Site icon የሕይወት እንጀራ

የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምንድን ነው?

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

መግቢያ

ስለ መንፈስ ቅዱስ ለምን እናጠናለን?

ሥነ መለኮት ምንድን ነው?

መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የምንረዳበት ምንጭ

መንፈስ ቅዱስን ማወቅ

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ስፍራ

የመንፈስ ቅዱስ ዋና ኃላፊነቶች ምንና ምን ናቸው?

የመንፈስ ቅዱስ ስሞች

የመንፈስ ቅዱስ ተምሳሌቶች

እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ማን ነው?

መንፈስ ቅዱስ፤ ሦስተኛው የሥላሴ አካል

መጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ አምላክ መሆኑን ያሳየናልን?

መንፈስ ቅዱስ በብሉይ ኪዳን

የእግዚአብሔርን ሕዝብ ይመሩ ዘንድ መሪዎችን ብቁ በማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል እንዲጽፉ በመምራት የሰጠው አገልግሎት

የብሉይ ኪዳን ነቢያት መሢሑ የሚመጣበትን ወቅትና የመንፈስ ቅዱስ አገልግሉት የሚለወጥበትን ጊዜ እስቀድመው አመልክተው ነበር

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት በወንጌላት

መንፈስ ቅዱስ በጌታ ኢየሱስ ሕይወትና አገልግሎት ውስጥ

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ የሰጠው ትምህርት፤ ክፍል 1

ኢየሱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ያስተማረው ትምህርት፤ ክፍል 2

ክርስቲያኖች እንደ መንፈስ ቅዱስ ባሉ መሠረታዊ የክርስትና አስተምህሮዎች ላይ ባላቸው አመለካከት ልዩነት የሚያሳዩት ለምንድን ነው?

መንፈስ ቅዱስን በተመለከተ የተለያዩ መረዳቶች የሚታዩት ለምንድን ነው?

በመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችና በአምልኮ ልምምዶች ውስጥ ያሉ ልዩነቶችን እንዴት መያዝ አለብን?

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 1-2 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 3-8 )

በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጡ ትምህርቶች አጠቃላይ መግለጫ (ሐዋ. 9-28)

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 1

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 2

የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በሰው ድነት (ደኅንነት) ውስጥ፤ ክፍል 3

የጴንጤቆስጤ ሥነ መለኮት ታሪክ

የጰንጠቆስጤና የአንዳንድ ካሪዝማቲክ ክርስቲያኖች ዋና ትምህርቶች ምን ምን ናቸው?

ከካሪዝማቲክ ትምህርት ለቤተ ክርስቲያን የተረፉ መልካም ውጤቶች

በካሪዝማቲክ የሥነ መለኮት ትምህርት የሚገኙ ሚዛናዊ ያልሆኑ ነገሮች

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል አንድ)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሁለት)

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት (ክፍል ሦስት)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 1)

በክርስቲያኖች መካከል ከፍተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ክፍሎች (ክፍል 2)

በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና ልሳን በመናገር መካከል ያሉ ግንኙነቶች

የመንፈስ ቅዱስ አማኞችን ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ የመምራት አገልግሎት

መንፈስ ቅዱስ እንድናመልክ ይረዳናል

መንፈስ ቅዱስ የክርስቲያኖች ሕይወት ኢየሱስን እንዲመስል የሚሰጠው አገልግሎት

ሰይጣንን ድል የማድረግ የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት

ስለ መንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች መግቢያ

መንፈሳዊ ስጦታ ምንድን ነው?

መንፈሳዊ ስጦታ (ሮሜ 12፡1-8)

መንፈሳዊ ስጦታ (ኤፌሶን 4፡1-16 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ጴጥሮስ 4፡7-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡1-3)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡4-11 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 12፡12-31 )

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 13)

መንፈሳዊ ስጦታ (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡1-19)

መንፈሳዊ ስጦታዎችና የማያምኑ ሰዎች (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡20-40)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 1)

በልሳናት ስለመናገር ተጨማሪ ጉዳዮች (ክፍል 2) የተለያዩ ዓይነት ልሳናት አሉን?

በቤተ ክርስቱያን ውስጥ ስለሚመጣው ትንቢት ተጨማሪ አሳቦች

ትንቢት ምንድን ነው? ነቢይስ?

የትንቢት ስጦታ ምንድን ነው?

የእውነተኛና ሐሰተኛ ነቢያት ንጽጽር

የትንቢት ስጦታን ለመጠቀም መመሪያዎቹ ምን ምን ናቸው?

የመፈወስና ተአምራትን የማድረግ ስጦታዎች

የብሉይ ኪዳን ተአምራትና አዲሱን ዘመን በተስፋ መመልከት

ተአምራትና ፈውሶች በአዲስ ኪዳን

እግዚአብሔር ፈውስን የሚሰጥባቸው የተለያዩ አሠራሮች

ስለ ተአምራትና ፈውሶች የሚሰጡ የተሳሳቱ አሳቦች

የመንፈሳዊ ስጦታዎች ትምህርት ማጠቃለያ

በመንፈስ ቅዱስ መሞላት

የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምንድን ነው?

ከኤፌ 5፡18-20 በመንፈስ ቅዱስ ስላ መሞላት ምን ልንመለከት እንችላለን?

በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ማረጋገጫዎች

በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት የሚቀርቡ ቅድመ ሁኔታዎች

በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና መንፈሳዊ ብስለት

የመጀመሪያው የመንፈስ ቅዱስ ዋና ሥራ፡- ዘላለማዊው አምላክ በውስጣችን መኖሩ

የመንፈስ ቅዱስ ሁለተኛ ዋና ተግባሩ፡- ወደ ኢየሱስ ማመልከትና እርሱን እንድንመስል ማድረግ።

የመንፈስ ቅዱስ አገልግሎቶች ክለሳ

ጥያቄ፡– የሚከተሉትን ጥቅሶች ተመልከት። ዘፀኤ 31፡3፤ 36፡1፤ ዘዳ 34፡9፤ ሉቃስ 1፡5፥ 41፥ 67፥ 2፡4፤ የሐዋ. 2፡4፤ 4፡8፥ 31፤ 9፡17-20፤ 13፡9-11። ሀ) በእነዚህ ጥቅሶች በመንፈስ ቅዱስ የተሞሉ የተለያዩ ሰዎችን ጥቀስ። ለ) በመንፈስ ቅዱስ መሞላታቸውን የሚያረጋግጥ ምን ነገር አደረጉ? 

በመንፈስ ቅዱስ ስለ መሞላት በምናስብበት ጊዜ ወደ አእምሮአችን የሚመጣው ነገር የሆነ አስደናቂ ነገር ነው። ለምሳሌ በመንፈስ በመሞላትን ስናስብ ታላቅ የፍልስጥኤም ሠራዊትን ያሸነፈውን ሳምሶንን እናስባለን። ወይም ደግሞ በበዓለ ኀምሣ ቀን የታዩትን የእሳት ልሳኖችና በልሳናት መናገርን እናስባለን። ይህ የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ምን እንደሚመስል ትክክለኛውን ሥዕል የሚሰጥ ነውን? የብሉይ ኪዳንና የአዲስ ኪዳን መጻሕፍትን በአጠቃላይ ከተመለከትን በመንፈስ ቅዱስ ተሞልተው ያልተለመዱና ልዕለ-ተፈጥሮአዊ የሆኑ ነገሮች ባደረጉ ሰዎች ታሪክ የተሞላ ነው። በመንፈስ ቅዱስ የተሞሉ ነገር ግን ከተላመዱ ነገሮች ያልተለዩ ተግባራት የፈጸሙ ሌሎች ሰዎችም ነበሩ። ቀጥሎ በመጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ የተለያዩ ሰዎችን መሙላቱን የሚያሳዩ ጥቂት ምሳሌዎችን እናቀርባለን። 

ባስልኤል በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ የመገናኛውን ድንኳን የሚሠራበትን ጥበብ አገኘ (ዘፀአ 3፡3)። 

ኢያሱ በጥበብ መንፈስ በመሞላት የእግዚአብሔርን ሕዝብ ለመምራት ቶላ (ዘዳግ34፡9)። 

መጥምቁ ዮሐንስ ከመወለዱ በፊት ጀምሮ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ ነቢይ ተብሎ ተጠራ (ሉቃ. 1፡5)። 

ኤልሳቤጥና ዘካርያስ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልተው ትንቢት ተናገሩ (ሉቃ. 1፡41፤ 67)። 

ደቀ መዛሙርት በመንፈስ ቅዱስ በመሞላት በልሳኖች መናገር ቻሉ (የሐዋ. 2፡4)። 

ጴጥሮስ በመንፈስ ቅዱስ በመሞላት ለመሪዎች መናገር ቻለ የሐዋ. 4፡8)። 

ደቀ መዛሙርት በመንፈስ ቅዱስ ተሞልተው የእግዚአብሔርን ቃል በግልጥ ተናገሩ የሐዋ. 4፡3)። 

ሰባቱ ዲያቆናት በተለይ ደግሞ እስጢፋኖስ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልተው የተቸገሩትን የመርዳትና ወንጌልን የመስበክ ስጦታ ነበራቸው (የሐዋ. 6፡3)። 

እስጢፋኖስ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ በሰማይ ያለውን ኢየሱስን ተመለከተ (የሐዋ. 15)። 

ጳውሎስ በመንፈስ ቅዱስ በመሞላት ለእግዚአብሔር በድፍረት የሚመሰክር ሆነ (የሐዋ. 9፡17-20)። 

ጳውሎስ በመንፈስ ቅዱስ በመሞላት በኤልማስ ላይ የፍርድ መልእክት አስተላለፈ የሐዋ. 13፡9-10። 

በመንፈስ ቅዱስ የተሞሉ የተለያዩ ሰዎችን የሚያሳየው ይህ ዝርዝር ሰው በመንፈስ ቅዱስ በሚሞላበትና በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ቁጥጥር ሥር በሚሆንበት ወቅት የሚያደርገው አንድ የተለየ ነገር እንደሌለ በግልጽ ያመላክታል። ለአንዳንዶች ለእግዚአብሔር ክብር የሚሆን አንድ ነገርን ለመገንባት ይሆናል። ለሌሎች ሠራዊትን የመምራትና ጠላትን ድል የማድረግ፥ የመተንበይ፥ ራእይ የማየት ወይም ያለፍርሃት የመመስከር፥ ወዘተ ተግባር ይሆናል። የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ውጣዊ መግለጫ የተለያየ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን በመንፈስ ቅዱስ በተሞላ ሰው ሕይወት ውስጥ የሚፈጸመው ነገር ተመሳሳይ ነው። ከላይ የተመለከትናቸው ሰዎች በሙሉ በተፈጥሮአዊ ብርታታቸው ሊያደርጉ የማይችሉትን ነገሮች ማድረግ ችለዋል። እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በተፈጥሮአዊ ችሎታቸው ሊያደርጉት ፈጽሞ የማይችሉትን ነገር እንዲያደርጉና ለእግዚአብሔር ክብር እንዲያመጡ አድርጐአቸዋል። 

ጥያቄ፡- ኤፌ. 5፡18-21 አንብብ። ሀ) የመንፈስ ቅዱስ ሙላት የተነጻጸረው ከምን ጋር ነው? ለ) አንድ የሰከረ ሰው ሊያሳያቸው የሚችላቸውን የተለያዩ ባሕርያት ግላጽ። እነዚህ ባሕርያት በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ሥር በሆንን ጊዜ ከሚፈጸሙት ነገሮች ጋር የሚመሳሰሉት እንዴት ነው? ሐ) በዚህ ጥቅስ ላይ የሚገኘው ግሥ የተገለጸው በምን ጊዜ ነው? ስለ አንድ ጭብጥ ነው የሚገልጸው? ጥያቄ ነው የሚጠይቀው? ወይስ ትእዛዝ ነው የሚሰጠው? መ) ጳውሎስ የመንፈስ ቅዱስ ሙላት የሚረጋገጥባቸው መንገዶች ምን ምን ናቸው አለ? 

መንፈስ ቅዱስ በሰው ሕይወት ውስጥ የሚያደርገውን ይህን ተደጋጋሚ ልምምድ ከሁሉ በላቀ ሁኔታ ለመግለጽ አገልግሎት ላይ የዋለው ቃል «የመንፈስ ቅዱስ ሙላት» የሚለው ይሆናል። የእውነተኛ መንፈሳዊነት ሁሉ ምክንያት መንፈስ ቅዱስ ነው። በሕይወታችን የመሥራት፥ ክርስቶስን እንመስል ዘንድ የመለወጥ፥ የክርስቶስን ህልውና በሕይወታችን የመለማመቶችን ብቻ ሳይሆን በተግባራችንም እንደንመስለው ማድረግ የእርሱ ኃላፊነት ነው። ይህ ተግባር እንዳንድ ጊዜ በአስደናቂ ውጫዊ ሁኔታ ሊገለጽ ይችላል። ነገር ግን ብዙ ጊዜ እስደናቂ ስማይመስል፥ ነገር ግን በፍቅር፥ በደስታ፥ በሰላምና በተስፋ በተሞላ ሕይወት መኖር ነው። 

ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ስለሚኖረን ኅብረት በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኙ ግልጽ ትእዛዛት ጥቂት ናቸው። በመንፈስ ቅዱስ እንድንጠመቅ ፈጽሞ አልታዘዝንም። በመንፈስ ቅዱስ እንድንቀባም የተሰጠ ትእዛዝ የላም። ከሁሉ የሚበልጡትን ጠቃሚ መንፈሳዊ ስጦታዎች እንድንፈልግ የተነገረን ቢሆንም እንኳ የመንፈሳዊ ስጦታዎችን ህልውና እንድንፈልግ አልታዘዝንም። ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ስላለን ኅብረት የሚገልጹ እነዚህ ነገሮች በሙሉ ከክርስቲያኖች ሁሉ ጋር አብረው ያሉ ናቸው። ወደ መንፈስ ቅዱስ ሙላት ስንመጣ ግን «መንፈስ ቅዱስ እንዲሞላብን») ታዝዘናል (ኤፌ. 5፡18)። መንፈስ ቅዱስን እንዳናሳዝን (ኤፌ. 4፡30)፥ የመንፈስ ቅዱስን እሳት እንዳናጻፍን (1ኛ ተሰ. 5፡19)፥ እና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር እንድንራመድ (ገላ. 5፡5) ታዝዘናል። 

በኤፌ. 5፡18 በመንፈስ ቅዱስ «እንሞላ » ዘንድ እግዚአብሔር ያዝዘናል። በመንፈስ ቅዱስ መሞላት ማለት ምን ማለት እንደሆነ መረዳት እንድንችል በቁጥጥር ሥር ከሚያደርግ ሌላ ዓይነት ነገር ማለትም ከስካር ጋር ማነጻጸር አለብን። በአንድ በኩል በእነዚህ ሁለት ዓይነት መሞላቶች መካከል ከፍተኛ ልዩነቶች አሉ። አንድ ሰው በወይን በተሞላ ጊዜ ራሱን ስለማይቆጣጠር ምን እንደሚያደርግ እንኳ አያውቅም። ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ አንድን ሰው በሚቆጣጠርበት ጊዜ ስለሚፈጸመው ነገር የተሞላው ሰው በሚገባ ያውቃል። 

እእምሮአቸውን ይቆጣጠራሉ። በተጨማሪ መንፈስ ቅዱስ በአስደናቂ መንገድ በኃይል እየተጠቀመባቸው እንዳለም ያውቃሉ። 

ስለዚህ በወይን በመስከርና በመንፈስ ቅዱስ በመሞላት መካከል ያለው ተመሳሳይነት ምንድን ነው? 

1. በወይን ጠጅ የተሞላ ሰው መጠጡ ስለሚቆጣጠረው ከመጠጣቱ በፊት ሊያደርገው የማይችለውን ነገር ማድረግ ይችላል። በተመሳሳይ መንገድ በመንፈስ ቅዱስ መሞላት ማለት በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ሥር መሆንና ተለማምደውት የማያውቁትን ሕይወት መኖር ማለት ነው። ለምሳሌ የሰውዩው ባሕርይ ከቁጣ ወደ ፍቅር ይለወጣል፤ ከላስታምነት ሌሎችን ወደ ማገልገል ይቀየራል። 

2. የመጠጥ ሱሰኛ የሆነ ሰው የሚያጋጥመውን ችግር ለመጋፈጥና ብርታት ለማግኘት በመጠጡ ላይ ይደገፋል። በተመሳሳይ መንገድ በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ሥር የሚኖር ሰው እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ኑር ለመኖር ኃይል ይሆነው ዘንድ ፊቱን ወደ እግዚአብሔር ይመልሳል።

ምንጭ፡- “የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ”፣ በቲም ፌሎስ ተጽፎ፣ በጌቱ ግዛው የተተረጎመ እና በኤስ አይ ኤም ጽሑፍ ክፍል የተዘጋጀ ነው፡፡ ለዚህ ድንቅ አገልግሎታቸው እግዚአብሔር ይባርካቸው፡፡ ይህን ጽሁፍ ኮፒ እና ፕሪንት አድርጎ መጠቀም ይቻላል፤ ሆኖም ጽሁፉን መለወጥና ለሽያጭ ማዋል በሕግ የተከለከለ ነው፡፡

የመንፈስ ቅዱስ የጥናት መምሪያና ማብራሪያ

በመንፈስ ቅዱስ መሞላት ከኤፌ 5፡18-20 በመንፈስ ቅዱስ ስላ መሞላት ምን ልንመለከት እንችላለን?
Exit mobile version