Site icon የሕይወት እንጀራ

ቅዱስ ቁርባንን መቀበል፥ ደኅንነት ያስገኛል? 

This entry is part 92 of 95 in the series አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

አስተምህሮ ምንድን ነው? 

የክርስቶስ አስተምህሮ አስፈላጊነትና ድነት (ደኅንነት) 

የክርስቶስ መለኮታዊነት 

ኢየሱስ ሁሉን ቻይ እና ሁሉን የሚገዛ ነው

ኢየሱስ ሁሉን አዋቂ ነው 

ኢየሱስ በሁሉም ቦታ ይገኛል 

የኢየሱስ ባሕርይ አይለዋወጥም 

ኢየሱስ ሕይወትን ይሰጣል 

ኢየሱስ ተሰግዶለታል

ኢየሱስ አምላክ መሆኑን ገልጾአል ፤ ኢየሱስ ይቅርታን መስጠት ይችላል 

ኢየሱስ በእግዚአብሔር ቃል ላይ ሥልጣን አለው 

ኢየሱስ ከእግዚአብሔር ጋር አንድ ዓይነት ባሕርይ እንዳለው ገለጸ 

ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ተቀብሏል 

የክርስቶስ አምላክነት በቆላስይስ 1፡15-20 

የኢየሱስ ክርስቶስ ሰብአዊነት 

ኢየሱስ ፍጹም ሰው መሆኑን እንዴት እናውቃለን? 

የኢየሱስ ሰብአዊ ስሜቶች 

ኃጢአት አልባው የኢየሱስ ሰብአዊነት 

የኢየሱስ ከድንግል መወለድ 

ተሠገዎ በዮሐንስ 1 

ስለ ተሠገዎ በፊልጵስዩስ ምዕራፍ 2 

ስለ ተሠገዎ በዕብራውያን ምዕራፍ 2 

በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን የተሠገዎ ታሪክ፣ ኢቢዮናውያን 

በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን የተሠገዎ ታሪክ፣ ኖስቲካዊነት

በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን የተሠገዎ ታሪክ፣ ሞናርካዊነት ወይም ስባልዮሳዊነት 

በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን የተሠገዎ ታሪክ፣ አርዮሳዊነት 

ተሠገዎ፥ ክፍል 2 

ክርስቶስ «አንድ ባሕርይ» አለው የሚለው አስተምህሮ በኢትዮጵያ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ስለ ክርስቶስ ተሠገዎ ያላት ምሥጢረ እምነት

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን ስለ ክርስቶስ ባሕርይና አካል ያላቸው እምነት

ክርስቶስ በብሉይ ኪዳን ውስጥ የተገለጠባቸው መልኮችና ምሳሌዎች

በብሉይ ኪዳን ውስጥ የያህዌ መልአክ (ቅድመ- ተሠገዎ የክርስቶስ መገለጥ)

ክርስቶስ በብሉይ ኪዳን ዘመን ሲገለጥ (ቅድመ-ተሠገዎ)

በብሉይ ኪዳን የክርስቶስ ተምሳሌቶች

የሚመጣው መሢሕ ትንቢቶችና ተስፋዎች 

የሚመጣው መሢሕ ትንቢቶችና ተስፋዎች 

የሚመጣው መሢሕ ትንቢቶችና ተስፋዎች 

መሢሑ ኢየሱስ

መሢሑ እንደ ንጉሥ 

መሢሑ እንደ ካህን 

መሢሑ እንደ ነቢይ 

መሢሑ እንደ መድኅን 

ኢየሱስ የሰው ልጅ 

ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ስለ መሆኑ በብሉይና በወንጌላት ውስጥ 

የእግዚአብሔር ልጅ መለኮታዊ ነው። 

በጳውሎስና በዮሐንስ መጻሕፍት ውስጥ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ መገለጹ 

ኢየሱስ እንደ ጌታ 

የክርስቶስ መቀባት

ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ምሳሌያችን 

ኢየሱስ እና የእግዚአብሔር መንግሥት

የኢየሱስ ሞት 

የክርስቶስ ከፍ ከፍ ማለት (ዕርገት)

የኢየሱስ ዕርገት (ከፍ ከፍ ማለት) 

ኢየሱስ አሁን ያለው ባሕሪና አገልግሎቱ

ክርስቶስ እንደ መካከለኛና እንደ አማላጅ 

የደኅንነት አስፈላጊነት- ሰዎች ኃጢአተኛ በሆነ ባሕርይ ተወለዱ ማለት ምን ማለት ነው?

ኃጢአት ከየት መጣ? 

የኃጢአት ውጤት፡- ሞት 

ሁላችንም ከአዳም ኃጢአት በደልን ወርሰናል

ሁሉም ሰው የኃጢአት ተግባርን ፈጽሟል 

ኃጢአት በክርስቲያን ሕይወት ውስጥ 

ሕፃናት በእርግጥ ኃጢአትን ለመሥራት ከደረሱበት ጊዜ በፊት የኃጢአት በደለኞች ይባላሉ? 

አንዳንዱ ኃጢአት ከሌላው የባሰ ነውን? 

ይቅርታ የማይደረግበት ኃጢአት ምንድን ነው? 

የደኅንነት ትርጉም፡- ከኃጢአትና ከኃጢአት ውጤቶች ሁሉ መዳን 

የእግዚአብሔር ቅዱስነት የኃጢአትን መሥዋዕት ይሻል፡- የብሉይ ኪዳን ምሳሌ 

ኢየሱስ ለኃጢአት ፍጹም የሆነ መሥዋዕት ሆነ፦ የአዲስ ኪዳን መፈጸም

የኢየሱስ ሞት የእግዚአብሔርን ቅዱስ ቁጣ ለማርካት (ለማብረድ) የቀረበ መሥዋዕት ነው። 

ኢየሱስ ከእግዚአብሔር ጋር አስታረቀን 

ኢየሱስ የራሱ ሰዎች እንድንሆን ከኃጢአት ዋጀን

የኢየሱስ ሞት በሰይጣን ላይ ታላቅ ድልን አስገኝቷል- ክፍል አንድ 

ኢየሱስ በሞቱ በሰይጣን ላይ ታላቅ ድልን ተቀዳጅቷል – ክፍል ሁለት 

ወደ ደኅንነት መድረሻው መንገድ – የእግዚአብሔር ምርጫና የእግዚአብሔር ጥሪ 

እግዚአብሔር ለጥቂቶች ምሕረቱን ሊሰጥ ይመርጣል 

እግዚአብሔር በሉዓላዊነቱ የመረጣቸውን አበክሮ ይጠራቸዋል። 

ስለ እግዚአብሔር ምርጫና ለደኅንነት ስለሚያደርገው ጥሪ ጥያቄዎች 

የመዳኛ መንገድ፡- ንስሐ እምነትና ወደ እግዚአብሔር መመለስ 

ወደ እግዚአብሔር መመለስ ወይም «መለወጥ» 

እምነት ከታዛዥነት ጋር እንዴት ይዛመዳል? 

ዳግም መወለድ፥ ክፍል 1 

ዳግም መወለድ፥ ክፍል 2 

ከክርስቶስ ጋር መተባበር – ከክርስቶስ ጋር የመተባበር በረከቶች ምንድን ናቸው? 

ከክርስቶስ ጋር መተባበር – ከክርስቶስ ጋር መተባበር ማለት ምን ማለት ነው? 

ጽድቅና ይቅርታ፥ ክፍል አንድ 

ጉዲፈቻ (የማደጎ ልጅ) 

ቅድስና 

የደኅንነት በረከቶች – እንከብራለን ሲባል ምን ማለት ነው?  

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫ እና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 1 

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 2 

የዘላለማዊ ዋስትና ማረጋገጫና የእግዚአብሔር ቅዱሳን ጽናት፥ ክፍል 3 

ደኅንነትን የመቀበል ጥያቄ፣ እምነትና ጥምቀት  

ቅዱስ ቁርባንን መቀበል፥ ደኅንነት ያስገኛል? 

የሚሞቱ ሕፃናት ይድናሉ? 

ለመሆኑ በመጨረሻው ሰዎች ሁሉ ይድናሉ ወይ? 

ሰዎች የክርስቶስን መልእክት ሳይሰሙ ሊድኑ ይችላሉ? 

ጥያቄ፡- ዮሐ 6፡53-54 እንብብ። ሀ) ጌታ ኢየሱስ፥ አንድ ሰው ሕይወትን ማግኘት ከፈለገ ምን ያድርግ ይላል? ለ) ጌታ ኢየሱስ አንድ ሰው ሥጋውን ቢበላና ደሙን ቢጠጣ ምንን ያገኛል አለ? 

ጥያቄ ዮሐ. 6፡35 አንብብ። ጌታ ኢየሱስ አንድ ሰው እንዳይራብ ወይም እንዳይጠማ ምን ያድር አለ? 

ብዙ ሰዎች የእግዚአብሔርን ጸጋ ተቀብለው ለመዳን ሲሉ ቅዱስ ቁርባንን መቀበል ይፈልጋሉ። ሌሎች ደግሞ ካልቀረቡ በስተቀር ሊድኑ እንደማይችሉ ይሰማቸዋል። የተቀሩት ሰዎች ደግሞ፥ የቅዱስ ቁርባን ተካፋዮች በመሆን የእግዚአብሔርን ጸጋ በመቀበል መዳናቸውን እንደሚያረጋግጡ ያምናሉ። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ እነዚህ ሰዎች በቅዱስ ቁርባን ላይ መሳተፍ በዮሐንስ 6፡53-54 ውስጥ እንደተጻፈው የእግዚአብሔርን የማዳን ጸጋ የሚያሰጣቸው መሆኑን ለአሳባቸው ድጋፍ አድርገው ያቀርባሉ፡ በዚህ ክፍል ኢየሱስ የሚናገረው፥ ሰዎች «ሥጋውን በልተው፥ ደሙን የሚጠጡት» ሕይወትን ለማግኘት ስለሆነ፥ ማንም ሰው ሥጋውን የሚበላና ደሙን የሚጠጣ ሁሉ የዘላለም ሕይወትን ያገኛል። ለአንዳንድ ሰዎች ጌታ ኢየሱስ ስለ ቅዱስ ቁርባን የተናገረ ይመስላቸዋል። በመጀመሪያ ጊዜ፥ ኢየሱስ ቅዱስ ቁርባንን ለደቀ መዛሙርቱ በሰጠ ጊዜ፥ «ይህ ለእናንተ የሚሰጥ ሥጋዬ ነው። ይህ ጽዋ ስለ እናንተ በሚፈሰው ደሜ የሚፈጸም አዲስ ኪዳን ነው» አላለምን? (1ኛ ቆሮንቶስ 11፡24-25። እነዚህ ሰዎች በቅዱስ ቁርባን ጊዜ ኅብስቱን መብላትና ከጽዋው መጠጣት የዘላለምን ሕይወት የሚሰጣቸው አድርጎ ኢየሱስ የተናገረ አድርገው ያምናሉ። 

ሆኖም፤ ደቀ መዛሙርቱ ሥጋውን እንዲበሉና ደሙንም እንዲጠጡ ኢየሱስ ሲነግራቸው ምን ማለቱ እንደሆነ በጣም የተሻለ ማብራሪያ አለ። በዮሐንስ 6፡53-54 ውስጥ ኢየሱስ ስለ ኅብስት ከአይሁዶች ጋር ያደረገው ረጅም ውይይት ከፊሉ ይገኛል። የመጽሐፍ ቅዱስን አንድ ክፍለ ምንባብ ትርጉም የመተንተን የመጀመሪያውና እጅግ በጣም ጠቃሚ የሆነው መመሪያ፥ የክፍለ ምንባቡን ጭብጥና ይዘት ማጥናት ነው። ኢየሱስ በዮሐንስ 6፡52-53 ውስጥ ስለተናገረው ጥቅል ትርጉም ለመተንተን የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 6 መላውን ክፍል ማጥናት ይገባናል። በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 6 በመጀመሪያዎቹ ጥቅሶች ላይ ኢየሱስ አምስት እንጀራና ሁለት ዓሣዎችን ለአምስት ሺህ ሰዎች እንደ መገበ እንነዘባለን። ከዚህ በኋላ ኢየሱስ ሕዝቡን ተለይቶ ሄደ። ወዲያው ቀን አገኙት (ዮሐንስ 6፡25)። ሕዝቡ ኢየሱስን ባገኙት ጊዜ፥ እንጀራ ስላበላቸው የፈለጉት መሆናቸውን ነገራቸው። ቀጥሎም፥ ለሚጠፋ ምግብ አትሥሩ፥ የዘላለም ለሚሆን ምግብ ሥሩ አላቸው (ዮሐንስ 26፡27)። ነገር ግን አይሁዶቹ በሥጋዊ ምግብ ፍላጎት ስላየለባቸው፥ ኢየሱስ እነርሱን ለመመገብ ሌላ ተአምር እንዲፈጽም ጠየቁት (ዮሐ 6፡31-32)። ከዘላለም ሕይወት ይልቅ ምግብን አስበልጠው ስላዩ፥ እርሱ ከሰጣቸው ሥጋዊ ምግብ ይልቅ እርሱን እንዲች አሳሰባቸው። እውነተኛ የእግዚአብሔር እንጀራ ከሰማይ የመጣው መሆኑን ነገራቸው (ዮሐ. 6፡33)። ሰዎቹ ግን አሁንም ኢየሱስ ስለ ዓለማዊ እንጀራ የሚናገር መሰላቸው። ይህን እንጀራ እንዲሰጣቸው ጠየቁት (ዮሐ 6፡34)። በጣም ጠቃሚ በሆነ ጥቅስ አማካይነት ኢየሱስ ስለሚናገረው በትክክል ያስገነዝባቸዋል። በዮሐንስ 6፡35 ውስጥ ኢየሱስ ራሱ ከሰማይ የመጣ እንጀራ መሆኑንና ወደ እርሱ የሚመጣ ጨርሶ እንደማይራብ፥ የሚያምንበትም የማይጠማ መሆኑን ይነግራቸዋል። ኢየሱስ የመንፈስን ምግብና መጠጥ የማግኘቱ መንገድ ወደ እርሱ ዘንድ መምጣትና በእርሱ ማመን መሆኑን በማስረዳት፥ ወደ እርሱ ዘንድ ቢመጡ እርሱ ከሰማይ የመጣ እንጀራ ስለሆነ በፍጹም የማይራቡና በመንፈስም የማይጠሙ መሆናቸውን አስገንዝቦአቸዋል። ኢየሱስ ከሰማይ ስለ መምጣቱ በተናገረ ጊዜ አይሁዶች አጉረመረሙ (ቁጥር 41-42)። ምክንያቱም እርሱ የተናገረው ቃል አልገባቸውም ነበር። ኢየሱስ በመመገብ ሥጋዊ ፍላጎታቸውን የፈጸመላቸው፥ መንፈሳዊ ትምህርትን ሊያስተምራቸው እንደነበረ አልገባቸውም ነበር። ኢየሱስም አያይዞ፥ ሰዎች ሊመጡበት የሚገባ ከሰማይ የመጣ እንጀራ መሆኑን ስለ ራሱ ተናገረ (ዮሐ 6፡50-51)። ሰዎች ሥጋውን እንዲበሉና ደሙን እንዲጠጡ ሲናገራቸው (ዮሐ 6፡53-54)፥ በቁጥር 32 ውስጥ በተናገረው ስልት ዓይነት ነበር አሳቡን የገለጸው። ኢየሱስ ሊናገር የፈለገውን የአነጋገር ስልትና ምሥጢር ቁጥር 35 ውስጥ ትርጉሙን አብራርቶታል። ሥጋውን መብላትና ደሙን የመጠጣት ምሥጢር ወደ ኢየሱስ የመምጣትና በእርሱ የማመን ምሥጢር ነው። ኢየሱስ ለአይሁዶች ሲናገር፥ የዘላለም ሕይወትን ለማግኘት ቢሹ ወደ እርሱ ዘንድ መጥተው በእርሱ ማመን እንዳለባቸው አሳስቦአቸዋል። 

ቅዱስ ቁርባን በእያንዳንዱ ክርስቲያን ሕይወት ውስጥ እጅግ በጣም ጠቃሚ የሆነ ሥነ ሥርዓት ነው። ቅዱስ የሆነ የአምልኮ ጊዜ ነው። በዚህን ጊዜ አማኙ ኃጢአቱን ይናዘዛል፥ የክርስቶስን ሞት ያስባል፥ ከእግዚአብሔርና ከሌሎች ምእመናን ጋር ይገናኛል። ደግሞም ኢየሱስ ደኅነትን ሊሰጠው ስለ ፈጸመው ሁሉ ምሥጋና ያቀርባል፥ እርሱንም ያመልካል። ሆኖም ቅዱስ ቁርባንን መቀበል ማንንም ሊያድን ወይም የዘላለም ሕይወትን ሊሰጥ አይችልም። የዘላለምን ሕይወት የምናገኘው፥ ወደ ኢየሱስ ዘንድ በእምነት በመምጣት ነው። ይህንንም ራሱ በዮሐንስ 6፡35 ውስጥ ተናግሮአል።

ምንጭ፡- “አስተምህሮ ክርስቶስና ደኅንነት”፤ ጽሑፍ፣ በዶ/ር ስቲቭ ስራውስ፤ ትርጉም በኃይሉ ልመንህ

አስተምህሮ ክርስቶስ እና ደኅንነት

ደኅንነትን የመቀበል ጥያቄ፣ እምነትና ጥምቀት   የሚሞቱ ሕፃናት ይድናሉ? 
Exit mobile version