የሕይወት እንጀራ

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች ክለሳ

ጥያቄ፡- ሀ) ስለ መንፈስ ቅዱስ ስዚህ ኮርስ የተመላክትናቸውን እውነቶች ዘርዝር። ለ) እነዚህ አገልግሎቶች እያንዳንዳቸው ሕይወትህን የሚነኩት እንዴት ነው? ሐህ እነዚህን አገልግሎቶች እያንዳንዳቸውን ማጥናት አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው?  መንፈስ ቅዱስ ማን እንደሆነና ምን እንደሚያደርግ ለመረዳት በጥናታችን ያደረግነው ጉዞ ረጅም ነበር። ዛሬ ቤተ ክርስቲያን በሚከፋፍሉ ዋና ዋና ጉዳዮች ምክንያት አለመግባባቱን የሚያመጡ ርእሰ ጉዳዮችን ለመመልከት ሰፊ ጊዜ ወስደናል። ይህን በማድረጋችን ብዙ ክርስቲያኖች የሚስማሙበትን ስለ መንፈስ ቅዱስ ያላውን ሰፊ ትምህርት በመዘንጋት አደጋ ውስጥ እንወድቃለን። ቀጥሎ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተመለከትናቸው አንዳንድ ዐበይት እውነቶች ተሰጥተዋል።  1) መንፈስ ቅዱስ ማን እንደሆነና ምን እንደሚያደርግ በተቀዳሚ ልንማር የምንችልበት ምንጭ መጽሐፍ ቅዱስ ነው። መንፈስ ቅዱስ ማን እንደሆነና ከእግዚአብሔር አብና ከወልድ ጋር ስላለው ግንኙነት እግዚአብሔር ካልገለጠልን ልናውቅ አንችልም። በሦስት አካላዊ ህልውና የተገለጠ አንድ አምላክን የማምላካችንን እውነት ልንረዳው የምንችለው በሰብአዊ አእምሮ ሥራ ሳይሆን በእምነት ብቻ ነው። መንፈስ ቅዱስ ማን እንደሆነ ግልጽ የሆነ መረዳት ከፈለግን ወደ መጽሐፍ ቅዱስ መመላስ አለብን። መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የገለጠውን ለመመርመር በጥናት መጽሐፋችን ላይ እጅግ ብዙ ጊዜ ያጠፋነው ለዚህ ነው።  2. መንፈስ ቅዱስ የሥላሴ ሦስተኛ አካል ነው።  ሀ. ስሙ እራሱ «ቅዱስ» የተለየ ከማንኛውም ተራና ኃጢአታዊ ነገር የተላየ መሆኑን ያመለክተናል። ደግሞም «መንፈስ» ስለሆነ እንደ እኛ ሥጋዊ አካል የለውም።  ለ. መንፈስ ቅዱስ የራሱ የሆነ አካላዊ ህልውና አለው። መንፈስ ቅዱስ ሕይወት እንደሌላቸው እንደ ነፋስና እሳት ሳይሆን ሕይወት ያለው ኑባሬ ነው። አንድ ነገር አካላዊ ኑባሬ ያለው መሆኑን የሚያመለክቱ ነገሮች ሁሉ (ለማሰብ የሚችል ስሜት ያለው፥ ለመወሰን የሚችል፥ የሚያዝን፥ ወዘተ…) ለእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስም እውነት ናቸው። ይህ ልናስታውሳቸው ከሚገቡን እጅግ ጠቃሚ እውነቶች አንዱ ነው። ስለዚህ ብዙ ጊዜ መንፈስ ቅዱስን ልንቆጣጠረው የምንችለው፥ የራሱ አካላዊ ህልውና የሌለው ኃይል አድርገን እንቆጥራለን። ይህም ብዙ ክርስቲያን ያልሆኑ ሰዎች አንድ የሚፈልጉትን ነገር ለማግኘት እስማታዊ ኃይልን እንደሚጠቀሙበት ዓይነት ነው።  ይህ ችግር በሁለት የተለያዩ መንገዶች ሊፈጸም ይችላል። በመጀመሪያ። ብዙ ክርስቲያኖች መጽሐፍ ቅዱስን በጥብቅ ለመከተል ካላቸው ፍላጎት አንጻር እንደ አስማታዊ መጽሐፍ ይቆጥሩታል። ስለ መጽሐፍ ቅዱስ በቂ እውነቶች ካወቁ ሊያደርጉ የፈለጉትን ነገሮች እንዳከናወኑ ይቆጥራሉ። ስለ መጽሐፍ ቅዱስ እውነቶች ያለን እውቀት ከጉዳት ይጠብቀናል። መንፈሳዊ ያደርገናል። እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ኑሮ እንኖር ዘንድ ኃይል ይሰጠናል። ስለዚህ ሊጣና፥ በቃል ሊያዝና በጥብቅ ሰዎች ሊክተሉት ይገባል። ሆኖም ግን መጽሐፍ ቅዱስን የማጥናት ዓላማችን መጽሐፍ ቅዱስን የበለጠ ለማወቅ መሆን የለበትም። ይልቅ በመጽሐፍ ቅዱስ የተገለጠውን እግዚአብሔርን የበለጠ ለማወቅ እንድንችል ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የምናደርገው አትኩሮት ከመጠን አልፎ ሄዶ የመጽሐፍ ቅዱስ ተቀዳሚ ዓላማ በውስጡ ያለውን ሕያው እግዚአብሔር ለመገናኘት መሆኑን ከዘነጋን አስማታዊ ኃይል እንዳለው መጽሐፍ መቁጠር ጀምረናል ማለት ነው።  ሕያው ቃል ከሆነውና አብን ከሚያሳየን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር የምንገናኘው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ነው። መንፈስ ቅዱስ ከአብ ጋር በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በቃሉ ውስጥ እንድንገናኝ ይፈልጋል። እርሱ የራሱ የሆነ አካላዊ ህልውና ስላለው ከእኛ ጋር የግል ግንኙነት ለማድረግ ይፈልጋል። እርሱ ሊረዳን ከጎናችን ያላ አጽናኛችን ነው። መጽሐፍ ቅዱሳችንን በማጥናት ስለ መንፈስ ቅዱስ በማወቃችን ብቻ መንፈስ ቅዱስን እናውቃለን ማለት አይደለም። መንፈስ ቅዱስ አካላዊ ኑባሬ ነው። ከእርሱ ጋር ያለን ግንኙነት ሊያድግና ድምፁን አውቀን የቅርብ ወዳጆች ልንሆን ይገባል።  ሁለተኛው፥ አደጋ የቅጽበታዊ ኃይል ምንጭ መሆኑን ለማየት አስማታዊ ኃይል አድርገው መቁጠራቸው ነው። ለእነርሱ የሚያስፈልጋቸውን ነገሮች ለማድረግ ነው እርሱ በዚያ ያለው። ስለዚህ በሚታመሙበት ጊዜ መፈወስ ግዴታው እንደሆነ አድርገው ይጸልያሉ። ምንም ዓይነት ችግር ቢገጥማቸው ከዚያ ችግር እንዲያወጣቸው መንፈስ ቅዱስን ያዛሉ። መንፈስ ቅዱስን እንደ መልካም ዕድል እድራጊ በመቁጠር የሚፈልጉትን እንዲያደርግ ያዙታል። መንፈስ ቅዱስ የምንቆጣጠረው ነገር አይደለም። እንደ ወዳጅ የማያቋረጥ ግንኙነት ከእርሱ ጋር ለማድረግ የምንችለው ዘላለማዊና አካላዊ አምላክ ነው። ልናውቀውና በጊዜ ሂደት ዘላለማዊ የሆነ የቅርብ ግንኙነት ከእርሱ ጋር ልናደርግ ይገባል። እንደ ልዩ ወዳጃችን ከሁሉ በላቀ ሁኔታ ሊረዳን እብሮን አለ። አንዳንድ ጊዜ ከበሽታና ከችግሮች በመታደግ ሊሆን ይችላል። በሌላ ጊዜ ደግሞ በችግሮች ውስጥ ድል እየሰጠ በእርሱ ላይ በመደገፍና ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን በመምሰል እንድናድግ ያደርጋል።  እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን አካላዊ ኑባሬ እንደሌለው እስማታዊ ኃይል መቁጠር በፍጹም፥ በፍጹም፥ በፍጹም የሚገባ ነገር አይደለም። ከእርሱ ጋር ጥብቅ ግንኙነት ለማድረግና ግንኙነትህንም ለማሳደግ የምትችልበት የራሱ አካላዊ ኑባሬ እንዳለው አድርገህ ተመልክተው።  ጥያቄ፡- ሀ) መንፈስ ቅዱስን እካላዊ ህልውና የሌላው ኃይል ብቻ እንደሆነና የራሳቸውን ፍላጎቶች ለማሟላት እንደሚፈልጉት የሚጠቀሙበት ነገር አድርገው የሚቆጥሩ ምን ያህል ክርስቲያኖች እንዳሉ ግለጽ። ለ) ብዙ ክርስቲያኖች ከመጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔርና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር የግል ግንኙነት ከመመሥረት የመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችና ስለ መንፈስ ቅዱስ የተጻፉ እውነቶችን በማወቅ ላይ የሚያተኩሩት እንዴት ነው? ሐ) ይህ አደገኛ የሚሆነው ለምንድን ነው?  ሐ.መንፈስ ቅዱስ እግዚአብሔር ነው። የሥላሴ አንዱ አካል ነው። የመጽሐፍ ቅዱስ ማስረጃ ግልጽ ነው። መንፈስ ቅዱስ ከእግዚአብሔር አብና ከእግዚአብሔር ወልድ ጋር አካል የሆነ ምሉዕ አምላክ ነው። የእግዚአብሔር ኃይል ያለውና እግዚአብሔር ብቻ ሊያደርጋቸው የሚችላቸውን ተግባራት የሚያደርግ ነው። እግዚአብሔር በሦስት ውስጥ ያለ አንድ የመሆኑ ጉዳይ ፈጽሞ ልንረዳው የማንችላው ቢሆንም መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር አንድ መሆኑን ደግሞም የተለያዩ ሦስት የሥላሴ አካላት ነገር ግን በባሕርይም እኩል የሆኑ አምላክ መሆናቸውን በግልጽ ስለሚያስተምር ይህን እውነት በእምነት መቀበል አለብን።  3. ስለ መንፈስ ቅዱስ በብሉይ ኪዳንና በወንጌላት የተሰጡ እውነቶች። መንፈስ ቅዱስ በመጽሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ በሙሉ የተገለጠ ቢሆንም በብሉይ ኪዳን የነበረውን አገልግሎት ለመረዳት የአዲስ ኪዳን መገለጥ ያስፈልገናል።  ሀ. በብሉይ ኪዳን መንፈስ ቅዱስ በሁለት ዋና ዋና መንገዶች ይሠራ ነበር። በመጀመሪያ፥ በመፍጠር ሥራ ይሳተፍ ነበር። በተለይ በመፍጠርና የተፈጠሩትን በሕይወት በማቆየት ሥራ ነበር። በሁለተኛ ደረጃ: አንዳንድ መሪዎችን (መሳፍንት፥ ነገሥታት፥ ነቢያት) ኃይል በማስታጠቅ ይሠራ ነበር። ኃይል የሚያስታጥቃቸው የእግዚአብሔርን ሕዝብ በጥበብና በኃይል እንዲመሩ ነበር። መንፈስ ቅዱስ ኃይል የማስታጠቅ አገልግሎቱ ለአማኞች በሙሉ ሳይሆን ለተወሰኑ ሰዎች ብቻ ነበር። በተጨማሪ ይህ አገልግሎት የጊዜ ገደብም ነበረው፤ ማለትም ሥራው በሚጠናቀቅ ወይም ኃይሉን የተቀበለው ሰው ትልቅ ኃጢአት በሚያደርግበት ጊዜ ሰውዬውን ትቶ ይሄድ ነበር።  በብሉይ ኪዳን መጨረሻ ነቢያት መንፈስ ቅዱስ ከእግዚአብሔር ልጆች ሁሉ ጋር በጥልቀት አብሮ የሚሆንበት አዲስ ዘመን እንደሚመጣ እሻረው ተመለከቱ። ይህ ዘመን በመጣ ጊዜ መንፈስ ቅዱስ እግዚአብሔርን እንዲታዘዙና እንዲያገለግሉ እንደሚያስችላቸው ነበር።  ለ. በወንጌላት ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ተቀዳሚ አገልግሎት ግልጽ ሆነ። በመጀመሪያ መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ በሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወት ውስጥ በቅርብ የሚኖረውን ሕይወት በምሳሌነት አሳየ። ኢየሱስ እግዚአብሔር አብ እንዲሠራው የፈለገውን ነገር ሁሉ የሠራው በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ነው።  በሁለተኛ ደረጃ፥ መንፈስ ቅዱስ ከኢየሱስ ጋር የነበረውን ዓይነት ኅብረት ከአማኞች ሁሉ ጋር የሚያደርግበት ጊዜ እንደሚመጣ ኢየሱስ ያመለክታል። ኢየሱስ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከተመለሰ በኋላ መንፈስ ቅዱስ ለእያንዳንዱ ክርስቲያን አጽናኝ፥ መምህር፥ ጓደኛና ኃይል ሰጪ ይሆናል።  4. መንፈስ ቅዱስ በክርስቲያን ሕይወት ውስጥ ያለው አገልግሎት። ስለ መንፈስ ቅዱስ እያደገ በሚመጣ ሂደት በሐዋርያት ሥራና በመልእክቶች ውስጥ የተሰጡ ትምህርቶችን ከሰው ከመመልከት ይልቅ አሁን እየተሳተፈባቸው ያሉ የተለያዩ አገልግሎቶችን እንመለከታለን። ቀጥሎ የእነዚህ አገልግሎቶች ማጠቃለያ ቀርቧል።  ሀ. ኃጢአትና ውጤቶቹ በዓለም እንዳይስፋፉ በማድረግ አጠቃላይ እገልግሎት ውስጥ መንፈስ ቅዱስ ይሳተፋል። በዓለም ላይ መንፈስ ቅዱስ ባይኖር ኖሮ የሰው ልጅ ኃጢአት እሁን ካለበት በላይ እጅግ አድጎ በአጭር ጊዜ ውስጥ ራሱኑ መልሶ ያጠፋው ነበር።  ለ. መንፈስ ቅዱስ፥ የማያምን ሰው ኃጢአተኝነቱን ተረድቶ ለደኅንነቱ : በኢየሱስ ክርስቶስ ማመን እንዳለበት በማሳወቅ ተግባር ይሳተፋል። መንፈስ ቅዱስ የግለሰቡን መንፈሳዊ ዓይኖች በመክፈት ኃጢአተኛነቱን እግዚአብሔር እንደሚያየው እንዲያይና ኢየሱስንም ከኃጢአትና ከሞት የማምለጫው ብቸኛ መንገድ አድርጎ እንዲመለከት ያስችላዋል። በዚህ ሁኔታ

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች ክለሳ Read More »

የመንፈስ ቅዱስ ሁለተኛ ዋና ተግባሩ፡- ወደ ኢየሱስ ማመልከትና እርሱን እንድንመስል ማድረግ።

ሁሴን እስላም ነበር። አንድ ቀን ታዋቂ ክርስቲያን የሆነ ሰባኪ ሰው እንደመጣና የፈውስ ፕሮግራም እንደሚያካሂድ ሰማ። ሁኔታውን ለማጣራት ስለጓጓ ወደ ሥፍራው ሄደ። ለብዙ ዓመታት ታምሞ የነበረ ሰው ሊፈወስ ተመለከተ። ሁሴን የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ኃይል ስለተመለከተ በኢየሱስ አመነ። ያመነበት ምክንያት ኃጢአተኛ መሆኑን ኢየሱስ ከኃጢአቱ እንዲያነጻው እንደሚያስፈልግ በመገንዘብ አልነበረም። ነገር ግን ለዚያ ኃይል ቅርብ ለመሆን በመፈለግ ነው። በየሳምንቱ ወደ ቤተ ክርስቲያን መመላለስ ጀመረ። እግዚአብሔር ሰውን ሁሉ እንደማይፈውስ በተገነዘበ ጊዜ ቀን ተስፋ ቆረጠ። ሁሴን እግዚአብሔር ሰዎችን የፈወሰባቸውን ጊዜያት በተጨማሪ ተመልክቷል። ይህ ቀን ለእርሱ የሚያስደንቅ መሆኑ ቀረ። እግዚአብሔር በየጊዜው የተሻሉና ትላልቅ ተአምራትን እንዲያደርግ ፈለገ። ይህ ያልሆነው ምናልባት በዚያ ቤተ ክርስቲያን የነበሩ ሰዎች እምነት ጉድለት ሊሆን ይችላል። ትላልቅ ተአምራት የሚደረግበት ሌላ ቤተ ክርስቲያን እንዳለ ሰማ። በዚያ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተአምራትን የሚያደርግ ሰው ነበር። ኃይሉ ታላቅ ከመሆኑ የተነሣ ሰዎች በየመድረኩ ራሳቸውን ስተው እስከሚወድቁ ይደርሱ ነበር። ሁሴን መጀመሪያ የነበረበትን ቤተ ክርስቲያን ትቶ ወደዚያች ቤተ ክርስቲያን ሄደ። ከጥቂት ጊዜ በኋላ በዚህ ቤተ ክርስቲያንም እርካታ እጥቶ ከዚያ የላቀ ተአምራት እንደሚደረግ ወደ ሰማበት ሌላ ቤተ ክርስቲያን ሄደ። ሁሴን የሚፈልገው ነገር ቢኖር የተአምራት መስካሪና እድናቂ መሆን ነበር። በእግዚአብሔር እውቀትና በቃሉ ላማደግ የነበረው አትኩሮት ዝቅተኛ ነበር። ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን በባሕርይ ለመምሰል የሚያደርገው ጥረት አልነበረም። አንድ ቀን ሚስቱ ታማ ሞተች። ቢጸልይላትም፥ ተአምራትን ሠሪዎች ወደ እርሱ በማምጣት እንዲጸልዩላት ቢያደርግም አልተሳካላቸውም። ከሞተች በኋላ እምነቱን በመካድ ወደ መጀመሪያ ቅርሱ ወደ እስልምናው ተመለሰ።  ጥያቄ፡- ሀ) ብዙ ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ኃይል የሚማረኩትና ተአምራትንና ሌሎች ትላልቅ ነገሮችን ለማየት የሚፈልጉት ለምን ይመስልሃል? ለ) መንፈስ ቅዱስ በሰዎች ሕይወት ውስጥ በየዕለቱ ቀስ በቀለ በሚያመጣው ጸጥተኛ የለውጥ አሠራር ብዙ ሰዎች የማይነኩት ለምንድን ነው? ሐ) በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ላይ ከሚገባ በላይ አትኩሮት መስጠት ወደ ስሕተት ትምህርቶች እንዴት ሊመራ እንደሚችል ምሳሌዎችን ስጥ። መ) በእውቀት በጥልቀት ባለማደጋቸው ምክንያት ክእምነት ስተው የወደቁ እንደ ሁሴን ያሉ ሰዎችን ምሳሌዎች ጥቀስ።   ሰዎች ሊያሸንፉት ወይም ሊያመልኩት በሚከብዳቸው ኃይል ላይ የመደናቀፍ ነገር አላቸው። ሰዎች በቤተ ክርስቲያንም ሆነ በመንግሥት መሥሪያ ቤት ውስጥ መሪዎች ለመሆን የሚፈልጉበት አንድ ምክንያት ሌሎችን ለመቆጣጠር ኃይል ለማግኘት ስለሚፈልጉ ነው። ሰዎች በተጨማሪ ኃይልን የሚገልጽ ማለትም የመንፈስ ቅዱስን ኃይል የሚገልጽ የሚማርኩ አስደናቂ ተአምራትን ማየት ይወዳሉ። ካልተጠነቀቅን በስተቀር እንዲህ ዓይነቱ ለአስደናቂ ነገሮች የመሳብ አዝማሚያ፥ ሱስ እንደሚያሲዙ መድኃኒቶች የሚሠራ በመሆኑ ይበልጥ ታላላቅ ኃይል ያላቸውን ተአምራት ለማየት እንድንጓጓ ያደርገናል። የእሳት እራት ወደ ሻማ ብርሃን እጅግ እየተሳበች በነበልባሉ ተቃጥላ እንደምትጠፋ ሁሉ ተአምራትን ብቻ ለማየት ብለን በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ከተሳብን ሚዛናዊነት ልናጣና ሕይወታችን የተበላሸ ሊሆን ይችላል። የመንፈስ ቅዱስን ኃይልና አገልግሎት በሚገባ ስፍራ ሰጥተን ማክበር ሲኖርብንም እንኳ የመንፈስ ቅዱስን አገልግሎት መመልከት ያለብን መጽሐፍ ቅዱስ ከሚያስተምረው መሠረት አኳያ እንጂ አድናቆትን ከሚፈጥሩ የመንፈስ ቅዱስ እገልሎተች አኳያ መሆን የለበትም።  የመንፈስ ቅዱስ ዋና ሥራ ምንድን ነው? ለሚለው ጥያቄ ዛሬ በቤተ ክርስቲያን ውስጥም ሆነ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ የተንጸባረቁ በርካታ የተለያዩ አመለካከቶች አሉ። አንዳንዶች መንፈስ ቅዱስ ከኃጢአት እኛን ለማንጻት ባለው ፍላጎት ላይ በማተኮር የመንፈስ ቅዱስ ተቀዳሚ አገልግሎት ሰውን መቀደስ ነው ይላሉ። ሌሎች በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ላይ በማተኮር የመንፈስ ቅዱስ ተቀዳሚ አገልግሎት በቤተ ክርስቲያን ውስጥና በቤተ ክርስቲያን በኩል ተአምራትን ማድረግ ነው ይላሉ። እነዚህ ተአምራት መንፈስ ቅዱስ በሕይወታችን እንደሚኖር ያረጋግጣሉ ይላሉ።  ነገር ግን ወደ ጥያቄው እንመለስና «መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ተቀዳሚ አገልግሎት ምን ያስተምረናል?» መንፈስ ቅዱስ ማን እንደሆነና በሕይወታችን ምን ለማድረግ እንደሚፈልግ ለመወሰን የምንጠቀምባቸው ሌሎች መንገዶች ሁሉ አደገኛ ናቸው። አመለካከታቸውና ተግባሮቻቸው በእግዚአብሔር ቃል ላይ ይመዘኑ ዘንድ የማይፈቅዱ እንዳንድ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ፍጹም እውነት የለም ከሚሉ ጋር በሚናወጥ መሠረት ላይ የቆሙ ናቸው። «የተሰማን ነገር በሙሉ፥ በልባችን የምናምነው ነገር ሁሉ ትክክል ነው» በማለት ያስተምራሉ። ስለዚህ እውነትን የሚመዝኑት እንደ መጽሐፍ ቅዱስ ባለ ፍጹም መመዘኛ ሳይሆን በስሜታቸው ነው። ይህ አመለካከት ዛሬ በስሩት በተለመደው «መንገዶች ሁሉ ወደ እግዚአብሔር ያደርሳሉ» ከሚለው የሐሰት ትምህርት ጋር ተመሳሳይ ነው። «ቅንና እውነተኛ እስከሆንን ድረስ ሙስሊም፥ ቡድሂስት፡ ኦርቶዶክስ ወይም ዛፍ እምላኪ እንኳ ብንሆን ሁሉም ቅንነት የሞላባቸው ስለሆኑ ትክክል ናቸው» ይላሉ። ይህ የሰይጣን ውሸት የአዲስ ዘመን እንቅስቃሴ፥ የዓለም አቀፍ አብያተ ክርስቲያናት እንቅስቃሴና በዘመናችን ያሉ በርካታ የሐሰት ሃይማኖቶች እምብርት ነው። አንድ እርጠኛ የማይነቃነቅ የእውነት ምንጭ ብቻ አለ። እርሱም መጽሐፍ ቅዱስ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ የሚያስተምራቸውን እውነቶች ልናምንባቸውና ልንቆምላቸው ይገባል። ግልጽ ትምህርት ያልተሰጠባቸው እውነቶች ወይም አመላካክቶችን ሁሉ እግዚአብሔር ቃል ጋር ለመስማማት ጥረት እስካደረጉ ድረስ ያላቸውን መብት ልንጠብቅላቸው ይገባል።  ጥያቄ፡- ሀ) አንዳንድ ክርስቲያኖች አመላካከቶቻቸው ወይም ትምህርቶቻቸው በመጽሐፍ ቅዱስ ሚዛን መመዘናቸውን የሚፈሩት ለምንድን ነው? ለ) አመለካከቶቻችን በእግዚአብሔር ቃል ያላመመዘናቸው አደጋ ምንድን ነው?  የእግዚአብሔር ተቀዳሚ ዓላማ በዓለም ውስጥ።  ጥያቄ፡- የሚከተሉትን ጥቅሶች ተመልከት። ቈላ. 5-23፤ 2ኛ ቆሮ. 5፡18-20፤ ሮሜ 8፡29። ስለ እግዚአብሔር ዓላማዎችና በዘመናችን እያደረጋቸው ስላሉ ነገሮች ምን ያስተምራሉ?  የመንፈስ ቅዱስን አገልግሎት ለመረዳት የእግዚአብሔርን ተቀጓሚ ዓላማ መረዳት ያስፈልገናል። የእግዚአብሔር ዘላለማዊ ዕቅዶች ዋና ማዕክል ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። የብሉይ ኪዳን ትምህርቶችና ተስፋዎች በሙሉ ወደ እርሱ ያመለክታሉ። አዲስ ኪዳን በሞላ የእግዚአብሔርን ዘላለማዊ ዕቅድ የሚፈጽም እርሱ እንደሆነም ያመላክታል። ስለ ኢየሱስ የተነገሩትን የሚከተሉትን ነገሮች ልብ በል።  1 ኢየሱስ እግዚአብሔር አብን በሙላት የሚወክል ነው። ወደ ምድር የመጣው እግዚአብሔር ምን እንደሚመስል ለሰው ልጆች በግልጽ ለማሳየት ነው። ስለዚህ ኢየሱስን ያየ አብን አይቷል ተብሎ ተነግሮናል (ዕብ 1፡3፤ ቈላ. ፡9)።  2. ኢየሱስ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ስሙላት ለሌሎች የሚገልጥ የእግዚአብሔር ቃል ነው (ዮሐ 1፡1-5፤ ዕብ. 1፡1-2)።  3 ኢየሱስ ዓለምን ከእግዚአብሔር ጋር ለማስታረቅ የመጣ ነው። በኢየሱስ በሰማይና በምድር ያሉ ነገሮች በሙሉ ወደ ፍጹም አንድነት ይጠቀላላሉ። ኢየሱስ ታሪክን በሙሉ ነገሮችንም ሁሉ ለእግዚአብሔር ወደ መታዘዝ እንደገና መልሶአቸዋል (ኤፌ. 1፡10፤ ቆላ. 1፡20)።  4. ኢየሱስ በእርሱ ውስጥና በእርሱ በኩል እግዚአብሔር አብ የሚመለክበት አዲስ አካልን ይኽውም ቤተ ክርስቲያንን የሚነሳ ነው (ኤፌ. 20-23)።  ስለዚህ የአዲስ ኪዳን ዋና ነጥብ መንፈስ ቅዱስ ሳይሆን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እርሱ የእምነታችን ራስና ፈጻሚ (ዕብ 12፡2) ማዕከልና መሠረት ነው። የቤተ ክርስቲያን ዋና ትምህርትና ዋና አምልኮ ሁልጊዜ ማመልክት ያለበት ወደ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በእርሱም በኩል ወደ እዚአብሔር አብ ነው። ከዚህ የምንመለከተው ማንኛውም የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር በጥብቅ መቆራኘት እንዳለበት ነው። የእግዚአብሔር ዕቅድ «ጉልበት ሁሉ ለኢየሱስ ይንበረክክ ዘንድ» (ፊልጵ. 29=ህ ከሆነ የመንፈስ ቅዱስ ተቀዳሚ ሥራ ከዚህ ጋር የሚስማማና ይህ እንዲከናወንም የሚፈልግ መሆን እንዳለበት እንጠብቃለን።  መንፈስ ቅዱስ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ያለው ግንኙነት  ጥያቄ፡- የሚክተሉትን ጥቅሶች ተመልከት። ዮሐ 14፡2818፡26-27 16፡12-15። እነዚህ ጥቅሶች መንፈስ ቅዱስ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ያለውን ግንኙነት እንዴት ያሳያሉ?  በመላው አዲስ ኪዳን መንፈስ ቅዱስ ከኢየሱስ ጋር ተቆራኝቶ ከመቅረቡ የተነሣ «የኢየሱስ መንፈስ» ተብሎ ተጠርቷል። በምድር ላይ በነበረ ጊዜ ያለማቋረጥ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ የሆነው ኢየሱስ ያንኑ መንፈስ ቅዱስ ለእውነተኛ ክርስቲያኖች ሁሉ ሰጠ። መንፈስ ቅዱስ ወደ አማኙ ልብ ከመግባቱ ጋር ኢየሱስ ክርስቶስ እራሱ ወደ ሕይወቱ ይመጣል (ሮሜ 8፡9-11)። በአዲስ ኪዳን በሞላ ኢየሱስ ክርስቶስና መንፈስ ቅዱስ እጅግ ተቆራኝተው ስለቀረቡ አንዱን ማግኘት ሌላውንም ማግኘት ነው (2ኛ ቆሮ. 3፡17-18)።  ኢየሱስ ከመሞቱ በፊት ለደቀ መዛሙርቱ ስለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ አስተማራቸው። ኢየሱስ፥ ላደቀ መዛሙርቱ ስለ መንፈስ ቅዱስ በሚያስተምራቸው ወቅት ስለ መንፈስ ቅዱስ ኃይል፥ ስለ ሚሠራቸው ተአምራት፥ በልሳናት ስለ መናገር፥ ስለ ፈውሶች፥ ስለ መንፈሳዊ ስጦታዎች፥

የመንፈስ ቅዱስ ሁለተኛ ዋና ተግባሩ፡- ወደ ኢየሱስ ማመልከትና እርሱን እንድንመስል ማድረግ። Read More »

የመጀመሪያው የመንፈስ ቅዱስ ዋና ሥራ፡- ዘላለማዊው አምላክ በውስጣችን መኖሩ

በመንፈስ ቅዱስ ላይ ያደረግነው ጥናት ሰፊ የነበረ ሲሆን ብዙ የተለያዩ አወዛጋቢ ርእሶችንም ተመልክተናል። በዚህ ሂደት ስለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ መማር ብቻ ሳይሆን ከእግዚአብሔር ጋር ባላችሁ ኅብረትሦ እንዳደጋችሁ እምነቴ ነው። በመንፈስ ቅዱስ ርእሰ ጉዳይ ላይ በሚደረግ እንደዚህ ዓይነት ዝርዝር ጥናት መካከል ስለ መንፈስ ቅዱስ እጅግ አስፈላጊ የሆነ ትምህርቶችን የመዘንጋት ዕድሉ የቀለለ ነው። ስለዚህ የዚህ ትምህርት ዓላማ እጅግ አስፈላጊ የሆኑ መሠረታዊ የእምነት ትምህርቶችን መከለስ ነው።  ጥያቄ፡– ከሁሉ የላቁ ሥራዎች በሚል ለመመደብ ሁለት የመንፈስ ቅዱስ ሥራዎችን መምረጥ ቢያስፈልግ የትኞቹን ትመርጥ ነበር? ለምን?  ጥያቄ፡- ሀ) በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የተፈጸመ ኃይለኛ ለውጥ ምንድን ነው? ለ) በሕይወትህ የተፈጸመ ወይም የተላማመድከው ዕፁብ ድንቅ ለውጥ ምንድን ነው?  በሩሲያ ኮሙኒዝም የወደቀበትን ዕፁብ ድንቅ ለውጥ ማን ሊዘነጋ ይችላል? ወይም በጀርመን የበርሊን ግንብ መፍረስና በምሥራቅ ጀርመን የኮሙኒዝምን ማክተም ማን ሊዘነጋ ይችላል? ወይም በኢትዮጵያ የኃይለ ሥላሴ መንግሥትና በኋላም የኮሙኒዝም አገዛዝ የወደቁበትን ሁኔታ ማን ሊዘነጋ ይችላል? እነዚህ ዕፁብ ድንቅ ለውጦች በዓለም ታሪክ ላይ ተጽዕኖ አድርገዋል።  በቀላሉ የሚታይ ሳይሆንም እንኳ በብሉይ ኪዳንና በአዲስ ኪዳን መካከል ያላው ለውጥ የበለጠ አስደናቂ ነው። በእግዚአብሔር ዘላለማዊ ዕቅድ ውስጥ ኢየሱስ በመስቀል ላይ የሞተበት፥ ከሞት የተነሣበት፥ መንፈስ ቅዱስ በመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች ላይ የወረደበት ዓመት ዓለም ከተፈጠረ ጀምር ከነበሩ ዓመታት ሁሉ የላቀ ነው። ነገር ግን በክርስቲያን ቤተሰብ ላደግንና የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን ደጋግመን ለሰማን ለብዙዎቻችን፥ ብዙዎች እራሳችውን ክርስቲያን ብለው በሚጠሩ ሕዝቦች መካከል ለምንኖር ለውጡ ምን ያህል ታላቅ እንደሆነና እነዚህ ሦስት ክስተቶች በእግዚአብሔር ዕቅድ ውስጥ ምን ያህል ታላቅ ስፍራ እንዳላቸው ዘንግተናል። ታሪኩን በጣም ከመልመዳችን የተነሣ እግዚአብሔር የሠራሳቸውን መንገዶች ማድነቅ ቀርቷል። በመጀመሪያው ክፍለ ዘመን ላነበሩ ክርስቲያኖች ግን እንደዚህ አልነበረም። አንድ አስደናቂ ነገር እንደሆነ ያውቁ ነበር። በዓለም ሁኔታዎች ውጪአዊ ገጽታ ነገሮች ወዲያውኑ ብዙ ሳይለወጡም፥ ደቀ መዛሙርት ዓለም እንደ ድርዋ እንደማትሆን እስከሚገነዘቡ ድረስ ዕፁብ ድንቅ ነገር ተከናውኗል።  አዳምና ሔዋን በኃጢአት ክወደቁበት ከፍጥረት ጀምሮ ኢየሱስ እስከመጣበት ጊዜ ድረስ እግዚአብሔር ኃጢአት በዓለም ያመጣቸውን ውጤቶች ድል ለማድረግ በሺዎች ለሚቆጠሩ ዓመታት ሲሠራ ቆይቷል። የእስራኤልን ሕዝብ በመምረጥ በዚህ ሕዝብ አማካይነት የዓለም ሕዝብ በሙሉ ወደ እርሱ ቀርቦ በመንፈስና በእውነት እንዲያመልከው ለማድረግ ጥሯል። ነገር ግን የመረጠውና በመካከሉ የኖረበት ሕዝብ እንኳ በኃጢአት በመውደቁ መቀጣት ነበረበት። እግዚአብሔር የተመረጠውን ሕዝብ ለመቅጣት ወደ ምርኮ ከመላኩ በፊት በነቢያቱ በኩል ስለሚመጣው አዲስ ዘመን ለሕዝቡ ተናገረ። በዚያ አዲስ ዘመን የቀድሞው ኪዳን ለሰዎች ሊያደርግ ያልቻላቸው ነገሮች ሁሉ እንደሚፈጸሙና ሕዝቡም ከልባቸው እግዚአብሔርን እንደሚያመልኩ ነበር (ሕዝ 36፡26-27)።  በመቶዎች ለሚቆጠሩ ዓመታት ከእግዚአብሔር ዘንድ በሆነ የጸጥታ ጊዜ ሕዝቡ ከታወክ በኋላ በድንገት መሢሑ ኢየሱስ ክርስቶስ መጣ። ሕዝቡ አሁን አስደናቂው የእግዚአብሔር መንግሥት ይጀመራል ብሎ አሰበ። በዚያ ምትክ ቀን የጠበቁት መሢሕ እነርሱ እንዳሰቡት ሳይሆን ቀረ። ምድራዊ መንግሥት አልተመሠረተም። በዚህ ፈንታ መሢሑ በመስቀል ላይ ሞተ። ነገር ግን በሁላት ክስተቶች እግዚአብሔር ነገሮች የነበራቸውን አካሄድ ካፈራረሰ በኋላ አዲስ ነገርን መሠረተ። የመጀመሪያው የኢየሱስ ክርስቶስ ከሞት መነሣትና ወደ ሰማይ ዐርጐ በአባቱ ዙፋን ቀኝ መቀመጥ ነው። ይህ ድርጊት ሰይጣንና ሞት በአማኞች ላይ የነበራቸውን ሥልጣን መደምሰስ ብቻ ሳይሆን ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑንም አሳየ። ስለ አዲስ ኪዳን የተናገራቸው ነገሮች በሙሉሰዎች ኃጢአታቸው በመስቀል ላይ በፈሰሰው በኢየሱስ ደም ተሸፍኖ እግዚአብሔርን የሚያመልኩበት አዲስ መንገድ መፈጠሩ እውነት መሆኑን አረጋገጠ።  በአስደናቂ ሁኔታ ዓለምን የለወጠው ሁለተኛ ድርጊት የተፈጸመው በበዓለ ኃምሣ ቀን በአማኞች ላይ መንፈስ ቅዱስ ሲወርድ ነበር። የብሉይ ኪዳን ተላሩዎች በሙሉ በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ተፈጸሙ። ሕዝቡ የእግዚአብሔርን ሕግጋት ከልቡ በራሱ ጥረት ሳይሆን በመንፈስ ቅዱስ ኃይል እንዲታዘዝ እደረገ።  ነገር ግን እግዚአብሔር ይህን አዲስ ዘመን ያመጣው ሕዝቡ በጠበቀው መንገድ አልነበረም። ብሉይ ኪዳን መሢሑ በመጣ ጊዜ ክፋትን ሁሉ የሚያስወግድ አዲስ ዘመን እንደሚጀመር የሚናገር ይመስላል። የዓለም ክፉ ሕዝቦች ጠፍተው የእግዚአብሔር ሕዝብ በቅድስና አምላኩን የሚያመልክበት ጊዜ እንደሚሆን ይመስል ነበር። እግዚአብሔር በብሉይ ኪዳን ቃል የገባበትን «አዲስ ዘመን» በጀመረበት ጊዜ ግን በአዳምና ሔዋን ኃጢአት የተጀመረውን አሮጌውን ዘመን አላስወገደም። በአዲስ ኪዳን የሚጀመረው አዲስ ዘመንና በእግዚአብሔር ላይ ዓመፃን የሚያሳየው የቀድሞው ዘመን በአንድነት ጐን ለጐን መኖራቸውን ቀጠሉ። እግዚአብሔር መንግሥቱን በሕዝቡ መካከል ቢመሠርት ኃጢአትና በሽታው ቀን አልጠፋም ነበር። ሰይጣን፥ ኃጢአትና በሽታ ጠፍተው የቀድሞው ዘመን ሙሉ በሙሉ የሚወገደው ኢየሱስ ክርስቶስ እንደገና ሲመለስ ነው።  እግዚአብሔር ተስፋ በሰጠበት በአዲስ ዘመን የመኖራችን ዋና ምልክት መንፈስ ቅዱስ ነው። ኃጢአትን እንዲያሸንፍና ሁል ጊዜ እርሱ በሚፈቅደው መንገድ እንዲያመልኩት እያስቻላ መንፈስ ቅዱስ በሰው ውስጥ ለማደር ባለው ኃይል አማካኝነት እግዚአብሔር ራሱ በሰው ውስጥ ይኖራል።  እግዚአብሔር ተስፋ የሰጠው አዲሱ ዘመን የእግዚአብሔርን ዘላለማዊ ተስፋዎች ሁሉ እየተለማመድን፥ በሥጋት ከዚህ ከአሮጌው ዘመንና ከሰብአዊ ድካማችን ጋር እየታገልንም እንኳ ቢሆን አሁን በመለኮታዊ ኃይል እንድንኖር የሚረዳን መንፈስ ቅዱስ ነው።  አሁንም የምንኖረው በወደቀው ዓለም ውስጥ ነው። የእግዚአብሔርን ፍላጐቶች የምንፈልገውን ያህል አንታዘዝም። ብዙ ጊዜ የኃጢአታዊ ተፈጥሮአችንን ፍላጐቶች በማሟላት በአሮጌው ዘመን እንደሚኖሩ ሰዎች እንመላለሳለን። ይህ አሮጌው ዘመን ያለማቋረጥ በዙሪያችን ነው። በሽታና ሞት አሁንም አሉ። ስደትም እንደቀጠለ ነው። ክርስቲያኖች መንፈስ ቅዱስ የሰጣቸውን ኃይል እንኳ ስሙላት እየተላማመዱት እይደለም። ቤተ ክርስቲያን መሆን የሚገባትን ያህል የተቀዳጀች አይደለችም። ነገር ግን በምድር ላይ ያለ ሕይወት አሳዛኝ ቢሆንም እንኳ መንፈስ ቅዱስ በልባችን ስላለ መኖር የተጀመረውን የዘላለማዊ መንግሥት ጉዳይ ወደ ፍጻሜ እንደሚያመጣው ሙሉ እምነት አለን። እግዚአብሔር ስለ አዲሱ ዘመን የገባቸው ቃል ኪዳኖች አንድ ቀን ሙሉ በሙሉ የራሳችን እንደሚሆኑ እርሱ ዋስትናችን፥ ቀብዳችንና መያዣችን ነው (ኤፌ 1፡13-14)።  ጥያቄ፡– የሚከተሉትን ጥቅሶች ተመልከት። ሕዝ. 36፡26-28 37፡14} ኤር. 31፡31-34። ሀ) እነዚህ ጥቅሶች እግዚአብሔር ከሕዝቡ ጋር ለመኖር ስላለው ፍላጐት ምን ያስተምሩፃል? ለ) በአዲሱ ኪዳን እግዚአብሔርና ሰው ስላሚኖራቸው ግንኙነት የተሰጡት ተስፋዎች ምንድን ናቸው?  በብሉይ ኪዳን ተዘውትረው ከተጠቀሱት ዋና አሳቦች አንዱ እግዚአብሔር በሕዝቡ መካከል ለማደር መፈለጉ ነው። ይህ እግዚአብሔር በሕዝቡ መካከል የማደሩ ጉዳይ በሁለት መንገዶች ይታያል። በመጀመሪያ፥ መደበኛ በሆነ ሁኔታ የእግዚአብሔር በሰዎች መካከል ማደሩ ነው። እስራኤላውያን በምድረ በጻ በኖሩበት ወቅት እግዚአብሔር በመካከላቸው ያድር ዘንድ የመገናኛ ድንኳን እንዲያዘጋጁ አዘዛቸው። የመገናኛው ድንኳን የሚያሳየው እግዚአብሔር በሕዝቡ መካከል ለማደር መፈለጉን ቢሆንም እንኳ በተራው ሰውና የእግዚአብሔር ማደሪያ በሆነው በቅድስተ ቅዱሳን መካከል ሁልጊዜ ግድግዳ ነበር። ወደ እግዚአብሔር እንዲቀርቡ የሚፈቀድላቸው ሁልጊዜ ካህናቱ ብቻ ነበሩ። የእግዚአብሔር ሕዝብ ከእግዚአብሔር ጋር የጠበቀ ኅብረት እንዳይኖራቸው ያገደው ኃጢአት ለመሆኑ የዘወትር አስታዋሽ ነበር። ኋላ በሰለሞን ዘመን እግዚአብሔር ሕዝቡ መካከል የኖረው ሰለሞን በሠራው ቤተ መቅደስ ውስጥ ነበር። ሆኖም ግን ወደ እግዚአብሔር እንዳንቀርብ የሚያግዱት ግድግዳዎች እንዳሉ ቀጠሉ።  ሁለተኛው፥ መደበኛ ባልሆነ ሁኔታ የእግዚአብሔር በሰዎች መካከል መገኘት ነው። ፈርዖን ፊት በሚሆንበት ወቅት ከእርሱ ጋር እንደሚሆን እግዚአብሔር ለሙሴ ቃል ገብቶላት ነበር (ዘፀአ 3፡12፣ 33፡14-17)። እግዚአብሔር ኢያሱና ሕዝቡ የተስፋዪቱን ምድር ከከነዓናውያን እጅ ድል ባደረጉ ጊዜ አብሮአቸው እንደሚሆን ቃል ገብቶላቸው ነበር (ኢያሱ 5፥ 9)። ሕዝቡ በምርኮ በነበሩበት ወቅት ደግሞ በስደት ማዕበል ውስጥ ቢሆኑም እንኳ እግዚአብሔር አብሮአቸው እንደሚሆን ቃል ገብቶላቸው ነበር (ኢሳ. 43፡2)። እነዚህ ግን እግዚአብሔር ከሕዝቡ ጋር ልዩ በሆነ መንገድ የሚገኝባቸው ጊዜያዊ ወቅቶች ነበሩ። ችግሮቻቸውን ሁሉ ለመርታት እንዳይችሉ ዘላቂ የእግዚአብሔር ህልውና ከሕዝቡ ጋር አልነበረም።  ነገሮች በሦስት ዐበይት መንገዶች የሚለወጡበትን ጊዜ እግዚአብሔር በነቢያት በኩል አስቀድሞ ተናገረ።  ሀ. የእግዚአብሔር ሕዝብ አዲስ ልብ እንደሚኖራቸው (ኤር. 31፡31-33)። በእስራኤላውያን እንደሆነው ከእግዚአብሔር ርቀው ከመባዘን ይልቅ እግዚአብሔርን የሚታዘዝ ልብ ይኖራቸዋል።  ለ. አዲሱ ልብ እግዚአብሔር ለሕዝቡ «እዲስ መንፈስ» የመስጠቱ ውጤት ነው (ሕዝ. 36፡26)። ይህ አዲስ መንፈስ

የመጀመሪያው የመንፈስ ቅዱስ ዋና ሥራ፡- ዘላለማዊው አምላክ በውስጣችን መኖሩ Read More »

በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና መንፈሳዊ ብስለት

ተሾመ ትልቅ ሰው ነበር። ለረጅም ጊዜ ከእግዚአብሔር ጋር ተመላልሷል። መጋቢ ወይም ወንጌላዊ ሆኖ አያውቅም። የትምህርት ደረጃ ውም ሁለተኛ ክፍል ብቻ ነበር። ተሾመ ፊደላቱ እጅግ ቢያስቸግሩትም እንኳ በየዕለቱ በትዕግሥት መጽሐፍ ቅዱስን ያነብ ነበር። የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌ ስላልሆነና የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌዎች በእውቀት ከእርሱ የሚሻሉ ስለነበሩ ማንም ሰው እንደ መሪ ሳያየውም ቅሉ ሕዝቡ በተሾመ የተማረከበት አንድ ጉዳይ ነበር። ሰው በሚቸገርበት ወቅት ሁልጊዜ ፈጥኖ ይደርስ ነበር። ትዕግሥቱ እልቆ፥ ሳላቤቱን ተማቶ አያውቅም ነበር። ሌሎችም ብዙዎችን በትዕግሥት ይመክር ነበር፥ ወዘተ…። ለጥቂት ጊዜ እንኳ ከእርሱ ጋር አብሮ የቆየ ሰው እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው ጋር እንደሆነ ይሰማዋል።  ጥያቄ፡- ሀ) እንደ ተሾመ ያሉ እግዚአብሔርን የሚፈሩና የበሰሉ የእግዚአብሔር ሰዎች መሆናቸውን ማንም የሚመሰክርላቸው ሰዎችን በምሳሌነት ጥቀስ። ለህ እንደዚህ እንዲሆኑ ያደረጋቸው ምን ይመስልሃል? ሐህ በመንፈስ ቅዱስ በመሞላትና በመንፈሳዊ ሕይወት በሣል በመሆን መካከል ልዩነቱ ምንድን ነው? መ) እነዚህ ሁለት ጽንሰ እሳቦች እንዴት የተያያዙ ይመስልሃል?  ብዙዎቹ ቤተ ክርስቲያኖች በተለይ በወጣቶች የተሞሉ በሆኑባቸው በእነዚህ ጊዜያት ቤተ ክርስቲያን እጅግ የሚያስፈልጋት ነገር እግዚአብሔርን የሚፈሩ የበሰሉ ወንዶችና ሴቶችን ማግኘት ነው። በጊዜ ሂደት ውስጥ ከእግዚአብሔር ጋር አብሮ በቅርበት መጓዝ ምን ማለት እንደሆነ በሕይወታቸው የሚያሳዩ እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሰዎች ያስፈልጉናል። አንድ ሰው በመንፈሳዊ ሕይወት የበሰለ የሚሆነው እንዴት ነው?  ጥያቄ፡- ሀ) ታዋቂ የሆኑ ኢትዮጵያዊያን የማራቶን ጀግኖችን ጥቀስ። [ለ) ጥሩ ሯጭ ያደረጓቸው ነገሮች ምንድን ናቸው? ሐ) ማራቶን በመሮጥና አጭር ርቀት በመሮጥ መካከል ምን ልዩነት አለ? መ) የማራቶን ሩጫ በመሮጥና የሕይወትን ሩጫ በመሮጥ መካከል ምን ዓይነት ተመሳሳይነት ታገኛላህ? (1ኛ ቆሮ.9፡ 24-27፤ ፊልጵ. 2፡16፤ ዕብ.12፡1 ተመልከት።  ኢትዮጵያ በማራቶን ጀግኖች የታወቀች ነች። ከአበበ ቢቂላ ጀምሮ እስከ ፋጡማ ሮባ ድረስ የጥሩ ሯዮች የማያቋርጥ ምንጭ ሆናለች። የማራቶን ራሮች ከአጭር ርቀት ሯጮች በጣም ይለያሉ። የአጭር ርቀት ሯጮች ለአጭር ጊዜ በቻሉት ፍጥነት የሚሮጡ ናቸው። የማራቶን ሯጮች ግን ከአንድ ሰዓት ለበለጠ ጊዜ ረጅም ርቀትን በሚገባ የሚሮጡ ናቸው። የማራቶን ሩጫ ሕመምና ድካም ያላበት እንኳ ቢሆንም እስከ ፍጻሜ የመሮጥን ቁርጥ ውሳኔና መሰጠት የሚጠይቅ ነው። በጥልቅ ሸለቆዎችና በከፍተኛ ተራራዎች ሯጩ እርምጃውን አስተካክሎ መሮጥ አለበት።  መንፈሳዊ ሕይወት ማራቶን እንደ መሮጥ ነው። ዋናው ነገር በምን ያህል ፍጥነት ወይም ቅልጥፍና ለተወሰነ ጊዜ መንፈሳዊ ሩማን መሮጥ አይደለም። መንፈሳዊ ሕይወታቸውን በታላቅ ሁኔታ ጀምረው በመካክል የሆነ ነገር ተፈጥሮ የወደቁ በርካታ ክርስቲያኖች አሉ። ቁም ነገሩ በሕይወት ዘመናችን ሁሉ መልካሙን ሩጥ መሮጥ ነው። የሚያሳዝነው ግን ብዙ ክርስቲያኖች ትኩረት የሚሰጡት እንድ ክርስቲያን እሁን ምን ያህል ጥሩ እንደሚሮጥ እንጂ ካመነበት ጊዜ ጀምሮ ምን ያህል በሚገባ ይሮጥ እንደነበርና እንዳለ አይደለም። «ድነሃልን?» በማለት ይጠይቃሉ። ሩጫው የሚጀምረው ከዚህ ስለሆነ ጥሩ ጥያቄ ነው። ቀጥሎ «የመንፈስ ቅዱስን ኃይል ተቀብለሃል?» ይላሉ። ጥያቄያቸው እንደገና ጥሩ ጥያቄ ነው፥ ምክንያቱም ያለ መንፈስ ቅዱስ ኃይልና ሙላት ማንም ሰው እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘትና በመንፈሳዊ ሕይወት ማደግ አይችልም። ነገር ግን የመጨረሻው ከሁሉ የላቀው ጥያቄ «ከዳንክበት ጊዜ ጀምሮ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል እየኖርክ ነውን?» የሚል ነው። «በእምነትህና በመንፈሳዊ ሕይወትህ እያደግህ ነውን? በዓመታቱ ሁሉ ውስጥ በጽናት ተመላልሰሃልን?» እኛ የምናተኩረው ሰውዬው አሁን ስለደረሰበት ደረጃ ሲሆን እግዚአብሔር ግን የሚገድደው በሕይወት ዘመኑ ሁሉ ምን ያህል ስሚገባ እንደሮጠና አሁንም ሞቶ ወደ መንግሥተ ሰማያት የሚሄድበት ቀን እስከሚደርስ እየሮጠ መሆኑ ነው። 22ኛ ጥያቄ፡- የሚከተሉትን ጥቅሶች ተመልከት። የሐዋ. 20፡7-27፤ 2ኛ ቆሮ. 3፡18፤ 4፡16=18፤ ፊልጵ. 3፡7-14፤ 1ኛ ጢሞ.4፡6-8። እግዚአብሔር በዘመናት ሁሉ በሕይወታችን ሊያደርጋቸው ከሚመክራቸው ነገሮች እንዳንዶቹን ጥቀሱ። እነዚህ ቁጥሮች ኢየሱስ ክርስቶስ እስኪመጣ ድረስ ያለማቋረጥ መትጋት አስፈላጊ ስለመሆኑ ምን ያስተምሩናል?  በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በብዛት ትምህርት ሊሰጥበት የማንመለከተው አንድ ቃል አለ። ይህ ቃል «መጽናት» የሚል ነው። መጽናት ለረጅም ጊዜ በታማኝነት የመቆየትን ጉዳይ ያመለክታል። ሆኖም ግን መጽናት የክርስቲያን እጅግ አስፈላጊ ባሕርያት ከሆኑት አንዱ ነው። ለምን? የእግዚአብሔር ተቀዳሚ ትኩረት ነገሮች አሁን በሚገባ መከናወናቸው አይደለም። ይልቁኑ እግዚአብሔር የረጅም ጊዜ እመለካከትን ይወስዳል። እግዚአብሔር በሕይወታችን ሊያደርገው ስለሚፈልገው ነገርና እንዴት ምላሹን መስጠት እንዳለብን የሚከተሉትን እውነቶች ልብ በል።  1. እግዚአብሔር ዕለት በዕለት ሊያድሰን ይፈልጋል (2ኛ ቆሮ. 4፡16-18)። በውስጣችን ከሚከናወነው አብዛኛው ነገር ለመለካት ከባድ ስለሆነ በሕይወታችን ትክክለኛ እሴቶች ወይም ፋይዳዎች ሊኖሩን ይገባል እንጂ በሚታይ ነገር የጨበጥነውን ስኬት መቁጠር የለብንም። የሕይወታችን ስኬታማነት በትምህርት፥ በሥልጣንና በሥራ የሚለካ አይዴለም። እነዚህ የሕይወታችንን ስኬታማነት ለመናገር ትክክለኛ አመልካቾችም አይደሉም። ይልቁኑ እግዚአብሔር በልባችን ያደረገው የማይታይ ሥራ ከማይታየውና ዘላለማዊ ከሆነው የሚመጣ ነው። ከሁሉ የላቀው አስፈላጊ ነገር ነው።  2. የእግዚአብሔር ተቀዳሚ ትኩረት ኢየሱስ ክርስቶስን እንመስል ዘንድ በመንፈሳዊ ሕይወታችን ያለማቋረጥ ማደጋችን ነው። ኢየሱስ የነበረው ባሕርይ፥ ፍቅሩ፥ ቸርነቱ፥ ንጽሕናው፥ ጽድቁ፥ ቅድስናው፥ ወዘተ… የእኛ ባሕርያት መሆን ይገባቸዋል (2ኛ ቆሮ. 3፡18)።  3. ጳውሎስ መንፈሳዊ እድገት እግዚአብሔርን የማያከብሩ ነገሮችን  ማስወገድና የሕይወት ትክክለኛ ግብን መያዝ እንደሆነ ተገንዝቦ ነበር። ስለዚህ በቤተሰብና በዘር ሊመጣ የሚችለውን ትምክህት ወደ ጎን ትቶ ስለ ኢየሱስ ፍቅር ሞትና የትንሣኤ ኃይል መማርን ግቡ አድርጎ ያዘ። በመንፈሳዊ ሕይወቱ ለማደግ እጅግ ጣረ። ያለፈው ጊዜ ለእርሱ ብዙ ቁም ነገር አልነበረም። ይልቁኑ የሚያሳስበው የወደፊቱ ጉዳይ ነበርና በመልካም ይፈጽመው ዘንድ ተግቶ ሠራ (ፊልጵ. 3፡7-14)።  4. ጳውሎላ ለአሕዛብ ወንጌልን ይሰብክ ዘንድ አደራ እንደተሰጠው ያውቅ ነበር። ይህ ለሕይወት ዘመኑ በሙሉ የተሰጠ አደራ ነበር። በታላቅ ሐዘን ውስጥ እንባዎች የነበሩበት ነበር። ለብዙ ዓመታት በታማኝነት ማሰብን የሚጠይቅ ነበር። እውነተች ሁሉ በትክክል መሰጠታቸውን የማረጋገጥ ባለአደራነት ነበረበት። የጳውሎስ ሕይወት ታላቁ ፍላጎት ሩጫውን በሚገባ መፈጸም ነበር። ለእምነቱ ቢታሰርና ሲሞትም እንኳ ብድ አልነበረውም። «ከጌታ ከኢየሱስ የተቀበልሁትን አገልግሎት እርሱም የእግዚአብሔርን ጸጋ ወንጌልን መመስከር እፈጽም ዘንድ» እያላ ይልቁን ይፈልግ የነበረው በሚገባ መፈጸሙን ብቻ ነበር። እስካሁን ድረስ የነበረውን እሩግ በሚገባ በታማኝነት ሮጬአለሁ ብሎ ሊናገር ይችል ነበር። ወንጌልን ባይሰብክ ኖሮ ሊኖርበት ይችል ከነበረ ክማናቸውም ሰው ደም እዳ እጁ ንጹሕ ነበር። ነገር ግን ገና ስላልሞተ ወደ ፊት ለመቀጠልና ሩጫውን በሚገባ ለመፈጸም ይፈልግ ነበር (የሐዋ. 20፡7 27)።  5። ጳውሎስ ጥንቃቄ ባያደርግና ያለማቋረጥ ጸንቶ ባይቀጥል በቀላሉ በኃጢአት በመውደቅ እንደ እንድ ሯጭ ከውድድር እንደሚወገድ ያውቅ ነበር። ስለዚህ፥ ከሩጫው ውድድር እንዳይወጣ አስፈላጊ የሆነውን ነገር ሁሉ ሥጋውን በሚገባ እንደተቆጣጠረ ይናገራል (1ኛ ቆሮ.9፡24-2)።  6. ክብዙ ዓመታት በኋላ ጳውሎስ በወህኒ ሆኖ ሞቱን ሊጠበቅ ነበር። በምድር የነበረውን ሩጫ እንዳጠናቀቀና ጌታን የሚገናኝበት ጊዜ እንደደረሰ አውቆት ነበር። አሁን የእፎይታ ትንፋሽን መተንፈስ የሚችልበት ጊዜ ነበር። ሩጫው ተጠናቀቀ። በታላቅ ጽናት ሩጫውን ጨረሰ። እምነቱን አልተወም፤ ለጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ታማኝነት ያጎደላበት ጊዜ አልነበረም (2ኛ ጢሞ.4፡6-8)።  ጥያቄ፡- እነዚህን ስድስት ነጥቦች ከልዕ። ቀጥሎ ለጸሎትና ቃሉን ለማሰላሰል ጊዜ ውሰድ። በልብህ በእድገት አቅጣጫ ወደፊት ለመቀጠል፥ ለመትጋት፥ በንጽሕና ለመቆየት እግዚአብሔር በሕይወትህ ሁሉ የሰጠህን ጥሪ ለማሟላት ቃል ኪዳን ግባ።  ከላይ የተመለከቱትን ነገሮች ሁሉ አጠቃልሎ የመግለጫ ሌላው መንገድ በመንፈሳዊ ሕይወት የበሰሉ መሆን ነው። በመንፈሳዊ ሕይወቱ የበሰለ ሰው እስከሚሞትበት ቀን ድረስ ኢየሱስን ለመምሰል ባለው ፍላጎት ያለማቋረጥ በእድገት የሚጓዝ ሰው ነው። ታዲያ በመንፈሳዊ ሕይወታችን የበሰልን የምንሆነው እንዴት ነው? መንፈሳዊ ብስለትን የሚያመጡ ሦስት ዋና ነገሮች አሉ።  1. ለመንፈሳዊ እድገት መሠረት ከሆኑት ነገሮች መካከል ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረትን በማድረግ መኖር ነው (1ኛ ዮሐ 1፡5-10)። ይህን በሌላ አባባል መግለጽ ካስፈለገ በመንፈሳዊ ሕይወት እንድናድግ ምክንያት የሚሆነን ተቀዳሚ ነገር በመንፈስ ቅዱስ መሞላታችን ነው። በሕይወት ጉዞአችን በማንኛውም ወቅት ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረት ይኖረናል ወይም አይኖረንም። በመንፈስ ቅዱስ የተሞላን እንሆናላን ወይም ሕይወታችን በመንፈስ ቅዱስ ያልተሞላ ይሆናል።) ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ምንም ዓይነት ኅብረት

በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና መንፈሳዊ ብስለት Read More »

በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት የሚቀርቡ ቅድመ ሁኔታዎች

ጥያቄ፡- የሚከተሉትን ጥቅሶች አንብብ። ኤፌ. 5፡18፤ 4፡30፤ 1ኛ ተሰ. 5፡19። ሀ) ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ የተላያዩ ትእዛዛትን ዘርዝር። ለ) እያንዳንዱ ትእዛዝ የመንፈስ ቅዱስ ሙላትን እንዴት ሊነካ እንደሚችል አንዳንድ ምሳሌዎችን ጥቀሰ።  ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጠን የመጀመሪያ ትእዛዝ «በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ» የሚል ነው። ዋናው ጥያቄ በመንፈስ ቅዱስ እንዴት እንሞላለን? የሚል ነው። ከመንፈስ ቅዱስ ሙላት በምንጐድልበት ወቅት ያንን ሙላት ተመልሰን የምናገኘው እንዴት ነው? መጽሐፍ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ ስላመሞላት ምንም ዓይነት ግልጽ ቀመር አይሰጠንም። ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ ይሞላን ዘንድ መሟላት ያለባቸው ሁኔታዎች አሉ። መንፈስ ቅዱስ ይሞላብንና በሕይወታችን በአስደናቂ መንገዶች ይሠራ ዘንድ የሚያስችሉ አንዳንድ ሁኔታዎች ቀጥሎ ቀርበዋል።  1. መንፈስ ቅዱስ የሚሞላን ለሕይወታችን ላለው መመሪያ ስንገዛና እራሳችንን ሕያው መሥዋዕት አድርገን ለእርሱ ልናቀርብ ነው (ሮሜ 12፡1)።  መንፈስ ቅዱስ በሕይወታችን ዙፋን ላይ ነግሦ ምን እንደሚሆን እንወስን ዘንድ አይፈቅድም። ይልቁኑ ሕይወታችንን ሙሉ በሙሉ እንዲቆጣጠረው ለእርሱ እንድናስረክብ ይገፋፋናል። የራሳችንን ዕቅዶች፥ አሳቦችና ሕልሞች ለመፈጸም ያለንን መብት ላእርሱ መተው አለብን። ሕይወታችንን በሙሉ እግዚአብሔር ለእኛ ለወሰነው ነገር ማስገዛት አለብን። መንፈስ ቅዱስ የሚሞላን በዚያን ጊዜ ብቻ ነው። በሕይወታችን ማንኛውም ወቅት የእግዚአብሔርን ፈቃድ የምንቃወም ከሆነ፥ እራሳችንን አሳልፎ ለመስጠት ወይም ለማስገዛት እምቢ የማላት ዝንባሌ ካለን በዚያን ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ መሞላታችን ይቀራል ማለት ነው።  አዲስ ኪዳን በመንፈስ ቅዱስ እንሞላ ዘንድ መጾም እንዳለብን አይናገርም። ለመንፈስ ቅዱስ ሙላት መጸለይ እንዳለብን እንኳ አልተነገረንም። ይልቁኑ ሕይወታችንን ሕያው መሥዋዕት አድርገን ስናቀርብ በመንፈስ ቅዱስ ወዲያውኑ እንሞላለን።  2. በሕይወታችን ከማናቸውም ነገሮች በላይ መንፈስ ቅዱስ እንዲቆጣጠረንና እንዲጠቀምብን መፈለግ አለብን።  ስስታሞች ሆነን ለራሳችን ክብርን ብንፈልግ ወይም ከእግዚአብሔር ይልቅ ሌላ ነገርን ብንወድ መንፈስ ቅዱስ አይሞላብንም። እግዚአብሔር ከእኛ በኩል የሚፈልገው ሙሉ ለሙሉ የሆነ መሰጠትን እንጂ ከፊል መሰጠትን አይደለም። ከሁሉ በላይ የቅድሚያን ስፍራ ይፈልጋል። በሕይወታችን ድርሻ ያላቸው ሌሎች ነገሮች ቤተሰብ፥ ሥራ +ዕቅድ፥ ወዘተ… ከኋላ መምጣት አለባቸው። ኢየሱስ እንዳለው የእርሱ ለመሆን የምንገባው ሌሎችን ነገሮች ሁሉ «ስንጣላ» ነው (ማቴ. 10፡32-39)። ሕይወታችንን በራሳችን ለመቆጣጠር ከመሞከር ፍጹም ነፃ የማንሆንበት ጊዜ አይኖር ይሆናል። በመንፈሳዊ ሕይወት ሰብለለት ማደግ የሕይወታችንን ክፍሎች ለእግዚአብሔር በመተው ከዕለት ወደ ዕለት የበለጠ በእርሱ ቁጥጥር ሥር የመሆን ተቀዳሚ ችሎታ ነው። እግዚአብሔር ጸጋን የተሞላ አምላክ ስለሆነ የመንፈስ ቅዱስ ሙላትን ፍጹሞ እስክምንሆን ድረስ አይቆጥብብንም።  ነገር ግን በሕይወታችን አስቀድሞ ባሳየን ነገሮች እየታዘዝን መኖር አለብን። መንፈስ ቅዱስ ያላስገዛንላትን የሕይወት ክፍላችንን ያሳየናል። ያንን የሕይወት ክፍላችንን እንድናስገዛለት ይረዳናል። ከዚያ በኋላ ማስገዛት ያለብንን ሌላ የሕይወት ክፍላችንን ያሳየናል። መንፈስ ቅዱስ በእርሱ ቁጥጥር ሥር እንዳልሆኑ የሚያሳየንን የሕይወታችንን ክፍሎች በማስገዛት እስከኖርን ድረስ እግዚአብሔር በቸርነቱ በመንፈስ ቅዱስ ሊሞላን ይችላል።  የሕይወታችን የትኩረት አቅጣጫ «ከመንፈስ ቅዱስ ሙላት» ላይ ሊሆን አይገባም። ይህን ካደረግን ግን ምክንያቶቻችን ከራስ ወዳድነት የመነጨ ፍላጐት ይሆናል። ከዚህ ይልቅ በእግዚአብሔር ላይ በማተኮር ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር የቀረበና የሞቀ ኅብረት እንዲኖረን መትጋት ያስፈልጋል። እግዚእብሔርን በምንፈልግበት ጊዜ ለእርሱ እንገኝለታለን። በእግዚአብሔር በተገኘን ጊዜ ቀንኙነታችን እውነተኛና ጥብቅ ይሆናል። ይህ በሚሆንበት ወቅት እኛ ምንም ዓይነት ጥረት መሻት ሳናደርግ መንፈስ ቅዱስ ይሞላናል።  3. መንፈስ ቅዱስ እኛን እንዲሞላን ከተፈለገ ለእግዚአብሔርና ለፈቃዱ ታዝዘን መኖራችን ሌላው መሠረታዊ ሁኔታ ነው። ሕይወታችንን ከኃጢአት ሁሉ ማንጻት አለብን።  በአዲስ ኪዳን ስለ መንፈስ ቅዱስ ከተሰጡን ትእዛዛት ሁለተኛው «መንፈስን አታሳዝኑ» (ኤፌ. 4፡30) የሚል ነው። [የመጀመሪያው ትእዛዝ በመንፈስ ተሞሉ] የሚል ነው። መንፈስ ቅዱስን የሚያሳዝነው ምንድን ነው?  ጥያቄ፡– ኤፌ. 4፡29-32 አንብብ። ሀ) አታድርጉ የተባልናቸውን ነገሮች ዘርዝር። ለ) አድርጉ የተባሉትን ነገሮች ዘርዝር።  በኤፌ.4 የሚገኙት እነዚህ ጥቅሶች ማድረግ ያለብንና የሌለብንን ነገሮች ይዘረዝራሉ። በአንድ በኩል ማድረግ የሌለብን ነገሮች እንዳሉ ተነግሮናል። ክፉ ንግግር ከአፋችን መውጣት እንዲወጣ መፍቀድ የለብንም። ከልባችን መራርነት፥ ቁጣ፥ ስድብ፥ ክፋትና ንዴት መወገድ አለባቸው። ጳውሎስ የሚናገረው ከሌሎች ጋር ያሉንን ግንኙነቶች የሚያጠፉ ነገሮች ሁሉ መወገድ እንዳለባቸው ነው። የተሳሳቱ የልብ ዝንባሌዎች ወደተሳሳቱ ንግግሮች ያመሩና የተበላሸ ቀንኙነት ይፈጥራሉ። በሌላ በኩል ከሌሎች ጋር ያላንን ግንኙነት የሚያመቻቹ ነገሮችን እንድናደርግ ታዝዘናል። በተለይ ቶርና ርኅሩኖች በመሆን ሌሎችን ማነጽ መቻል አለብን። በደል በሚደርስበት ጊዜ እንኳ እርስ በርስ ይቅር መባባል አለብን።  በእነዚህ ሁለት የትእዛዛት ዝርዝሮች መካከል «የእግዚአብሔርን መንፈስ እታሳዝኑ» (ኤፌ.4፡30) የሚል ትእዛዝ እናገኛለን። መንፈስ ቅዱስን ማሳዘን ማለት ምን ማለት ነው? ከክፍሉ አጠቃላይ ይዘት አንጻር ስናየው ከሌሎች ክርስቲያኖች ጋር ያለንን ግንኙነት የሚያበላሽ የተሳሳተ ዝንባሌ በማንኛውም ጊዜ በልባችን ሲኖር ነው። በመሠረቱ ይህ በሕይወታችን ኃጢአት የሚኖርበት ማንኛውም ጊዜ ነው። ኃጢአት ከእግዚአብሔር እብ ጋር ያለንን ግንኙነት ያቋርጠዋል። ከእግዚአብሔር እብ ጋር ያለን ግንኙነታችን ሲበላሽ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ያላን ግንኙነትም ይነካል። የመንፈስ ቅዱስ ሙላትና ኃይል ይታቀባል። ይህ ግን በዚህ ጊዜ መንፈስ ቅዱስ በሕይወታችን መኖሩን ያቋርጣል ማለት አይደለም። ሆኖም ቀን ሙላቱንና ሕይወታችንን የመቆጣጠሩ ጉዳይ ይነካል»  ብዙ ጊዜ ኃጢአታችን ከሌሎች ጋር ባለን ግንኙነት ይረጋገጣል። ወደ ቁጣ፥ ትክክል ወዳልሆኑ ንግግሮች፥ ብሎም ወደተበላሸ ቀንኙነት የሚመራ ትዕቢት በሕይወታችን ካለ መንፈስ ቅዱስን አሳዝነናል ማለት ነው። ይህ አካሄድ በድል ሊሰበር የሚችለው እራሳችንን ትሑት በማድረግ ደግና ርኅሩህ ስንሆን እርስ በርስ ይቅር ስንባባልና አንዱ ሌላውን ሲያንጽ ነው። ከሌሎች ሁሉ ጋር በሰላም ለመኖር የምንችለውና ግንኙነታችን የሚስተካከላው ያኔ ብቻ ነው።  ይህ ክፍል የሚያስተምረን የመንፈስ ቅዱስ ሙላት የሚወሰነው በሕይወታችን በምንኖረው ኑሮ መንፈስ ቅዱስን በማሳዘናችን ወይም ባለማሳዘናችን ላይ እንደሆነ ነው። ያልተናዘዝነው ኃጢአት በሕይወታችን ካለ መንፈስ ቅዱስን እያሳዘንነው ነው ማለት ነው። ከሌሎች ክርስቲያኖች ጋር ያለን ግንኙነት የሻከረ ከሆነ መንፈስ ቅዱስን እያሳዘንነው ነው ማለት ነው። ውጤቱም በሕይወታችን የመንፈስ ቅዱስን ኃይል ማጣት ይሆናል። የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ይመለስልን ዘንድ ኃጢአታችንን ለእግዚአብሔር መናዘዝና የለዴልናቸውን ሰዎች ይቅርታ መጠየቅ አለብን። ግንኙነታችንን ማስተካክል ይኖርብናል ማለት ነው። ከእግዚአብሔርና ከሌሎች ጋር ያለንን ግንኙነቶች እስካላስተካከልን ድረስ በመንፈስ ቅዱስ እንደገና ልንሞላ እንችልም።  ጥያቄ፡- ልብህን መርምር። ሀ) ያልተናዘዝክው ኃጢአት ካለ መንፈስ ቅዱስ እንዲያሳይህ ጠይቀው። (መዝ[39]23-24) ለ) ከባለቤትህ, ከልጆችህ፥ ከቤተሰቦችህና በቤተክርስቲያን ካሉ ከሌሎች ሰዎች ጋር ስላለህ ግንኙነት አስብ። የተቋረጡ ወይም የተበላሹ ግንኙነቶች አሉህን? የመንፈስ ቅዱስ ኃይልን እንደገና ትለማመድ ዘንድ እነዚህን የተቋረጡ ወይም የተበላሹ ግንኙነቶች ለማስተካክል ምን ማድረግ አለብህ?  የመንፈስ ቅዱስን ሥራ መቃወም፥ መገደብ፥ ወይም ጥያቄ ውስጥ መጣል የለብንም። መንፈስን ማጥፋት የለብንም (1ኛ ተሰ 5፡19)። ይህ መንፈስ ቅዱስ ከእኛ ጋር ስላለው ግንኙነት በአዲስ ኪዳን ውስጥ የተሰጠ ሦስተኛ ትእዛዝ ነው።  ጥያቄ፡– 1ኛ ተሰ5፡12-22 አንብብ። ሀ) እንዴት መኖር እንዳለብን መመሪያ የሚሰጡንን በእነዚህ ቁጥሮች ያሉ ነገሮችን ዘርዝር። ለ) የመንፈስ ቅዱስን እሳት በማጥፋትና ትንቢቶችን በማጥፋት መካከል ያለው ግንኙነት ምን ይመስልሃል?  በ1ኛ ተሰ. ጳውሎስ የመንፈስ ቅዱስን እሳት ያጠፋል ብሎ ያምን የነበረው ምን እንደሆነ ለማወቅ አስቸጋሪ ነው። «መንፈስን ማጥፋት» የሚለው ሐረግ ጳ ውሎስ የሚያመላክተው መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያንን ጥሎ እንዲሄድ የማስገደድን ጉዳይ ሳይሆን ክርስቲያኖችና ቤተ ከርስቲያን ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ያላቸውን ቅርብ ግንኙነት የማጣታቸውን ጉዳይ ነው። በአንድ ጎጆ ውስጥ መካከል ላይ የሚነደው እሳት ላቤቱ ሙቀትን እንደሚያመጣው ሁሉ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር የሚደረግ ሕያው የሆነ የቅርብ ግንኙነት ለክርስቲያን ልብና ለቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ሙቀትን ያመጣል።  ጳውሎስ የመንፈስ ቅዱስን እሳት ላለማጥፋት በሚያስጠነቅቅበት ጊዜ ስለ ሁለት ነገሮች ማመልከቱ ሳይሆን አይቀርም። እግዚአብሔርን በማያስከብር ማንኛውም መንገድ ስንኖር መንፈስን ማጥፋታችን ነው ማለቱ ሊሆን ይችላል። ተግተው የሚያገለግሉ የቤተ ክርስቲያን መሪዎችን ሳናከብር ስንቀር፥ ሰነፎች ሆነን እግዚአብሔርን በሚያስከብር መንገድ ሳንሠራ ስንቀር፥ ወይም አንዳችን ሌላችንን መታገሥና መርዳት ሲያቅተን፥ ወዘተ… የመንፈስ ቅዱስ እሳት በመካከላችን እየቀነሰ እንዲሄድ በዚሁም ከቀጠልን እንዲሞት እናደርጋለን። በሌላ አነጋገር በሕይወታችን በማንኛውም ጊዜ

በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት የሚቀርቡ ቅድመ ሁኔታዎች Read More »

በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ማረጋገጫዎች

ጥያቄ፡– የማያቋርጥ የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ያለበትን ሕይወት የሚኖር ሰውን አስብ። የመንፈስ ቅዱስ ሙላት አለው ብለህ እንድታስብ የሚያደርግ ምን ተግባር ይፈጸማል?  መጽሐፍ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ እንዴት እንደምንሞላ እይናገርም። ይልቁኑ መጽሐፍ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ ከመሞላት የሚያግዱንን ነገሮች የሚጠቁሙ አራት ትእዛዛት ይሰጠናል። መንፈስ ቅዱስ ሁሉንም ክርስቲያኖች መሙላት ይፈልጋል። የእግዚአብሔር ዕቅድ እንደዚያ ነው።  እያንዳንዱ ክርስቲያን በመንፈስ ቅዱስ መሞላት ይችላል። ነገር ግን የሚያሳዝነው ያላማቋረጥ በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ሕይወትን የሚኖሩ ሰዎች ጥቂቶች መሆናቸው ነው። ወይም ደግሞ ምናልባት በመንፈስ ቅዱስ የመሞላትን ማረጋገጥ አሳስተን እናቀርባለን። አንድ ሰው በመንፈስ ቅዱስ መሞላቱን እንዴት እናውቃለን? ቀጥሎ ለመንፈስ ቅዱስ ሙላት ማረጋገጥ የሚሆኑ እውነቶችን በዝርዝር እናቀርባለን።  1. የመንፈስ ቅዱስ ፍሬ  ጥያቄ፡- ገላ. 5፡16-26 አንብብ። ሀ) «በመንፈስ ስንመላለስ» ምን ይፈጸማል? ለ) በኃጢአታዊ ተፈጥሮና በመንፈሳዊ ተፈጥሮ መካከል ያለው ግንኙነት የተገለጠው እንዴት ነው? ሐህ ኃጢአታዊው ተፈጥሮ እንዴት ተገልጿል? መ) የመንፈሳዊ ተፈጥሮ ባሕርያት ምንድን ናቸው? ሀ) ክመንፈስ ቅዱስ ጋር እርምጃ ችንን ጠብቀን የምንኖረው እንዴት ይመስልሃል? ሠ) ገላ. 5፡22-23 ያለውን በቃልህ ለማጥናት ጊዜ ውሰድ። እዚህ «የመንፈስ ቅዱስ ፍሬ» ተብለው የተጠቀሱት ባሕርያት የሕይወትህና! ከሌሉች ጋር ያለህ ግንኙነት ዋና ክፍል የሚሆኑበትን መንገድ እንዲያሳይህ እግዚአብሔርን በጸሎትህ ጠይቀው።  መጽሐፍ ቅዱስ በዓለማችን ላይ ሦስት ዓይነት ሰዎች እንዳሉ ያስተምረናል። በመጀመሪያ፥ ያልዳኑ ሰዎች አሉ። በዚህ ውስጥ የሚካተቱት በኢየሱስ ክርስቶስ ያላመኑ መንፈስ ቅዱስ በሕይወታቸው ኖሮ የማያውቅ ለዘላለም ፍርድ የተጠበቁ ሁሉ ናቸው። በኃጢአታቸው የሞቱ ሰዎች ሁሉ በዚህ ውስጥ ይካተታሉ። በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠሩ በመሆናቸው ምክንያት ታላላቅ ነገሮችን ለማድረግ ቢችሉም እንኳ ሕይወታቸውን የሚኖሩት ከእግዚአብሔር ውጭ ስለሆነ ከሚያደርጓቸው ነገሮች የትኞቹም ድነት (ደኅንነት)ን ሊያስገኙላቸው አይችሉም። ጽድቃቸው ሁሉ እንደ «መርገም ጨርቅ» ነው (ኢሳ. 64፡6)።  በሁለተኛው ዓይነት የሚፈረጁት ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ የተሞሉ ክርስቲያኖች ናቸው። ሕይወታቸውን ለኢየሱስ የሰጡና በመንፈስ ቅዱስ ኃይል የሚኖሩ ናቸው። ባሕርያቸውና ሕይወታቸው የተለወጡ ናቸው። በመንፈስ ቅዱስ ስለተሞሉ ክርስቲያኖች ወደፊት የበላጣ እናጠናለን።  በሦስተኛ ዓይነት የሚፈረጁት ሰዎች ሥጋዊ ክርስቲያኖች ናቸው። እነዚህ ኢየሱስ ክርስቶስን ለመከተል የወሰኑ ክርስቲያኖች ናቸው። የሚኖሩት ግን በመንፈስ ቅዱስ ኃይል አይደለም። ነገር ግን በራሳቸው ኃይል ይመላለሳሉ። ስለዚህ ሕይወታቸው የማያምን ሰው ሕይወትን ይመስላል። «የኃጢአታዊው ተፈጥሮን ተግባራትን» መፈጸማቸውን አያቆሙም። ደግሞም እግዚአብሔርን በማያስከብር ሕይወት ይመላለሳሉ። ጳውሎስ ክርስቲያን ነን እያሉ ነገር ግን ያለሟቋረጥ በኃጢአታዊ ተፈጥሮ የሚኖሩትን በጥብቅ ያስጠነቅቃል። ያለማቋረጥ በኃጢአታዊ ተፈጥሮአቸው , የሚኖሩ ሰዎች «የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም» ይላል። የእግዚአብሔር ልጆች የመሆናችን ማረጋገጥ በአፋችን የምንለው ነገር ሳይሆን በየዕለቱ የምንኖረው ሕይወት ነው። በተወሰነ የጊዜ ክልል ውስጥ «የመንፈስ ቅዱስ ፍሬ» በሕይወታችን ካልታየ አስቀድሞም ቢሆን መንፈሳዊ ሕይወት ኖሮን እንዴሆነ መጠየቅ እጅግ ተገቢ ነው።  ጥያቄ፡- ሀ) ከራስህ ሕይወት ሦስቱንም ዓይነት ሰው እንዴት እንደነበርክና እንደሆንክ ግለጽ። ለ) አሁን ያለህበትን ሕይወት ከሦስቱ በላቀ ሁኔታ የሚገልጸው የትኛው ነው?  በመንፈስ የተሞላን ክርስቲያኖች ከሆንን ነገሮች የተለዩ ይሆናሉ። ከኃጢአታዊ ተፈጥሮ ጋር ያለንን ትግል የምንቀጥል ቢሆንም እንኳ በይበልጥ ያለማቋረጥ በመንፈሳዊ ተፈጥሮአችን እንኖራለን። የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ውጫዊ ተግባራችንን ይለውጣል። ሆኖም ግን የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ይበልጥ በተለያዩ ውስጣዊ ባሕርያት ይረጋገጣል። ያላ መንፈስ ቅዱስ አንዳንድ ውግዊ ለውጦችን ማሳየት እንችላለን (ለምሳሌ የአልኮል መጠጥ ማቆም፥ ከአንድ በላይ የነበሩን ሚስቶቻችንን መተው፥ ወዘተ)። እነዚህ በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ማረጋገጣ ላይሆኑ ይችላሉ። የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ማረጋገጫ ሙሉ በሙሉ የመለወጥ ባሕርይ ነው። ጳውሎስ እነዚህን ለውጦች «የመንፈስ ቅዱስ ፍሬ» በማለት ይጠራቸዋል።  ጳውሎስ ለክርስቲያኖች በመንፈስ የተሞላ ሕይወት ማረጋገጫን ሲነግራቸው በፈለገ ጊዜ በክርስቶስ አካል ውስጥ ከሌሎች ጋር ያሏቸውን ግንኙነቶች የሚነካውን ጉዳይ ለማሳየት ወደ ልቦናዎቻቸውና ወደ ዝንባሌዎቻቸው አመለከተ። በልሳናት የመናገር ፥ተአምራትን የማድረግ :የመተንበይ ወይም ሌሎች የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎችን ጉዳይ አልተናገረም። ይልቁኑ ውስጣዊ ስለሆነ፥ ለተፈጥሮአዊው ሰው ፈጽሞ ስለ ማይቻል ነገር ነው የተናገረው። የመንፈስ ቅዱስ ፍሬ ላመንፈስ ቅዱስ ሙላት ከሁሉ የላቀ ማስረጃ ነው።  የመንፈስ ቅዱስ ፍሬ ኢየሱስ በምድር ላይ በተመላለሰበት ወቅት የነበረው ባሕርይ ግልጽ መግላጫ ነው። የመንፈስ ቅዱስ ዋና ግቡ ኢየሱስን እንድንመስል ማድረግ በመሆኑ በመንፈስ የተሞሉ ክርስቲያኖች ምን እንደሚመስሉም ያሳየናል። በእነዚህ ቁጥሮች የሚከተሉትን እጅግ አስፈላጊ እውነቶች መመልከት እንችላለን።  1. ዘጠኙ ባሕርያት የመንፈስ ቅዱስ «ፍሬ» በመባል ይታወቃሉ። የመንፈስ ቅዱስ «ፍሬዎች» እይደሉም። አንዱን እያደረግን ሌላውን ላለማድረግ እንችልም። አንድ ሰው በመንፈስ ቅዱስ በሚሞላበት ጊዜ እነዚህ ባሕርያት በተለያየ ደረጃ በሕይወቱ ይኖራሉ።  2. «የመንፈስ ቅዱስ» ፍሬ በመባል ይጠራሉ። የሰው ሥራ አይደሉም። ይልቁኑ መንፈስ ቅዱስ በሰዎች ሕይወት ውስጥ የሚሠራው ሥራ ውጤት ናቸው። ብዙ ሰዎች በጣም በሞከርን ቁጥር የበለጠ ፍቅር ይኖረናል፤ የበለጠ ደስተኛ እንሆናለን፥ ወዘተ… ይላሉ። የሰው ጥረት ግን ይህንን ፍሬ አያመጣም። በሰው ሕይወት ውስጥ በሚሠራ መንፈስ ቅዱስ አማካኝነት የሚመጣ ውጤት ነው። ስለዚህ ይህ ፍሬ በሕይወታችን እንዲረጋገጥ ከፈለግን ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ባለን ትክክለኛ ግንኙነት መሥራት መቻል አለብን።  3. የተጠቀሱት ዘጠኝ ባሕርያት ከሰው ልብ በመውጣት በተግባር የሚታዩ ይሆናሉ። በተቀጻሚ ከሌሎች ጋር ባለን ግንኙነቶች የሚረጋገጡ ውስጣዊ ባሕርያት ናቸው።  ጥያቄ፡- ሀ) በሥጋ ሥራዎች (ገላ. 5፡19-2) የተሞላ ሕይወትና በመንፈስ ቅዱስ የተሞላ ሕይወትን አወዳድር። ለ) በሥጋ ፈቃድ እየተመላለስክ እንደሆነ የሚያሳዩ በሕይወትህ የሚፈጸሙ የተለያዩ ድርጊቶችን በምሳሌነት ጥቀስ። ሐ) በመንፈስ ቅዱስ መሞላት የመንፈስ ቅዱስ ፍሬን እንዴት እንደሚያመጣ ከግል ሕይወትህ የተለያዩ ምሳሌዎችን ስጥ።  2. መንፈሳዊ ስጦታዎች ለመንፈሳዊ አገልግሎት  መንፈሳዊ ስጦታዎች በሰው ሕይወት ውስጥ መንፈስ ቅዱስ የመኖሩ ውጤቶች ናቸው። እነዚህ መንፈሳዊ ስጦታዎች አንድ ሰው በመንፈስ ቅዱስ ባይሞላም እንኳ ሊኖሩት ይችላሉ። ለምሳሌ በልባችን መንፈሳዊ ትዕቢት እያላ እንኳ በልሳን መናገር እንችላለን። ስለዚህ መንፈሳዊ ስጦታዎችን መለማመድ ብቻ በራሱ በመንፈስ ቅዱስ ላመሞላታችን ማረጋገጥ አይደላም። ሆኖም ግን እነዚህን መንፈሳዊ ስጦታዎች ያለማቋረጥ በተገቢ ሁኔታ ለእግዚአብሔር ክብርን የሚያመጣና የክርስቲያንን ኅብረት በሚነባ መንገድ መጠቀም የሚቻለው በመንፈስ ቅዱስ በመሞላት ብቻ ነው። መንፈሳዊ ስጦታዎቻችንን ስንጠቀም በመንፈስ ቅዱስ ካልተሞላን ግን ብዙም ሳይቆይ ሰዎች የተሳሳቱ ነገርች ከሕይወታችን ማውጣት ይጀምራሉ። ውስጣዊ አመለካከታችን ንጹሕ ስለማይሆን በክርስቶስ አካል መካከል ፀብንና መከፋፈልን እናመጣለን። በመንፈስ ቅዱስ የተሞላ ሰው በመንፈስ ቅዱስ መሞላቱን ሌሎችን በትሕትና በማገልገሉና የክርስቶስን አካል አንድነት በመጠበቁ ይገልጻል።  3. በመንፈስ ቅዱስ መማር  ሰዎች በአእምሮ እውቀት ችሎታቸው ሊገነዘቡ የሚችሉት የመጽሐፍ ቅዱስ እውቀት ደረጃ አለ። ሆኖም ግን ጥልቅ የሆነ መረዳት፥ የእግዚአብሔርን ጥልቅ ነገር የመረዳትና በሕይወት ተግባራዊ ማድረግ የሚቻለው በመንፈስ ቅዱስ ላተሞሉ ሰዎች ብቻ ነው። ጥልቅ፥ ሕይወትን የሚለውጡ የመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶች በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት የሚገላጡት እርሱ ሕይወቱን በሚሞላበት ሰው ዘንድ ብቻ ነው (1ኛቆሮ. 2፡12፡3፡1፥ 2፤ 1ኛ ዮሐ 2፡20፥ 26-27)። አንድ ሰው መጽሐፍ ቅዱስ የሚለውን ለማንበብና ለመረዳት ቢችልም እንኳ መንፈስ ቅዱስ በሚናገርበት ወቅት በጥሞና ካላደመጠ እውነቱ ወደ ልቡ ጠልቶ አይገባም። ላሕይወቱ ግልጽ የሆነ መመሪያን አይቀበልም። በሌላ በኩል ግን አንድ ሰው በመንፈስ ቅዱስ ከተሞላና እርሱን የሚያደምጥ ከሆነ መጽሐፍ ቅዱስ በምድር ላይ ከሚገኙ ነገሮች ሁሉ ጣፋጭና ውድ ይሆንለታል። መንፈስ ቅዱስ ከእኛ ጋር ለመገኘት፥ ለእኛ ላመናገርና እኛን ለመምራት የሚጠቀምበት ዋና መሣሪያ መጽሐፍ ቅዱስ ይሆናል። ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር በመንፈስ ቅዱስ እማካይነት ጥብቅ የሆነ ግንኙነት የሚኖረን በእግዚአብሔር ቃል ላይ ጊዜ የምንወስድ ከሆነ ነው። ክርስቲያኖች የእግዚአብሔርን ቃል በማንበብ ሐሜት የማያደርጉና መንፈስ ቅዱስ እነርሱን ይናገርና ሕይወታቸውን ይለውጥ ዘንድ የማይጠቀምበት ከሆነ ምክንያቱ በመንፈስ ቅዱስ ያላመሞላታቸው ይሆናል።  የመንፈስ ቅዱስ ህልውና ወይም ሙላት ራሱን የሚያረጋግጥባቸው ሌሎች በርካታ መንገዶች አሉ። በመንፈስ ቅዱስ በምንሞላበት ጊዜ እምልኮአችንና ለእግዚአብሔር የምንሰጠው ክብር ይለወጣል (ኤፌ. 5፡18 20)። በስግብግብነት የተሞላው ፍላጐታችን በሕይወታችን ገዥ ስለማይሆን አንዳችን ለሌላችን እራሳችንን ለማስገዛት አስተሳሰባችን ይለወጣል (ኤፈ. 5፡21)። በመንፈስ ቅዱስ በምንሞላበት

በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ማረጋገጫዎች Read More »

ከኤፌ 5፡18-20 በመንፈስ ቅዱስ ስላ መሞላት ምን ልንመለከት እንችላለን?

1. ትእዛዝ ነው። በመንፈስ ቅዱስ መሞላት እንዳለብን ተነግሮናል። ይህ ሁለት ነገሮችን ያመለክታል። በመጀመሪያ ለመታዘዝ ወይም ላለመታዘዝ ምርግ እንዳለን ነው። በመንፈስ ቅዱስ እንሞላ ዘንድ በእግዚአብሔር ጋር ለመሥራት እንችላለን። ወይም በመንፈስ ቅዱስ ከመሞላት የሚያግደንን ኦኗኗር መኖር እንችላለን። ሁለተኛ በዚህ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት በአንድ ወይም በሌላ መንገድ ተሳታፊዎች መሆናችንን ያመለክታል። እግዚአብሔር የማንሳተፍበትን ነገር እንድናደርግ አያዘንም። ስለዚህ በመንፈስ ቅዱስ እንሞላ ዘንድ ከእግዚአብሔር ጋር ለመሥራት የምንችልበት መንገድ አለ። የእግዚአብሔር ሉዓላዊ ዕቅድ የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ከግለሰቡ ፈቃድ ጋር የሚሄድ እንዲሆን አድርጐታል። መንፈስ ቅዱስ በሕይወታችን እንዲሞላና እንዲጠቀምብን ማድረግ ወይም በከፊልም ቢሆን ይህ እንዳይሆን መከላከል እንችላለን።  2. በተደጋጋሚ የሚፈጸም ተግባር ነው። በግሪክ ቋንቋ በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ትእዛዝ የአሁን ጊዜን በሚያመለክት ግሥ ነው የተጻፈው። ይህ ማለት በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላታችን ሁልጊዜ እርግጠኞች መሆን አለብን ማለት ነው። ይህ ማለት በመንፈስ ቅዱስ ልንሞላ፥ በሆነ ምክንያት ደግሞ ይህን ሙላት ልናጣና እንደገና መሞላት ሊያስፈልገን ይችላል ማለት ነው። ይህ እውነት በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ተመልክቷል። የመጀመሪያዎቹ ደቀ መዛሙርት በበዓለ ኀምሣ ቀን በመንፈስ ቅዱስ ተሞልተው ነበር (የሐዋ. 2፡4)። ቆይቶ ጴጥሮስ በካህናት ጉባኤ የፍርድ ወንበር ፊት በቀረበ ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ እንደተሞላ ተጽፏል (የሐዋ. 4፡31)።  3. የመንፈስ ቅዱስ ሙላት በጣም በተላመደ ነገር ግን ኃይል በሞላበት መንገድ ተገልጧል። በግሪኩ ቋንቋ ኤፌ. 5፡18-21 ያለው ቃል አንድ ዐረፍተ ነገር ነው። አንድ ትእዛዝ ማላትም በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ» የሚለውን ይዟል። ይህ አንዱ ትእዛዝ በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት ምልክት የሚሆኑ አራት ቅድመ-ሁኔታዎችን ያስከትላል። እነርሱም መናገር (ቁጥር 19)፥ መዝሙር (ቁጥር 19)፥ ምስጋና ማቅረብ (ቁጥር 20) እና ለሌሎች መገዛት (ቁጥር 2) ናቸው።  በመንፈስ ቅዱስ በምንሞላበት ጊዜ መሞላታችን የሚረጋገጠው እንዴት ነው? በመንፈስ ቅዱስ መሞላት ክአስደናቂ ድርጊቶች ጋር እንደሚያያዝ እናስብ ይሆናል። ምናልባት የሆነ ታላቅ ተአምር ወይም ልዕለ-ተፈጥሮአዊ ምልክቶች እንደሚያጅቡት እናስብ ይሆናል። ጳውሎስ በእነዚህ ጥቅሶች የሚናገረው ነገር ይህን አይደለም። የመንፈስ ቅዱስ መሞላት በሁለት ዋና መንገዶች ራሱን ይገልጻል። በመጀመሪያ፥ አመላለካችን ይቀየራል። ልባችን በመዝሙርና በምስጋና ይጥለቀለቃል።  በሁለተኛ ደረጃ ፥ በመንፈስ ቅዱስ መሞላታችን ከሌሎች ጋር ያላንን ግንኙነት ይቀይራል። ተፈጥሮአችን የሆነውን የለለታምነታችንን ዝንባሌ ቀይረን በትሕትና ዝቅ ብለን ለሌሎች እራሳችንን እንድናስገዛ ያስችለናል። በዕድሜ የገፉ ለወጣቶች ፍላጐት እንደዚህም ወጣቶች በዕድሜ የገፉ ሰዎች ፍላጐት ይገዛሉ። ወንዶች ለሴቶች ሴቶችም ላወንዶች አመለካከት ይገዛሉ። ባሎች ለሚስቶች፥ ሚስቶች ደግሞ ለባሎች ይገዛሉ። ሀብታሞች ለድሆች፥ የተማሩት ላልተማሩት ወዘተ… ይገዛሉ። ሰዎች እግዚአብሔር በሰውዩው ሕይወት ኃይለኛ ነገር እየሠራ እንደሆነ ለማየት እስከሚገደዱ ድረስ ግንኙነቶች ይቀየራሉ።  ጥያቄ፡- ሀ) በመንፈስ ቅዱስ ስለ መሞላት ይህ የተመለከትነው መረዳት እኛ ብዙ ጊዜ ካለን አመለካከት የተለየ የሚሆነው እንዴት ነው? ለ) መንፈስ ቅቶስ ለእግዚአብሔር ክብር የሆነውን ነገር በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያደርግ ዘንድ ሥርዓት የሞላበት አምልኮና መልካም ግንኙነቶች ከሁሉ በላይ አስፈላጊ ነገሮች የሚሆኑት ለምንድን ነው?  የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ከሕይወታችን የሚቋረጥበት ተቀዳሚ ምክንያት የራሳችንን ሕይወት ኃጢአት በሞላበት መንገድ ልንቆጣጠር በምንሞክርበት ጊዜ ነው። የራሳችንን ሕይወት ልንቆጣጠር በምንወስንበት ወቅት መንፈስ ቅዱስ እኛን መቆጣጠሩን ያቆማል። ነገር ግን ንስሐ በምንገባበትና እግዚአብሔር ሕይወታችንን በሙላት እንዲቆጣጠር በምንጠይቅበት ወቅት መንፈስ ቅዱስ እንደገና ይሞላናል።  በክርስቲያኖች ሕይወት ብዙ ጊዜ ከደኅንነታቸው በኋላ ቀውስ የተፈጠረባቸው ወቅቶች ይኖራሉ። ውስጣዊ የሆነ ጥልቅ ሕይወታቸውን ለመቆጣጠር የሚካሄድ ትግል አለ። መንፈስ ቅዱስ በሕይወታችን ዙፋን ላይ በመቀመጥ የምንፈልገውን፥ የምናደርገውንና የምንናገረውን ሁሉ ላመቆጣጠር ይፈልጋል። በሕይወት ዘመናችን ሁሉ ግን የኖርነው እራሳችንን በመቆጣጠር ነው። ስለዚህ ታላቅ ጦርነት ይካሄዳል። በመጨረሻ ይህ ራስ ወዳድ የሆነው መንፈሳችን ይሰበራል። ለእግዚአብሔር ቁጥጥር እራሳችንን እሳልፈን እንሰጣለን። ትልቁ ጦርነት ከተጠናቀቀ በኋላ በሕይወታችን ታላቅ ለውጥ ይከናወናል። ታላቅ ደስታና ሰላም ይሆናል። አገልግሎታችን ኃይልን ይቀዳጃል። ከእግዚአብሔር ጋር የምናደርገው ጉዞ ጣፋጭና በጥብቅ ቁርኝት የሚካሄድ ይሆናል። ሕይወታችንን ለመቆጣጠር የሚደረጉ እነስተኛ ውጊያዎች ይኖራሉ። ለኃጢአታዊ ተፈጥሮአችን እራሳችንን የምናስገዛበትና እግዚአብሔር በላያችን ላይ እንዳይሠለጥን የምናደርግባቸው ጊዜያት ይኖራሉ። የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ወይም ቁጥጥር በዚያ ነጥብ ላይ ይጠፋል። ነገር ግን ለመንፈስ ቅዱስ ድምፅ ንቁ የመሆን ልምምድ በሕይወታችን ስለሚኖር ወዲያውኑ ወደ ጸጋ ዙፋኑ ፊት በመቅረብና ይቅርታን በመጠየቅ በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ሥር ወደ መኖሩ እንመለሳለን። ከዚያም እንደገና በመንፈስ ቅዱስ እንሞላና በመንፈሳዊ ሕይወታችን እንደገና እንቀጥላለን። ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ በሰው ሕይወት ውስጥ ከሚሠራቸው ሥራዎች አንዱ የበላይነት አግኝቶ ይቆጣጣር ዘንድ ወሳኙን ጦርነት ማካሄድ ነው። ከዚያም በክርስቲያን ሕይወት ዘመን ሁሉ የሕይወቱን እያንዳንዱን ክፍል የበለጠ በበላይነት ይቆጣጠር ዘንድ መንፈስ ቅዱስ ትናንሽ ጦርነቶችን ያካሄዳል። በመንፈሳዊ ሕይወት ማደግ ማለት ሕይወታችን ለዘላቄታው በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ሥር እንዲሆን መፍቀድን እንደሚያካትት እናያለን።  ጥያቄ፡- ሀ) ስለ ራስህ ሕይወት አስብ። የእግዚአብሔር መንፈስ ሕይወትህን እንዳይቆጣጠር የታገልክባቸው ጊዜያት በእርግጥ ነበሩን? ያንን ልምምድህን ግላጽ። ለ) እንደዚህ ዓይነት አስቸጋሪ ልምምድ ካልነበረህ መንፈስ ቅዱስ ከዚህ ቀደም እንደሞላብህ እሁንም ሕይወትህን እያገዘ ለመሆኑ ምን ማስረጃ አለህ? ሐ) መንፈስ ቅዱስ ሙሉ በሙሉ በሥልጣን እንዲገዛህ ያልፈቀድክባቸውን የሕይወትህን ክፍሎች እንዲያሳይህ በጸሎት ትጠይቀው ዘንድ አሁን ጊዜ ውሰድ። ስለ እነዚያ ሁኔታዎች ንስሐ ግባ። መንፈስ ቅዱስ እንደ አዲስ እንዲሞላህና ኢየሱስን እንድትመስል እንዲረዳህ ጸልይ።  እንግዲያውስ በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ትርጉሙ ምንድን ነው? በመንፈስ ቅዱስ መሞላት ክርስቲያን ሕይወቱን ለመንፈስ ቅዱስ በማስገዛት በባሕርይና በተግባር የበለጠ ኢየሱስን እየመሰላ እንዲሄድ መንፈስ ቅዱስ ሕይወቱን እንዲሠራ የሚፈቅድበት ተደጋጋሚ ልምምድ ነው። ምንጭ፡- “የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ”፣ በቲም ፌሎስ ተጽፎ፣ በጌቱ ግዛው የተተረጎመ እና በኤስ አይ ኤም ጽሑፍ ክፍል የተዘጋጀ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

ከኤፌ 5፡18-20 በመንፈስ ቅዱስ ስላ መሞላት ምን ልንመለከት እንችላለን? Read More »

የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምንድን ነው?

ጥያቄ፡– የሚከተሉትን ጥቅሶች ተመልከት። ዘፀኤ 31፡3፤ 36፡1፤ ዘዳ 34፡9፤ ሉቃስ 1፡5፥ 41፥ 67፥ 2፡4፤ የሐዋ. 2፡4፤ 4፡8፥ 31፤ 9፡17-20፤ 13፡9-11። ሀ) በእነዚህ ጥቅሶች በመንፈስ ቅዱስ የተሞሉ የተለያዩ ሰዎችን ጥቀስ። ለ) በመንፈስ ቅዱስ መሞላታቸውን የሚያረጋግጥ ምን ነገር አደረጉ?  በመንፈስ ቅዱስ ስለ መሞላት በምናስብበት ጊዜ ወደ አእምሮአችን የሚመጣው ነገር የሆነ አስደናቂ ነገር ነው። ለምሳሌ በመንፈስ በመሞላትን ስናስብ ታላቅ የፍልስጥኤም ሠራዊትን ያሸነፈውን ሳምሶንን እናስባለን። ወይም ደግሞ በበዓለ ኀምሣ ቀን የታዩትን የእሳት ልሳኖችና በልሳናት መናገርን እናስባለን። ይህ የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምን እንደሚመስል ትክክለኛውን ሥዕል የሚሰጥ ነውን? የብሉይ ኪዳንና የአዲስ ኪዳን መጻሕፍትን በአጠቃላይ ከተመለከትን በመንፈስ ቅዱስ ተሞልተው ያልተለመዱና ልዕለ-ተፈጥሮአዊ የሆኑ ነገሮች ባደረጉ ሰዎች ታሪክ የተሞላ ነው። በመንፈስ ቅዱስ የተሞሉ ነገር ግን ከተላመዱ ነገሮች ያልተለዩ ተግባራት የፈጸሙ ሌሎች ሰዎችም ነበሩ። ቀጥሎ በመጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ የተለያዩ ሰዎችን መሙላቱን የሚያሳዩ ጥቂት ምሳሌዎችን እናቀርባለን።  ባስልኤል በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ የመገናኛውን ድንኳን የሚሠራበትን ጥበብ አገኘ (ዘፀአ 3፡3)።  ኢያሱ በጥበብ መንፈስ በመሞላት የእግዚአብሔርን ሕዝብ ለመምራት ቶላ (ዘዳግ34፡9)።  መጥምቁ ዮሐንስ ከመወለዱ በፊት ጀምሮ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ ነቢይ ተብሎ ተጠራ (ሉቃ. 1፡5)።  ኤልሳቤጥና ዘካርያስ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልተው ትንቢት ተናገሩ (ሉቃ. 1፡41፤ 67)።  ደቀ መዛሙርት በመንፈስ ቅዱስ በመሞላት በልሳኖች መናገር ቻሉ (የሐዋ. 2፡4)።  ጴጥሮስ በመንፈስ ቅዱስ በመሞላት ለመሪዎች መናገር ቻለ የሐዋ. 4፡8)።  ደቀ መዛሙርት በመንፈስ ቅዱስ ተሞልተው የእግዚአብሔርን ቃል በግልጥ ተናገሩ የሐዋ. 4፡3)።  ሰባቱ ዲያቆናት በተለይ ደግሞ እስጢፋኖስ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልተው የተቸገሩትን የመርዳትና ወንጌልን የመስበክ ስጦታ ነበራቸው (የሐዋ. 6፡3)።  እስጢፋኖስ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ በሰማይ ያለውን ኢየሱስን ተመለከተ (የሐዋ. 15)።  ጳውሎስ በመንፈስ ቅዱስ በመሞላት ለእግዚአብሔር በድፍረት የሚመሰክር ሆነ (የሐዋ. 9፡17-20)።  ጳውሎስ በመንፈስ ቅዱስ በመሞላት በኤልማስ ላይ የፍርድ መልእክት አስተላለፈ የሐዋ. 13፡9-10።  በመንፈስ ቅዱስ የተሞሉ የተለያዩ ሰዎችን የሚያሳየው ይህ ዝርዝር ሰው በመንፈስ ቅዱስ በሚሞላበትና በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ቁጥጥር ሥር በሚሆንበት ወቅት የሚያደርገው አንድ የተለየ ነገር እንደሌለ በግልጽ ያመላክታል። ለአንዳንዶች ለእግዚአብሔር ክብር የሚሆን አንድ ነገርን ለመገንባት ይሆናል። ለሌሎች ሠራዊትን የመምራትና ጠላትን ድል የማድረግ፥ የመተንበይ፥ ራእይ የማየት ወይም ያለፍርሃት የመመስከር፥ ወዘተ ተግባር ይሆናል። የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ውጣዊ መግለጫ የተለያየ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን በመንፈስ ቅዱስ በተሞላ ሰው ሕይወት ውስጥ የሚፈጸመው ነገር ተመሳሳይ ነው። ከላይ የተመለከትናቸው ሰዎች በሙሉ በተፈጥሮአዊ ብርታታቸው ሊያደርጉ የማይችሉትን ነገሮች ማድረግ ችለዋል። እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በተፈጥሮአዊ ችሎታቸው ሊያደርጉት ፈጽሞ የማይችሉትን ነገር እንዲያደርጉና ለእግዚአብሔር ክብር እንዲያመጡ አድርጐአቸዋል።  ጥያቄ፡- ኤፌ. 5፡18-21 አንብብ። ሀ) የመንፈስ ቅዱስ ሙላት የተነጻጸረው ከምን ጋር ነው? ለ) አንድ የሰከረ ሰው ሊያሳያቸው የሚችላቸውን የተለያዩ ባሕርያት ግላጽ። እነዚህ ባሕርያት በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ሥር በሆንን ጊዜ ከሚፈጸሙት ነገሮች ጋር የሚመሳሰሉት እንዴት ነው? ሐ) በዚህ ጥቅስ ላይ የሚገኘው ግሥ የተገለጸው በምን ጊዜ ነው? ስለ አንድ ጭብጥ ነው የሚገልጸው? ጥያቄ ነው የሚጠይቀው? ወይስ ትእዛዝ ነው የሚሰጠው? መ) ጳውሎስ የመንፈስ ቅዱስ ሙላት የሚረጋገጥባቸው መንገዶች ምን ምን ናቸው አለ?  መንፈስ ቅዱስ በሰው ሕይወት ውስጥ የሚያደርገውን ይህን ተደጋጋሚ ልምምድ ከሁሉ በላቀ ሁኔታ ለመግለጽ አገልግሎት ላይ የዋለው ቃል «የመንፈስ ቅዱስ ሙላት» የሚለው ይሆናል። የእውነተኛ መንፈሳዊነት ሁሉ ምክንያት መንፈስ ቅዱስ ነው። በሕይወታችን የመሥራት፥ ክርስቶስን እንመስል ዘንድ የመለወጥ፥ የክርስቶስን ህልውና በሕይወታችን የመለማመቶችን ብቻ ሳይሆን በተግባራችንም እንደንመስለው ማድረግ የእርሱ ኃላፊነት ነው። ይህ ተግባር እንዳንድ ጊዜ በአስደናቂ ውጫዊ ሁኔታ ሊገለጽ ይችላል። ነገር ግን ብዙ ጊዜ እስደናቂ ስማይመስል፥ ነገር ግን በፍቅር፥ በደስታ፥ በሰላምና በተስፋ በተሞላ ሕይወት መኖር ነው።  ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ስለሚኖረን ኅብረት በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኙ ግልጽ ትእዛዛት ጥቂት ናቸው። በመንፈስ ቅዱስ እንድንጠመቅ ፈጽሞ አልታዘዝንም። በመንፈስ ቅዱስ እንድንቀባም የተሰጠ ትእዛዝ የላም። ከሁሉ የሚበልጡትን ጠቃሚ መንፈሳዊ ስጦታዎች እንድንፈልግ የተነገረን ቢሆንም እንኳ የመንፈሳዊ ስጦታዎችን ህልውና እንድንፈልግ አልታዘዝንም። ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ስላለን ኅብረት የሚገልጹ እነዚህ ነገሮች በሙሉ ከክርስቲያኖች ሁሉ ጋር አብረው ያሉ ናቸው። ወደ መንፈስ ቅዱስ ሙላት ስንመጣ ግን «መንፈስ ቅዱስ እንዲሞላብን») ታዝዘናል (ኤፌ. 5፡18)። መንፈስ ቅዱስን እንዳናሳዝን (ኤፌ. 4፡30)፥ የመንፈስ ቅዱስን እሳት እንዳናጻፍን (1ኛ ተሰ. 5፡19)፥ እና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር እንድንራመድ (ገላ. 5፡5) ታዝዘናል።  በኤፌ. 5፡18 በመንፈስ ቅዱስ «እንሞላ » ዘንድ እግዚአብሔር ያዝዘናል። በመንፈስ ቅዱስ መሞላት ማለት ምን ማለት እንደሆነ መረዳት እንድንችል በቁጥጥር ሥር ከሚያደርግ ሌላ ዓይነት ነገር ማለትም ከስካር ጋር ማነጻጸር አለብን። በአንድ በኩል በእነዚህ ሁለት ዓይነት መሞላቶች መካከል ከፍተኛ ልዩነቶች አሉ። አንድ ሰው በወይን በተሞላ ጊዜ ራሱን ስለማይቆጣጠር ምን እንደሚያደርግ እንኳ አያውቅም። ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ አንድን ሰው በሚቆጣጠርበት ጊዜ ስለሚፈጸመው ነገር የተሞላው ሰው በሚገባ ያውቃል።  እእምሮአቸውን ይቆጣጠራሉ። በተጨማሪ መንፈስ ቅዱስ በአስደናቂ መንገድ በኃይል እየተጠቀመባቸው እንዳለም ያውቃሉ።  ስለዚህ በወይን በመስከርና በመንፈስ ቅዱስ በመሞላት መካከል ያለው ተመሳሳይነት ምንድን ነው?  1. በወይን ጠጅ የተሞላ ሰው መጠጡ ስለሚቆጣጠረው ከመጠጣቱ በፊት ሊያደርገው የማይችለውን ነገር ማድረግ ይችላል። በተመሳሳይ መንገድ በመንፈስ ቅዱስ መሞላት ማለት በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ሥር መሆንና ተለማምደውት የማያውቁትን ሕይወት መኖር ማለት ነው። ለምሳሌ የሰውዩው ባሕርይ ከቁጣ ወደ ፍቅር ይለወጣል፤ ከላስታምነት ሌሎችን ወደ ማገልገል ይቀየራል።  2. የመጠጥ ሱሰኛ የሆነ ሰው የሚያጋጥመውን ችግር ለመጋፈጥና ብርታት ለማግኘት በመጠጡ ላይ ይደገፋል። በተመሳሳይ መንገድ በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ሥር የሚኖር ሰው እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ኑር ለመኖር ኃይል ይሆነው ዘንድ ፊቱን ወደ እግዚአብሔር ይመልሳል። ምንጭ፡- “የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ”፣ በቲም ፌሎስ ተጽፎ፣ በጌቱ ግዛው የተተረጎመ እና በኤስ አይ ኤም ጽሑፍ ክፍል የተዘጋጀ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምንድን ነው? Read More »

በመንፈስ ቅዱስ መሞላት

«ጌታ ሆይ፥ ሕይወቴ እጅግ ደርቋል። ከአንተ እጅግ እንደራቅሁ ይሰማኛል። እባክህን ድንጋይ ልቤን ለውጥ። የአንተ ህልውና እንዲሰማኝ እድርገኝ። ድምፅህን እንድሰማ እርዳኝ» እያልክ በመጸለይ ላይ ሳለህ ልብህ በድንገት እንግዳ በሆነ ሁኔታ ይሟሟቃል። እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ባለህበት ክፍል እንዳለ ይሰማሃል። ልብህን ደስታ ይሞላውና እግዚአብሔርን ማመስገን ትጀምራለህ።  «ጌታ ሆይ፥ በሕይወቴ ኃጢአት አለ። የምችለውን ሁሉ ላደርግ ብጥር እንኳ ላሸንፈው አልቻልኩም። እባክህን ይህን ኃጢአት እንዳሽንፍ ኃይልህን ስጠኝ» ብለህ ከጸላይክ ጥቂት ጊዜያት ካለፉ በኋላ የሚያስቸግርህ ኃጢአት ክአንተ መወገዱን ታያለህ።  «ጌታ ሆይ፥ በቤተ ክርስቲያን እንድሰብክ ተጠይቄአለሁ። ለማጥናትና ራሴን ለማሰናዳት ሞክሬአለሁ ነገር ግን እንደተዘጋጀሁ አይሰማኝም። ምን ብዩ እንደምናገር እንኳ እንደማላውቅ ነው የሚሰማኝ። ጌታ ሆይ፥ ቃላትን ለመደጋገም አልፈልግም። ነገር ግን የአንተን መልእክት ለማስተላለፍ እሻለሁ። ጌታ ሆይ፥ አሁን ለመናገር እቆማለሁ። እባክህን በእኔ ውስጥ ተናገር» ብለህ በመጸለይ በሕዝቡ ፊት ትቆማለህ። በድንገት ፍርሃትህ ይሸሻል። አስተሳሰብህ ግልጽ ይሆናል። ከዚህ ቀደም አስበሃቸው የማታውቃቸው ቃሎች፥ አሳቦችና መግለጫዎች በአእምሮህ ውስጥ ይፈስሳሉ። ቃሎችህ ልባቸውን እየሰነጠቁ ሲገቡ ከአድማጮችህ ፊት ልታነብብ ትችላለህ። ሰዎች ንስሐ ገቡ። ሌሎች ጌታን ለመከተል ወሰኑ።  ጥያቄ፡- ሀ) እላይ የተጠቀሱትን የሚመስሉ ነገሮች የተለማመድከው (እንዴት ነው? ለ) የሚከተሉትን ጥቅሶች ተመልከት። ዘፀአ 33፡18-23፤ መዝ| (42)፡1-2፤ ኤር. 29፡12-13፤ ፊልጵ. 3፡1-11። የእነዚህ ሰዎች ጸሎቶች ወይም ፍላጐቶች ምን ነበሩ? ሐ) እዚህ ጸሎቶች ልንጸልያቸው ከምንችላቸው ታላላቅ ጸሎቶች አንዱ ዓይነት የሚሆኑት ለምንድን ነው?  ክርስቲያኖች ዛሬ የሚያስፈልጋቸው ብቸኛ ታላቅ ነገር በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ሥር የሆነ ሕይወትን መኖር ነው። ሕይወታቸው ኃይል አልባ የሆኑ በርካታ ክርስቲያኖች አሉ። በኃጢአት ተሸንፈው ይኖራሉ። ከእግዚአብሔር ጋር ያላቸው ግንኙነት ሰልምድ የሚፈጸም ሥርዓት ብቻ ነው። የእግዚአብሔርን ቃል መስማት አቁመዋል። ሰልባቸው ህልውናው አይሰማቸውም። በየሳምንቱ የሚሰብኩት ስብከታቸው ግን ኃይል አልባ ስለሆነ የሰዎችን ሕይወት ፈጽሞ መለወጥ የማይችል የሆነባቸው ብዙ መሪዎች አሉ። እነርሱም ወጥ የሆነ፥ የመንፈስ ቅዱስ ፍሬ የሚታይበትና (ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ በጐነት፥ እምነት፥ የዋህነት፥ ቸርነት ትዕግሥት፥ ራስን መግዛት) ሰዎች በሕይወታቸው ያለውን ለውጥ የሚገነዘቡበት ሕይወት እንዲኖራቸው በመንፈስ ቅዱስ መሞላት ያስፈልጋቸዋል።  ላለፉት ሁለት ሳምንታት የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎችን ስናጠና ቆይተናል። እነዚህ መንፈሳዊ ስጦታዎች አስፈላጊ ቢሆኑም እንኳ በመጨረሻ በየዕለቱ እናንተም ሆናችሁ እኔ እንዴት እንደምንኖር በሕይወታችን ተጽዕኖ የሚያደርግ ከሁሉ የላቀው የመንፈስ ቅዱስ ሥራ «በመንፈስ ቅዱስ መሞላት ነው።» እግዚአብሔርን ደስ በሚያሰኝ መንገድ እንድንኖርና እንድናገለግል የሚያደርገን የመንፈስ ቅዱስ እገልግሎት ይህ ነው። በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ሥር በምንመላለስበት ወቅት በየዕለቱ በመንፈሳዊ ብስለት እያደግንና ኢየሱስን እየመሰልን እንሄዳለን። በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ሥር ሆነን እንደ ኢየሱስ እናስባለን፥ እንደ ኢየሱስ እንኖራለን፥ ለእርሱ ክብር የእርሱን ተግባራት እንፈጽማለን።  ጥያቄ፡- በመንፈስ ቅዱስ የተሞሉ ክርስቲያኖች በቤተ ክርስቲያኖቻችን ውስጥ መኖራቸው ጠቃሚ የሚሆነው ለምንድን ነው?  በክርስትና ታሪክ ሁሉ ውስጥ ከማንኛውም ተራ ክርስቲያኖች የተለዩ ክርስቲያኖች ነበሩ። ለእግዚአብሔር ያላቸው ቅናት እጅግ የሚቀጣጠል ከመሆኑ የተነሣ ሕይወታቸው እግዚአብሔርን የበለጠ ለማወቅ የሚያጓጓ ነው። ወይም በእግዚአብሔር ላይ የነበራቸው እምነት ታላቅ ስለሆነ ለእግዚአብሔር አስደናቂ ነገሮችን ለማድረግ የሚችሉ ነበሩ። አንዳንዶቹ እጅግ ልዩ ከመሆናቸው የተነሣ እነርሱ ባሉበት መሆን በእግዚአብሔር ፊት እንደ መገኘት ነበር። እነዚህን ክርስቲያኖች ልዩ ያደረጋቸው ምንድን ነው? ይህ የሕይወት ደረጃ ለተመረጡ ጥቂቶች ብቻ የተሰጠ ነውን? እንደ እነርሱ ለመሆን ምን ማድረግ አለብን?  የእነዚህን ታላላቅ ክርስቲያኖች ሕይወት ስናጠና ሁላቸውም በሕይወታቸው ሰቆቃ የነበረባቸው ወቅት ነበር። ይህ ጊዜ እግዚአብሔርን በዚያ ሁኔታ ውስጥ እጅግ የፈለጉበትና እግዚአብሔርም በእስደናቂ መንገድ የመለሰላቸው ጊዜ ነበር። እንደዚህ ዓይነቱ ልምምድ ስእነዚህ ትላልቅ ቅዱሳን ሕይወት በተደጋጋሚ በመከሰቱ በመንፈሳዊ ሕይወታቸው የሚታየው እድገት ከአንድ ኮረብታ ወደ ሌላ ከፍተኛ ኮረብታ የመዝለል ያህል ነበር። እነዚህ የቀድሞ ትላልቅ ክርስቲያኖች ከእግዚአብሔር ጋር የነበራቸውን ግንኙነት ለመግለጽ በተለያዩ ቃላት ተጠቅመዋል። አንዳንዶች በመንፈስ ቅዱስ መጠመቅ ብለውታል። ሌሎች በመንፈስ ቅዱስ መቀባት ብለውታል። አሁንም ሌሎች የጠለቀ ሕይወት ወይም ደግሞ በረከት ብለውታል። ወይም በመንፈስ ቅዱስ መሞላት የሚሉም አሉ። ስለ ልምምዶች ምንነት የተሳሳተ መረዳትን ሊሰጡ የሚችሉ ቢሆኑም፥ ልምምዳቸውን ለመግለጽ የተጠቀሙባቸው ቃላት በራሳቸው ጠቃሚ አይደሉም። ዋናው አስፈላጊ ነገር ልምምዳቸው ነው። የእግዚአብሔር ፍላጐት ሁላችንም ይህ ልዩ የሆነ ጥልቅ ግንኙነት ከእርሱ ጋር እንዲኖረን ነው። አጥብቀን ከልባችን ብንፈልግ እንደምናገኘው ተስፋ ሰጥቶናል (ኤር 29፡12-13)። በሕይወታችን የእግዚአብሔርን ክብር ከሁሉ በላቀ መንገድ ለማየት ከፈለግን (ዘፀአ 33፡18-23) እግዚአብሔር እራሱን ይገልጥልናል። እግዚአብሔር በጥልቀት እንድንላማመድ ያላስቻለን ነገር እግዚአብሔር ሌሎች ምርጦች ስላሉትና እኛን በተመሳሳይ መንገድ ሊባርከን ስለማይፈልግ ሳይሆን ነገር ግን የእነርሱን ያህል ጥረት ስለማናደርግ ነው። እግዚአብሔር ማንነቱን በጥልቀት የሚገልጸው በሙሉ ልባቸው ለሚፈልጉት ነው። ክርስቲያን ከእግዚአብሔር ጋር የሚያድግ ኅብረት እንዲለማመዱ በመጀመሪያ ፍላጐት እንዲኖረው ከማድረግ ጀምሮ በመርዳት የሚሠራ መንፈስ ቅዱስ ነው። ምንጭ፡- “የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ”፣ በቲም ፌሎስ ተጽፎ፣ በጌቱ ግዛው የተተረጎመ እና በኤስ አይ ኤም ጽሑፍ ክፍል የተዘጋጀ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

በመንፈስ ቅዱስ መሞላት Read More »

የመንፈሳዊ ስጦታዎች ትምህርት ማጠቃለያ

ጥያቄ፡- በ1ኛ ቆሮ. 14፡1 ላይ ታላላቅ መንፈሳዊ ስጦታዎችን በብርቱ እንድንፈልግ ተነግርናል። ሀ) ታላላቅ ስጦታዎች እንደሆኑ የምታምናቸውን ጥቀስ። ለ) ከእነዚህ ስጦታዎች አንዱን በማግኘት ምን ለማድረግ የምትችል ይመስልሃል?  ታላላቅ ስጦታዎችን እንዴት መፈለግ እንችላለን? እግዚአብሔር ለቤተ ክርስቲያን ከሰጠው ውድ ስጦታዎች አንዳንዶቹ መንፈሳዊ ስጦታዎች ናቸው። በእነዚህ ስጦታዎች ቤተ ክርስቲያን በውስጧ ያሉትንና ዓለምን ታገላግላለች። መንፈሳዊ ስጦታዎች ቤተ ክርስቲያን የኢየሱላ እጆች፥ አፎችና፥ እግሮች ሆና እንድታገለግል ያደርጋሉ። መንፈሳዊ ስጦታዎች በሙሉ እጅግ አስፈላጊዎች ናቸው። ከመንፈሳዊ ስጦታዎች እንዳንዶቹ እንኳ ቢጐድሉ ብዙ ሳይቆዩ ቤተ ክርስቲያን መፍገምገምና መንፈሳዊ ትጋቷን መጣል ትጀምራለች። ነገር ግን ከሌሎች የላቁና የተሻሉ እግዚአብሔር በልባችን ሸክምን ካኖረ የበለጠ ልንፈልጋቸው የሚገቡ አንዳንድ መንፈሳዊ ስጦታዎች እንዳሉ ተነግሮናል። በእግዚአብሔር ዓይን ከሌሎች የላቁ የሚባሉ መንፈሳዊ ስጦታዎች የትኞቹ መሆናቸውን እንዴት እናውቃለን? አስታውሱ መፈለግ ያለብን በሰው ዓይን የላቁ የሚባሉ መንፈሳዊ ስጦታዎችን አይደለም። ሰው ትኩረት የሚያደርገው ታላቅና መንፈሳዊ በሚመስል ውጫዊ ነገር ላይ ነው። እና ብዙ ጊዜ የምንፈልገው አስደናቂ የሆኑ ነገሮችን ነው። እግዚአብሔር ታላቅ የሚለው ቀን ብዙ ጊዜ እኛ ከምንላው የተለየ ነው።  አንድ መንፈሳዊ ስጦታን ታላቅ የሚያደርጉት ነገሮች ምንድን ናቸው? መንፈሳዊ ስጦታዎች የሚሰጡት ለጋራ ጥቅም መሆኑን ካስታወስን ታላላቹ መንፈሳዊ ስጦታዎች የክርስቶስን አካል ለማነጽ ከሁሉም በላይ የሚጠቅሙት ናቸው። ጳውሎስ በልሳን ከመናገር ስጦታ ትንቢት እንደሚበልጥ የተናገረው ለዚህ ነው። በቤተ ክርስቲያን ለሚገኙ ሁሉ የበለጠ የሚጠቅም ስለሆነ የተሻለ ነበር። መጽሐፍ ቅዱስ ከሁሉ የላቁ ስጦታዎች የሚላቸው ስት ለጦታዎች አሉ።  1. ወንጌልን እንዲሠራጭና ቤተ ክርስቲያን እንድትቆረቆር የሚያስችሉ መንፈሳዊ ስጦታዎች (ሐዋርያነትና ወንጌላዊነት)። እነዚህ ስጦታዎች ቤተ ክርስቲያን እንድትስሩሩ የባሕል ልዩነት ሳያግዳት ወንጌል ወዳልደረሰባቸው ሥፍራዎች ወንጌልን እንድታዳረስ ያስችሏታል።  ጥያቄ፡– ይህ ስጦታ በቤተ ክርስቲያንህ እንዴት እየተፈጸመ እንዳለ ምሳሌ ስጥ። ይህ ስጦታ እጅግ ጠቃሚና ፍጹም የማይታለፍ ለጦታ የሆነው ለምንድን ነው?  2. የቤተ ክርስቲያን አባላት በእግዚአብሔር ቃል እውቀትና በቤተ ክርስቲያንና በማኅበረሰባቸው መካከል እግዚአብሔርን በማገልገል ችሎታ እንዲያድጉ የሚረዱ ስጦታዎች (የማስተማር፥ የትንቢትሩ የስብከት)።  3. ለቤተ ክርስቲያንና ለጎስቋላ ሰዎች ሥጋዊ ችግሮች ክብካቤ ለመስጠት የሚረዱ ክርስቲያናዊ ፍቅርን የሚያንጸባርቁ መንፈሳዊ ስጦታዎች ፈውስና ምሕረት ማድረግ)  ጥያቄ፡- እነዚህ ሦስት ዓይነት ስጦታዎች ለቤተ ክርስቲያን አስፈላጊ የሆኑት ለምንድን ነው?  በልሳናት መናገር፥ የተነገረውን መተርጐም፥ ተአምራትን ማድረግና አስተዳደር ወዘተ… ለእነዚህ ዋነኛ የመንፈሳዊ ስጦታዎች ድጋፍ ሰጭ ናቸው። አስፈላጊ ቢሆኑም እንኳ ከሁሉ የላቁ ስጦታዎች ግን አይደሉም። እነዚህ ስጦታዎች ብዙ ጊዜ ድንቀኛ ቢሆኑም እንኳ የቤተ ክርስቲያን መሠረተች ግን አይደሉም። ያለ ዋንኞቹ ስጦታዎች ቤተ ክርስቲያን ልትኖር አትችልም። እዚህ ስጦታዎች ባይኖሩአትም እንኳ ቤተ ክርስቲያን ያለማቋረጥ መሥራትና ዓላማዋን መፈጸም ትችላለች። ስለዚህ እጅግ አስፈላጊ ባልሆኑ አንዳንድ ስጦታዎች ላይ ስናተኩር ውስጣዊ አሳባችንን ልንመረምር ይገባል። መንፈሳዊ ስጦታዎችን የምንፈልገው በእርግጥ በተሻለ ሁኔታ ለማገልገል ነውን? ወይስ በትዕቢትና በኩራት እራሳችንን ለመገንባት ነው?  ታላላቅ ስጦታዎችን እንዴት እናገኛለን?  1. መንፈሳዊ ስጦታዎችን እርሱ እንደ ፈለገ ማከፋፈል የመንፈስ ቅዱስ ሉዓላዊ ደስታ መሆኑን ማስታወስ አለብን። ሆኖም ቀን እግዚአብሔር ከሰጠን መብቶች አንዱ መንፈሳዊ ስጦታን ይሰጠን ዘንድ መንፈስ ቅዱስን መጠየቅ ነው። ውስጣዊ ዓላማችን ትክክል ከሆነ ብዙ ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ጥያቂዎቻችንን ይመልሳል።  2. ወደ ቤተ ክርስቲያንና ወደ ዓለም ችግሮች መመልከት አለብን። ለእነዚህ ችግሮች በሚያስፈልጉ መፍትሔዎች ላይ በመመሥረት ከሁሉ በላይ አስፈላጊ የሆኑ ስጦታዎች የትኞቹ እንደሆኑ እንገመግማለን።  3. ልባችንን በጥንቃቄ መመርመር አለብን። በአንድ ነገር ለመሳተፍ እዚአብሔር ፍላጐትን ሰጥተሃልን? መንፈስ ቅዱስ ይህን ፍላጐትህን ተጠቅሞ የላቀ ስጦታን እንድትሻ እያደረገህ ነውን?  4. አንድ ስጦታ የምንፈልግበት ውስጣዊ ዓላማችን ምንድን ነው? መንፈሳዊ ስጦታዎችን የተቀበልን ቢሆንና ትክክለኛ ዓላማ ሳይኖረን ፍጻሜያችን ቤተ ክርስቲያንን መጉዳት ይሆናል። ለምሳሌ አንዳንድ ሰዎች የመጋቢነት አገልግሎት ለመያዝ የሚፈልጉት ከዚህ ኃላፊነት የሚገኘውን ክብር ለመውሰድ ነው። በዚህ መንፈስ መጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት ቢገቡና ከዚያም በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አገልግሎት ማካሄድ ቢጀምሩ የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ከመሆን ይልቅ ሥልጣናቸውን የሚጭኑ አምባገንን ገዢዎች በመንጋው ላይ ይሆናሉ። በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የእግዚአብሔርን መንጋ እያጠሩ ያሉ እንደነዚህ ዓይነት መሪዎች በብዛት አሉ። መንፈሳዊ ስጦታዎችን በምንፈልግበት ወቀት ሊኖረን የሚገባ ብቸኛ ትክክለኛ ዓላማ እዚእብሔርንና ቤተ ክርስቲያንን በተሻለ መንገድ ማገልገል መሆን አለበት። እራሳችንን ሳይሆን ሌሎችን ለማነጽ መጣር ይገባናል።  5. እግዚአብሔር አስፈላጊውን መንፈሳዊ ስጦታ ይሰጥህ ዘንድ በጸሎት ጠይቀው። እግዚአብሔር ጸሉትህን እንደመለሰ እድርገህ እስከምታምን ድረስ መጸለይህን ቀጥል። እግዚአብሔርን በጸሎት በምትጠይቀው ጊዜ፥ «እሺ» ወይም «እምቢ» የሚል መልስ ሊሰጥህ መብት እንዳለው አስታውስ። እግዚአብሐር ላሉት ጥያቄህ የሰጠው መልስ አይሆንም ከሆነ ሌላ የተሻለ ዕቅድ ለሕይወትህ ስላለው ብቻ ነው።  6. ያንን መንፈሳዊ ስጦታ ላለው ሰው ሥልጣን እራስህን አስገዛ። ከእርሱ ወይም ከእርሷ ተማር። በእርሱ አመራር በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ማገልገል ጀምር። ያ ሰው እግዚአብሔር ይህን ስጦታ ሰጥተህ እንደሆነና እንዳልሆነ ሊያረጋግጥልህ ይችላል።  ጥያቄ፡- ሀ) እጅግ አስፈላጊ መንፈሳዊ ስጦታዎች ተብለው ከላይ የተዘረዘሩትን መንፈሳዊ ስጦታዎች ተመልከት። በቤተ ክርስቲያናችሁ ውስጥ ከእነዚህ ስጦታዎች መካከል በጣም የሚፈለጉት ወይም የሌሉት ስጦታዎች የትኞቹ ይመስሉሃል? ላ) ከእነዚህ መንፈሳዊ ስጦታዎች እግዚአብሔር እንድትሳተፍባቸው የሚፈልገው የትኞቹ ይመስሉሃል? ከላይ የተመለከቱት ቅደም ተከተሎች እነዚህን ስጦታዎች ለመጠቀም እንድትጀምር እንዴት ይረዱሃል?  መንፈሳዊ ስጦታዎቻችንን እንዴት እናውቃለን?  ክፍሌ በማደግ ላይ ያለ ክርስቲያን ነበር። ክርስቲያን ከሆነ አንድ ዓመት ሆኖታል። ሌላ ክርስቲያን ደቀ መዝሙር እያደረገው ሲሆን ያለማቋረጥ ወደ ቤተ ክርስቲያን ይሄድ ነበር። ክፍሌ፥ እግዚአብሔር በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንዲሳተፍ እንደሚፈልግ ተገነዘበ። ወጣቶች በሙሉ በመዘመራን ቡድን ውስጥ መግባት ይፈልጉ ነበር። ከዚህ ውጭ ግን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ለማገልገል ብዙ ዕድል ያለ አይመስልም ነበር። አንድ ቀን ክፍሌ ከሽማግሌዎች ወደ አንዱ በመሄድ «በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ለመሥራት እፈልጋለሁ፤ ምን ማድረግ እችላለሁ?» በማለት ጠየቀ።  ጥያቄ፡- ሀ) ሽማግሌ ብትሆን ኖሮ ለክፍሌ የምትሰጠው መልስ ምን ይሆን ነበር? ለ) በቤተ ክርስቲያን ምእመናንን ሁሉ በአገልግሎት እንዲሳተፉ ማድረግ ጠቃሚ የሆነው ለምንድን ነው? ሒ እንድ የቤተ ክርስቲያን መሪ ምእመናኑ መንፈሳዊ ስጦታዎቻቸውን እንዲያውቁ [ለማድረእንዴት አብሮአቸው መሥራት ይችላል? መ) መንፈሳዊ ላጦታዎችህ የትኞቹ እንደሆኑ ታምናለህ? ሀ) መንፈሳዊ ስጦታዎች እዚያ እንደሆኑ እንዴት ታውቃለህ?  ሰዎች ብዙ ጊዜ በሕይወታቸው ትግል ከሚገጥሙባቸው ጥያቄዎች አንዱ መንፈሳዊ ስጦታዎቻቸው የትኞቹ እንደሆኑ የመወሰን ጉዛይ ነው። ብዙ ክርስቲያኖች በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከመሳተፍ የሚታቀቡት መንፈስ ቅዱስ የሰጣቸውን ስጦታዎች ባለማወቃቸው ነው። ሌሎች ከርሰቲያኖች ደግሞ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ማምላክን ብቻ ይፈልጋሉ። ወደ ቤተ ክርስቲያን በመምጣት መዝሙር ይዘምራሉ። ደግሞም የእግዚአብሔርን ቃል ይሰማሉ። ነገር ግን በሌሎች ነገሮች ለመሳተፍ ፈቃደኛ አይደሉም። በሁለቱም መንገዶች ቢሆን መንፈስ ቅዱስ የሰጣቸው መንፈሳዊ ስጦታዎች አገልግሎት ላይ አልዋሉም።  እንደዚህ ዓይነት አመለካከት ቢያንስ ሁለት አሉታዊ ውጤቶች አሉት፡-  1 ግለሰቡ የበሰለ መንፈሳዊ ክርስቲያን ሆኖ ለማደግ አይችልም። ስኤፌ. 4፡12-13 የመንፈሳዊ ስጦታዎቻችን አጠቃቀም ከመንፈሳዊ እድገታችን ጋር በቅርብ የተያያዘ መሆኑን እናነባለን። መንፈሳዊ ስጦታችንን ካልተጠቀምን ራስ ወዳድ ወደ መሆን እናዘነብላለን። በራሳችን ዕቅድ ላይ ብቻ በማተኮር ሰዎችን በእምነታቸው ያድጉ ዘንድ እንዴት እንደምንረጻቸው ሳናስብ እንቀራለን። በኃላፊነት ከመሳተፍ ይልቅ በመገልገል ብቻ የምንረካ ከሆነ ባለመሳተፋችንና እግዚአብሔር የሰጠንን ስጦታዎች ባለመጠቀማችን . እምነታችን አያድግም።  ጥያቄ፡– በቤተ ክርስቲያንህ ስላሉ አባላት አስብ። አብዛኛዎቹ መንፈሳዊ ስጦታዎቻቸውን በመጠቀም በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ይሳተፋሉን? ካልተሳተፉ ለምን?  2. ቤተ ክርስቲያን መሆን ያለባትን ያህል ስኬታማ አትሆንም። ጳውሎስ ብዙ ጊዜ ቤተ ክርስቲያንን ከአካል ጋር እንደሚያወዳድር ትዝ ይልሃል። በክርስቶስ አካል ውስጥ ሰዎች የተለያዩ ክፍሎችን እንዲይዙ የሚያደርጉአቸው እነዚህ መንፈሳዊ ስጦታዎች ናቸው። ስለዚህ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያሉ ሰዎች መንፈሳዊ ስጦታቸውን ካልተጠቀሙ አካሉ እንደታመመ ወይም ጎዶሎ እንደሆነ ያህል ነው። ለምሳሌ እዚእብሔር በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ላሉ ሰዎች የወንገላዊነት ስጦታ እንደሰጠ እናስብ። ወንጌልን ወልዳኑ ሰዎች የሚያደርሱ ስለሆነ የቤተ ክርስቲያን

የመንፈሳዊ ስጦታዎች ትምህርት ማጠቃለያ Read More »