የሕይወት እንጀራ

የእውነተኛና ሐሰተኛ ነቢያት ንጽጽር

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

መግቢያ

ስለ መንፈስ ቅዱስ ለምን እናጠናለን?

ሥነ መለኮት ምንድን ነው?

መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የምንረዳበት ምንጭ

መንፈስ ቅዱስን ማወቅ

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ስፍራ

የመንፈስ ቅዱስ ዋና ኃላፊነቶች ምንና ምን ናቸው?

የመንፈስ ቅዱስ ስሞች

የመንፈስ ቅዱስ ተምሳሌቶች

እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ማን ነው?

መንፈስ ቅዱስ፤ ሦስተኛው የሥላሴ አካል

መጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ አምላክ መሆኑን ያሳየናልን?

መንፈስ ቅዱስ በብሉይ ኪዳን

የእግዚአብሔርን ሕዝብ ይመሩ ዘንድ መሪዎችን ብቁ በማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል እንዲጽፉ በመምራት የሰጠው አገልግሎት

የብሉይ ኪዳን ነቢያት መሢሑ የሚመጣበትን ወቅትና የመንፈስ ቅዱስ አገልግሉት የሚለወጥበትን ጊዜ እስቀድመው አመልክተው ነበር

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት በወንጌላት

መንፈስ ቅዱስ በጌታ ኢየሱስ ሕይወትና አገልግሎት ውስጥ

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የሰጠው ትምህርት፤ ክፍል 1

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ያስተማረው ትምህርት፤ ክፍል 2

ክርስቲያኖች እንደ መንፈስ ቅዱስ ባሉ መሠረታዊ የክርስትና አስተምህሮዎች ላይ ባላቸው አመለካከት ልዩነት የሚያሳዩት ለምንድን ነው?

መንፈስ ቅዱስን በተመለከተ የተለያዩ መረዳቶች የሚታዩት ለምንድን ነው?

በመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችና በአምልኮ ልምምዶች ውስጥ ያሉ ልዩነቶችን እንዴት መያዝ አለብን?

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 1-2 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 3-8 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 9-28)

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 1

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 2

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 3

የጴንጤቆስጤ ሥነ መለኮት ታሪክ

የጰንጠቆስጤና የአንዳንድ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ዋና ትምህርቶች ምን ምን ናቸው?

ከካሪዝማቲክ ትምህርት ለቤተ ክርስቲያን የተረፉ መልካም ውጤቶች

በካሪዝማቲክ የሥነ መለኮት ትምህርት የሚገኙ ሚዛናዊ ያልሆኑ ነገሮች

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል አንድ)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሁለት)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሦስት)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 1)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 2)

በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና ልሳን በመናገር መካከል ያሉ ግንኙነቶች

የመንፈስ ቅዱስ አማኞችን ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ የመምራት አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ እንድናመልክ ይረዳናል

መንፈስ ቅዱስ የክርስቲያኖች ሕይወት ኢየሱስን እንዲመስል የሚሰጠው አገልግሎት

ሰይጣንን ድል የማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

ስለ መንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች መግቢያ

መንፈሳዊ ስጦታ ምንድን ነው?

መንፈሳዊ ስጦታ (ሮሜ 12፡1-8)

መንፈሳዊ ስጦታ (ኤፌሶን 4፡1-16 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ጴጥሮስ 4፡7-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡1-3)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡4-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡12-31 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 13)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡1-19)

መንፈሳዊ ስጦታዎችና የማያምኑ ሰዎች (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡20-40)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 1)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 2) የተለያዩ ዓይነት ልሳናት አሉን?

በቤተ ክርስቱያን ውስጥ ስለሚመጣው ትንቢት ተጨማሪ አሳቦች

ትንቢት ምንድን ነው? ነቢይስ?

የትንቢት ስጦታ ምንድን ነው?

የእውነተኛና ሐሰተኛ ነቢያት ንጽጽር

የትንቢት ስጦታን ለመጠቀም መመሪያዎቹ ምን ምን ናቸው?

የመፈወስና ተአምራትን የማድረግ ስጦታዎች

የብሉይ ኪዳን ተአምራትና አዲሱን ዘመን በተስፋ መመልከት

ተአምራትና ፈውሶች በአዲስ ኪዳን

እግዚአብሔር ፈውስን የሚሰጥባቸው የተለያዩ አሠራሮች

ስለ ተአምራትና ፈውሶች የሚሰጡ የተሳሳቱ አሳቦች

የመንፈሳዊ ስጦታዎች ትምህርት ማጠቃለያ

በመንፈስ ቅዱስ መሞላት

የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምንድን ነው?

ከኤፌ 5፡18-20 በመንፈስ ቅዱስ ስላ መሞላት ምን ልንመለከት እንችላለን?

በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ማረጋገጫዎች

በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት የሚቀርቡ ቅድመ ሁኔታዎች

በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና መንፈሳዊ ብስለት

የመጀመሪያው የመንፈስ ቅዱስ ዋና ሥራ፡- ዘላለማዊው አምላክ በውስጣችን መኖሩ

የመንፈስ ቅዱስ ሁለተኛ ዋና ተግባሩ፡- ወደ ኢየሱስ ማመልከትና እርሱን እንድንመስል ማድረግ።

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች ክለሳ

ጥያቄ፡- ሀ) ኤር. 14፡13-16፤ 23፡9-40 አንብብ። ኤርምያስ ከሐሰተ ነቢያት ጋር ያሳለፈውን ችግር ግለጽ። ለ) ዘዳ 13፡3-5፤ 18፡17-22 አንብብ። ) አንድ ሐሰተኛ ነቢይ ከእውነተኛ ነቢይ የሚለይባቸው መንገዶች ምንድን ናቸው? 2) ሐሰተኛ ነቢይ የሚቀጣው በምን ነበር? 

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የእግዚአብሔርን ቃል ለሕዝብ የሚናገሩ እውነተኛ ነቢያት እንደነበሩ ሁሉ እውነተኛ ነቢያትን በመቃወም የሚሠሩ ሐሰተኛ ነቢያትም ነበሩ። የመጀመሪያዎቹ የእግዚአብሔርን ቃል ይናገሩ የነበሩ ሲሆን ሌሎች ደግሞ በእግዚአብሔር ስም ቢናገሩም እንኳ የሚናገሩት የእግዚአብሔርን ቃል አልነበረም። እውነተኞች ከእግዚአብሔር ስለነበሩ የእግዚአብሔር ሰዎች ሊሰሟቸው ይገባ ነበር። ሐሰተኞቹ ግን በሰይጣን ኃይል ቁጥጥር ሥር ሆነው የሚናገሩ ወይም እራሳቸው የፈጠሩትን ነገር የሚናገሩ ነበሩ። እነዚህን ማንም ሊቀበላቸው አይገባም ነበር። እግዚአብሔር ሐሰተኛ ነቢያትን እጅግ ከመጥላቱ የተነሣ ማንኛውም ነቢይ ሐሰተኛነቱ በሚረጋገጥበት ጊዜ መገደል ነበረበት። 

እስራኤላውያን አንድ ነቢይ፥ እውነተኛ ወይም ሐሰተኛ መሆኑን የሚያውቁት እንዴት ነበር? መጽሐፍ ቅዱስ ሐሰተኛ ነቢያት የሚለዩባቸውን የሚከተሉትን ባሕርያት ይሰጣል። 

1) ሐሰተኛ ነቢያት የእግዚአብሔርን ቃል በቀጥታ የሚቃወም መልእክቶችን ያመጣሉ። እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን በሚናገርበት ወቅት አንድ ነቢይ ወደ እናንተ ቢመጣና ከሙሴ ሕግጋት ጋር በቀጥታ የሚቃረን መልእክት ቢያመጣላችሁ ሐሰተኛ ነቢይ መሆኑን አውቃችሁ ልትገድሉት ይገባል ያላቸው ለዚህ ነበር። ነቢያት ያመጡትን መልእክት የምንመዝንበት የመጨረሻው ሥልጣን ያለው መጽሐፍ ቅዱስ የመሆኑን እውነታ ይህ እንደገና ያስረግጣል። መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ከሚያስተምራቸው ትምህርቶች ከእኛ አተረጓጐም ሳይሆን) አብሮ የማይሄድ ማንኛውም መላእክት ሐሰተኛ ነውና ሊኮነን ይገባዋል። 

2) ሐሰተኛ ነቢያት የተናገሩት መልእክት ልክ እንደተናገሩት አይፈጸምም። እግዚአብሔር የወደፊቱንም የሚያውቅ አምላክ ነው። ስለዚህ ወደፊት የሚፈጸመውን ነገር ለሕዝቡ ማሳወቅ እያስቸግረውም። ስለዚህ እንድ ሰው የወደፊቱን ጉዳይ በዝርዝር ቢያመለክትና ባመለከተው መንገድ ነገሮች ባይከናወኑ ሰውዬው ያመጣው መልእክት የእግዚአብሔር ቃል (ፈቃድ) አልነበረም ማለት ነው። ይህንንም ያለማቋረጥ ካደረገ እርሱ ሐሰተኛ ነቢይ ነው። ከዚህ ቀደም «ጌታ ኢየሱስ በዚህና በዚህ ቀን በዚህና በዚህ ስፍራ ይመጣል» ብለው የተናገሩ ብዙ ሰዎች ነበሩ። ብዙዎች ስላመኗቸው ሥራቸውን ሁሉ ትተው የኢየሱስን መመለስ ተጠባበቁ። ነገር ግን ቀኑ ቢደርስም እንኳ ኢየሱስ እልተመለሰም። ስለዚህ ሰው የምንረዳው ነገር ምንድን ነው? እግዚአብሔር ስለማይሳሳት ከእግዚአብሔር አለመሆኑን ነው። እውነተኛ ነቢያት የሚናገሩት መልእክት በሙሉ በትክክል ይፈጸማል። (ማስታወሻ፡— አንዳንዶች እግዚአብሔር ስለ ወደፊት የሚናገረው ነገር በሙሉ ትክክል ቢሆንም መልእክቱን የሚቀበላው ነቢይ ያለአግባብ ሊረጻውና ያለ አግባብ ሊተገብረው ይችላል የሚሉ አሉ፡፡) 

የአንድን ነቢይ መልእክት ለመመዘን መፈጸሙን ብቻ ማየት በቂ አይደለም። ሰይጣን እንደ ጠንቋዮች ያሉ ተከታዮቹን ስለ ወደፊቱ ጉዳይ እንዲናገሩ ሊረዳቸው ይችላል። የሚናገሩትም መልእክት ብዙ ጊዜ ትክክል ሊሆን ይችላል። ነገር ግን የሚናገሩአቸውን መልእክት ትክክለኛነት ላማረጋገጥ ለረጅም ጊዜ ብንከታተል ከትንቢቶቻቸው ብዙዎቹ አይፈጸሙም። እነዚህ የሐሰተኛ ነቢያት ባሕርያት አብዛኛው እርስ በርስ የተያያዙ ስለሆኑ አንድ ትንቢት መፈጸሙን ለማረጋገጥ አንዱን ዘርፍ ብቻ መመልክት የለብንም በቂ አይደለም። 

3) የሐሰተኛ ነቢያት ባሕርይ ብዙ ጊዜ መልካም አይደለም። አንድ ሰው ነቢይ ነኝ እያላ የእግዚአብሔርን ቅድስና በማያንፀባርቅ መንገድ የሚኖር ከሆነ እውነተኛ ነቢይ መሆኑን ወይም መሆኗን መጠራጠር ተገቢ ነው። አውነተኛ ነቢያት በትሕትና ይመላለሳሉ። አገልግሎታቸውም በሌሎች ሕይወት ውስጥ ትሕትናን ይፈጥራል። 

4) የሐሰተኛ ነቢያት አገልግሎት ለእግዚአብሔር ክብርን አያመጣም። እንድ ሰው ነቢይ ነኝ እያለ ለራሱ ጥቅም፥ ሀብት፥ ክብር ወይም ኃይል ለማግኘት ከሠራ ወይም የአገልግሎቱ ክብር ወደ እግዚአብሔር ሳይሆን ወደ ራሱ የሚሄድ ከሆነ ሰውዩውን መጠራጠር ተገቢ ነው። እግዚአብሔር «ክብሬን ለሌላ አልሰጥም» (ኢሳ. 42፡8) ብሏል። ስለዚህ ከእግዚአብሔር ያልሆነ ማንኛውም ትንቢት ክብርን ለሰው እንጂ ለእግዚአብሔር አያመጣም። እውነተኛ ነቢይ ለኢየሱስ ክብርን ያመጣል፤ ሌሎችም ኢየሱስ ክርስቶስን እንዲያከብሩ ያደርጋል። 

5) የእውነተኛ ነቢይ ትንቢት የመንፈስ ቅዱስ ፍሬን ያፈራል። በክርስቶስ አካል ውስጥ መክፋፈልን አያመጣም። 

ጥያቄ፡- እነዚህ መመሪያዎች አንድ ሰባኪን ወይም ነቢይን ለመመዘን የሚጠቅሙት እንዴት ነው? 

ጥያቄ፡- 1ኛ ቆሮ. 14፡26-40 አንብብ። ትንቢት ለመናገር የሚጠቅሙ የተላያዩ መመሪያዎችን ዘርዝር።

ምንጭ፡- “የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ”፣ በቲም ፌሎስ ተጽፎ፣ በጌቱ ግዛው የተተረጎመ እና በኤስ አይ ኤም ጽሑፍ ክፍል የተዘጋጀ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

የትንቢት ስጦታ ምንድን ነው? የትንቢት ስጦታን ለመጠቀም መመሪያዎቹ ምን ምን ናቸው?

1 thought on “የእውነተኛና ሐሰተኛ ነቢያት ንጽጽር”

የጌታ ጸጋ ከእርስዎ ጋር ይሁን፤ ሀሳብዎን ለመስማት ዝግጁ ነን።

Discover more from የሕይወት እንጀራ

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading