥናቶች፣ በጸሎት ቡድኖችና በመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ክፍለ ጊዜያት ለማስተማሪያነት ይጠቀሙባቸው።
ለሌሎች ማካፈል፡ ከእግዚአብሔር ቃል ያገኛችሁትን አደራና እውነት ሌሎች ታማኝና ማስተማር የሚችሉ ሰዎችን ለማብቃት አስተላልፉ (2 ጢሞ 2:2)።