የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች ክለሳ
ጥያቄ፡- ሀ) ስለ መንፈስ ቅዱስ ስዚህ ኮርስ የተመላክትናቸውን እውነቶች ዘርዝር። ለ) እነዚህ አገልግሎቶች እያንዳንዳቸው ሕይወትህን የሚነኩት እንዴት ነው? ሐህ እነዚህን አገልግሎቶች እያንዳንዳቸውን ማጥናት አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው? መንፈስ ቅዱስ ማን እንደሆነና ምን እንደሚያደርግ ለመረዳት በጥናታችን ያደረግነው ጉዞ ረጅም ነበር። ዛሬ ቤተ ክርስቲያን በሚከፋፍሉ ዋና ዋና ጉዳዮች ምክንያት አለመግባባቱን የሚያመጡ ርእሰ ጉዳዮችን ለመመልከት ሰፊ ጊዜ ወስደናል። ይህን በማድረጋችን ብዙ ክርስቲያኖች የሚስማሙበትን ስለ መንፈስ ቅዱስ ያላውን ሰፊ ትምህርት በመዘንጋት አደጋ ውስጥ እንወድቃለን። ቀጥሎ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተመለከትናቸው አንዳንድ ዐበይት እውነቶች ተሰጥተዋል። 1) መንፈስ ቅዱስ ማን እንደሆነና ምን እንደሚያደርግ በተቀዳሚ ልንማር የምንችልበት ምንጭ መጽሐፍ ቅዱስ ነው። መንፈስ ቅዱስ ማን እንደሆነና ከእግዚአብሔር አብና ከወልድ ጋር ስላለው ግንኙነት እግዚአብሔር ካልገለጠልን ልናውቅ አንችልም። በሦስት አካላዊ ህልውና የተገለጠ አንድ አምላክን የማምላካችንን እውነት ልንረዳው የምንችለው በሰብአዊ አእምሮ ሥራ ሳይሆን በእምነት ብቻ ነው። መንፈስ ቅዱስ ማን እንደሆነ ግልጽ የሆነ መረዳት ከፈለግን ወደ መጽሐፍ ቅዱስ መመላስ አለብን። መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የገለጠውን ለመመርመር በጥናት መጽሐፋችን ላይ እጅግ ብዙ ጊዜ ያጠፋነው ለዚህ ነው። 2. መንፈስ ቅዱስ የሥላሴ ሦስተኛ አካል ነው። ሀ. ስሙ እራሱ «ቅዱስ» የተለየ ከማንኛውም ተራና ኃጢአታዊ ነገር የተላየ መሆኑን ያመለክተናል። ደግሞም «መንፈስ» ስለሆነ እንደ እኛ ሥጋዊ አካል የለውም። ለ. መንፈስ ቅዱስ የራሱ የሆነ አካላዊ ህልውና አለው። መንፈስ ቅዱስ ሕይወት እንደሌላቸው እንደ ነፋስና እሳት ሳይሆን ሕይወት ያለው ኑባሬ ነው። አንድ ነገር አካላዊ ኑባሬ ያለው መሆኑን የሚያመለክቱ ነገሮች ሁሉ (ለማሰብ የሚችል ስሜት ያለው፥ ለመወሰን የሚችል፥ የሚያዝን፥ ወዘተ…) ለእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስም እውነት ናቸው። ይህ ልናስታውሳቸው ከሚገቡን እጅግ ጠቃሚ እውነቶች አንዱ ነው። ስለዚህ ብዙ ጊዜ መንፈስ ቅዱስን ልንቆጣጠረው የምንችለው፥ የራሱ አካላዊ ህልውና የሌለው ኃይል አድርገን እንቆጥራለን። ይህም ብዙ ክርስቲያን ያልሆኑ ሰዎች አንድ የሚፈልጉትን ነገር ለማግኘት እስማታዊ ኃይልን እንደሚጠቀሙበት ዓይነት ነው። ይህ ችግር በሁለት የተለያዩ መንገዶች ሊፈጸም ይችላል። በመጀመሪያ። ብዙ ክርስቲያኖች መጽሐፍ ቅዱስን በጥብቅ ለመከተል ካላቸው ፍላጎት አንጻር እንደ አስማታዊ መጽሐፍ ይቆጥሩታል። ስለ መጽሐፍ ቅዱስ በቂ እውነቶች ካወቁ ሊያደርጉ የፈለጉትን ነገሮች እንዳከናወኑ ይቆጥራሉ። ስለ መጽሐፍ ቅዱስ እውነቶች ያለን እውቀት ከጉዳት ይጠብቀናል። መንፈሳዊ ያደርገናል። እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ኑሮ እንኖር ዘንድ ኃይል ይሰጠናል። ስለዚህ ሊጣና፥ በቃል ሊያዝና በጥብቅ ሰዎች ሊክተሉት ይገባል። ሆኖም ግን መጽሐፍ ቅዱስን የማጥናት ዓላማችን መጽሐፍ ቅዱስን የበለጠ ለማወቅ መሆን የለበትም። ይልቅ በመጽሐፍ ቅዱስ የተገለጠውን እግዚአብሔርን የበለጠ ለማወቅ እንድንችል ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የምናደርገው አትኩሮት ከመጠን አልፎ ሄዶ የመጽሐፍ ቅዱስ ተቀዳሚ ዓላማ በውስጡ ያለውን ሕያው እግዚአብሔር ለመገናኘት መሆኑን ከዘነጋን አስማታዊ ኃይል እንዳለው መጽሐፍ መቁጠር ጀምረናል ማለት ነው። ሕያው ቃል ከሆነውና አብን ከሚያሳየን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር የምንገናኘው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ነው። መንፈስ ቅዱስ ከአብ ጋር በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በቃሉ ውስጥ እንድንገናኝ ይፈልጋል። እርሱ የራሱ የሆነ አካላዊ ህልውና ስላለው ከእኛ ጋር የግል ግንኙነት ለማድረግ ይፈልጋል። እርሱ ሊረዳን ከጎናችን ያላ አጽናኛችን ነው። መጽሐፍ ቅዱሳችንን በማጥናት ስለ መንፈስ ቅዱስ በማወቃችን ብቻ መንፈስ ቅዱስን እናውቃለን ማለት አይደለም። መንፈስ ቅዱስ አካላዊ ኑባሬ ነው። ከእርሱ ጋር ያለን ግንኙነት ሊያድግና ድምፁን አውቀን የቅርብ ወዳጆች ልንሆን ይገባል። ሁለተኛው፥ አደጋ የቅጽበታዊ ኃይል ምንጭ መሆኑን ለማየት አስማታዊ ኃይል አድርገው መቁጠራቸው ነው። ለእነርሱ የሚያስፈልጋቸውን ነገሮች ለማድረግ ነው እርሱ በዚያ ያለው። ስለዚህ በሚታመሙበት ጊዜ መፈወስ ግዴታው እንደሆነ አድርገው ይጸልያሉ። ምንም ዓይነት ችግር ቢገጥማቸው ከዚያ ችግር እንዲያወጣቸው መንፈስ ቅዱስን ያዛሉ። መንፈስ ቅዱስን እንደ መልካም ዕድል እድራጊ በመቁጠር የሚፈልጉትን እንዲያደርግ ያዙታል። መንፈስ ቅዱስ የምንቆጣጠረው ነገር አይደለም። እንደ ወዳጅ የማያቋረጥ ግንኙነት ከእርሱ ጋር ለማድረግ የምንችለው ዘላለማዊና አካላዊ አምላክ ነው። ልናውቀውና በጊዜ ሂደት ዘላለማዊ የሆነ የቅርብ ግንኙነት ከእርሱ ጋር ልናደርግ ይገባል። እንደ ልዩ ወዳጃችን ከሁሉ በላቀ ሁኔታ ሊረዳን እብሮን አለ። አንዳንድ ጊዜ ከበሽታና ከችግሮች በመታደግ ሊሆን ይችላል። በሌላ ጊዜ ደግሞ በችግሮች ውስጥ ድል እየሰጠ በእርሱ ላይ በመደገፍና ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን በመምሰል እንድናድግ ያደርጋል። እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን አካላዊ ኑባሬ እንደሌለው እስማታዊ ኃይል መቁጠር በፍጹም፥ በፍጹም፥ በፍጹም የሚገባ ነገር አይደለም። ከእርሱ ጋር ጥብቅ ግንኙነት ለማድረግና ግንኙነትህንም ለማሳደግ የምትችልበት የራሱ አካላዊ ኑባሬ እንዳለው አድርገህ ተመልክተው። ጥያቄ፡- ሀ) መንፈስ ቅዱስን እካላዊ ህልውና የሌላው ኃይል ብቻ እንደሆነና የራሳቸውን ፍላጎቶች ለማሟላት እንደሚፈልጉት የሚጠቀሙበት ነገር አድርገው የሚቆጥሩ ምን ያህል ክርስቲያኖች እንዳሉ ግለጽ። ለ) ብዙ ክርስቲያኖች ከመጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔርና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር የግል ግንኙነት ከመመሥረት የመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችና ስለ መንፈስ ቅዱስ የተጻፉ እውነቶችን በማወቅ ላይ የሚያተኩሩት እንዴት ነው? ሐ) ይህ አደገኛ የሚሆነው ለምንድን ነው? ሐ.መንፈስ ቅዱስ እግዚአብሔር ነው። የሥላሴ አንዱ አካል ነው። የመጽሐፍ ቅዱስ ማስረጃ ግልጽ ነው። መንፈስ ቅዱስ ከእግዚአብሔር አብና ከእግዚአብሔር ወልድ ጋር አካል የሆነ ምሉዕ አምላክ ነው። የእግዚአብሔር ኃይል ያለውና እግዚአብሔር ብቻ ሊያደርጋቸው የሚችላቸውን ተግባራት የሚያደርግ ነው። እግዚአብሔር በሦስት ውስጥ ያለ አንድ የመሆኑ ጉዳይ ፈጽሞ ልንረዳው የማንችላው ቢሆንም መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር አንድ መሆኑን ደግሞም የተለያዩ ሦስት የሥላሴ አካላት ነገር ግን በባሕርይም እኩል የሆኑ አምላክ መሆናቸውን በግልጽ ስለሚያስተምር ይህን እውነት በእምነት መቀበል አለብን። 3. ስለ መንፈስ ቅዱስ በብሉይ ኪዳንና በወንጌላት የተሰጡ እውነቶች። መንፈስ ቅዱስ በመጽሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ በሙሉ የተገለጠ ቢሆንም በብሉይ ኪዳን የነበረውን አገልግሎት ለመረዳት የአዲስ ኪዳን መገለጥ ያስፈልገናል። ሀ. በብሉይ ኪዳን መንፈስ ቅዱስ በሁለት ዋና ዋና መንገዶች ይሠራ ነበር። በመጀመሪያ፥ በመፍጠር ሥራ ይሳተፍ ነበር። በተለይ በመፍጠርና የተፈጠሩትን በሕይወት በማቆየት ሥራ ነበር። በሁለተኛ ደረጃ: አንዳንድ መሪዎችን (መሳፍንት፥ ነገሥታት፥ ነቢያት) ኃይል በማስታጠቅ ይሠራ ነበር። ኃይል የሚያስታጥቃቸው የእግዚአብሔርን ሕዝብ በጥበብና በኃይል እንዲመሩ ነበር። መንፈስ ቅዱስ ኃይል የማስታጠቅ አገልግሎቱ ለአማኞች በሙሉ ሳይሆን ለተወሰኑ ሰዎች ብቻ ነበር። በተጨማሪ ይህ አገልግሎት የጊዜ ገደብም ነበረው፤ ማለትም ሥራው በሚጠናቀቅ ወይም ኃይሉን የተቀበለው ሰው ትልቅ ኃጢአት በሚያደርግበት ጊዜ ሰውዬውን ትቶ ይሄድ ነበር። በብሉይ ኪዳን መጨረሻ ነቢያት መንፈስ ቅዱስ ከእግዚአብሔር ልጆች ሁሉ ጋር በጥልቀት አብሮ የሚሆንበት አዲስ ዘመን እንደሚመጣ እሻረው ተመለከቱ። ይህ ዘመን በመጣ ጊዜ መንፈስ ቅዱስ እግዚአብሔርን እንዲታዘዙና እንዲያገለግሉ እንደሚያስችላቸው ነበር። ለ. በወንጌላት ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ተቀዳሚ አገልግሎት ግልጽ ሆነ። በመጀመሪያ መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ በሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወት ውስጥ በቅርብ የሚኖረውን ሕይወት በምሳሌነት አሳየ። ኢየሱስ እግዚአብሔር አብ እንዲሠራው የፈለገውን ነገር ሁሉ የሠራው በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ነው። በሁለተኛ ደረጃ፥ መንፈስ ቅዱስ ከኢየሱስ ጋር የነበረውን ዓይነት ኅብረት ከአማኞች ሁሉ ጋር የሚያደርግበት ጊዜ እንደሚመጣ ኢየሱስ ያመለክታል። ኢየሱስ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከተመለሰ በኋላ መንፈስ ቅዱስ ለእያንዳንዱ ክርስቲያን አጽናኝ፥ መምህር፥ ጓደኛና ኃይል ሰጪ ይሆናል። 4. መንፈስ ቅዱስ በክርስቲያን ሕይወት ውስጥ ያለው አገልግሎት። ስለ መንፈስ ቅዱስ እያደገ በሚመጣ ሂደት በሐዋርያት ሥራና በመልእክቶች ውስጥ የተሰጡ ትምህርቶችን ከሰው ከመመልከት ይልቅ አሁን እየተሳተፈባቸው ያሉ የተለያዩ አገልግሎቶችን እንመለከታለን። ቀጥሎ የእነዚህ አገልግሎቶች ማጠቃለያ ቀርቧል። ሀ. ኃጢአትና ውጤቶቹ በዓለም እንዳይስፋፉ በማድረግ አጠቃላይ እገልግሎት ውስጥ መንፈስ ቅዱስ ይሳተፋል። በዓለም ላይ መንፈስ ቅዱስ ባይኖር ኖሮ የሰው ልጅ ኃጢአት እሁን ካለበት በላይ እጅግ አድጎ በአጭር ጊዜ ውስጥ ራሱኑ መልሶ ያጠፋው ነበር። ለ. መንፈስ ቅዱስ፥ የማያምን ሰው ኃጢአተኝነቱን ተረድቶ ለደኅንነቱ : በኢየሱስ ክርስቶስ ማመን እንዳለበት በማሳወቅ ተግባር ይሳተፋል። መንፈስ ቅዱስ የግለሰቡን መንፈሳዊ ዓይኖች በመክፈት ኃጢአተኛነቱን እግዚአብሔር እንደሚያየው እንዲያይና ኢየሱስንም ከኃጢአትና ከሞት የማምለጫው ብቸኛ መንገድ አድርጎ እንዲመለከት ያስችላዋል። በዚህ ሁኔታ
የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች ክለሳ Read More »