ሀ) መጽሐፍ ቅዱስ ስለ እግዚአብሔር ያስተምረናል
የእግዚአብሔር ቃል እምነት ሊጣልበት የሚችል መሆኑ – ሉቃስ 21፡33
የእግዚአብሔርና የቃሉ ስልጣን – ማቴ 4፡4፤ ዮሐ 10፡35
መጽሐፍ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ የተደረሰ መጽሐፍ ነው – 2ጢሞ 3፡16
መጽሐፍ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ ምሪት የተጻፈ ነው – 2ጴጥ 1፡21
ለ) መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔርን ለእኛ ለመግለጽ ሰዋዊ የሆኑ መግለጫዎችን ይጠቀማል
ክንድና እጅ – ዘጸ 3፡20፤ ዘዳ 4፡34፤ ዘጸ 5፡15
ፊት – ዘፍ 4፡14፤ 33፡10፤ ኢሳ 59፡2
አይኖችና ጆሮዎች – ኢሳ 37፡17፤ መዝ 11፡4፤ 34፡15፤ መሳ 15፡3፤ ዘካ 4፡10
መሄድና መምጣት – ዘፍ 11፡5፤ ኢሳ 64፡1-3፤ መዝ 18፡9-19
የእግዚአብሔር ድምጽ ለአዳምና ለሙሴ ተሰማ – ዘፍ 3፡9፣ 10፤ ዘዳ 4፡12
የእግዚአብሔርን ድምጽ መስማት እንችላለን – ዘዳ 5፡24፤ ሐዋ 22፡14
ሐ) እግዚአብሔር፣ ሰዎች ሊረዱት በሚችሉት መንገድ ይገለጣል
በራዕይ – ዳን 7፡9፣ 13፤ ራዕ 4፡3፤ 5፡7
በቀጥታ – አዳም – ዘፍ 3፡8-10 – ያዕቆብ – ዘፍ 32፡24-30 – አብርሃም – ዘፍ 18 ኢያሱ – ኢያሱ 5፡13-15 – ዳንኤል – ዳን 3፡ 25
እግዚአብሔር በኢየሱ በኩል – ማቴ፣ ማር፣ ሉቃ እና ዮሐ
መ) የፈጠራቸውን ነገሮች በመመልከት (ተፈጥሮን)
በ (ሮሜ 1፡18-25) የተጠቀሰውን ትምህርት ይመልከቱ።
ሰማያት የእግዚአብሔር ክብር ይናገራሉ – መዝ 19፡1
ተፈጥሮ የእርሱን ዘላለማዊ ሃይልና መለኮትነት ያበስራል – ሮሜ 1፡20
ህሊናችንና/ልባችን የእግዚአብሔርን ሕግ ያውቃል – ሮሜ 2፡14-16
የምድር በረከት ምስክር ነው – ሐዋ 14፡15-17
የእግዚአብሔር እውቀትና ጥበብ – መዝ 19፡1-6፤ 104
የእግዚአብሔር ሃይልና ግርማ ሞገስ – መዝ 18፡7-15፤ 29፤ 66፡1-7
ሠ) እግዚአብሔርን በተፈጥሮ ውስጥ ብቻ የማወቅ ጎዶሎ ጎኖች
ተፈጥሮ ሙሉዉን ድነት ለመረዳት በቂ አይደለም።
የማያምኑ ሰዎች አእምሮ በሰይጣን ታውሯል – 2ቆላ 4፡4
ሰባኪ ያስፈልጋል – ሮሜ 10፡14
የአዳም መውደቅ በተፈጥሮ ውስጥ የነበረውን የእግዚአብሔር ምስል በክሎታል። ለአብነት – በምጥ ጊዜ ያለ ህመም – ዘፍ 3፡16፤ አድካሚ ስራ፤ እሾህና አሜኬላ – ዘፍ 3፡17-18፤ ፍጥረት ሁሉ ለመታደስ በመጠባበቅ ላይ ይገኛል – ሮሜ 8፡18-25
ረ) እግዚአብሔር በክርስቶስ ኢየሱስ በሙላት ተገልጧል
ወልድ ለሚወደው ሁሉ አብን ይገልጥለታል – ማቴ 11፡27፤ ሉቃስ 10፡22
እኔን ያየ አብን አየ – ዮሐ 14፡6-7፤ 10፡30
ቃልም እግዚአብሔር ነበረ…ቃልም ሥጋ ሆነ – ዮሐ 1፡1-14
ሰ) እግዚአብሔር መንፈስ ነው (ዮሐ 4፡24)
ስለዚህ እራሱን ሊገልጥልን ይገባል – 1ሳሙ 3፡21
አንዳንድ ነገሮች ምስጢር እንደሆኑ ይቆያሉ – ዘዳ 29፡29
አንዳንድ ነገሮችን ለሰው ልጅ ይገልጻል – ዓሞጽ 3፡7፤ ኤፌ 3፡5
ሙሴ የእግዚአብሔርን ድምጽ ሰማ ነገር ግን እግዚአብሔርን አልተመለከተውም – ዘጸ 4፡12
ሰው እግዚአብሔርን አይቶ በሕይወት መቆየት አይችልም – ዘጸ 33፡20
ማስታወሻ፡- እግዚአብሔር መንፈስ ስለሆነ ራሱን ሊገልጥልን ይገባል፡፡
ሸ) እግዚአብሔር ለሰዎች ራሱን ለምን ይገልጣል?
በመከራ ጊዜያቸው ወቅት ሊያድናቸው – 2ሳሙ 22፡7፤ መዝ18፡6
ኖሕ ከጥፋት ውሃ ዳነ – ዘፍ 6፡1 – 9፡17
አብርሃም ከ ጣኦት አምልኮ ዳነ – ዘፍ 12፡1 – 22፡19
ሙሴ ከባርነት ነጻ ለመውጣት – ዘጸ 3፡-14፡
ድነትን ለመስጠት – ማቴ 1፡21
የሰይጣንን ስራ ለማፍረስ – 1ዮሐ 3፡8
ስለመጻኢ ጊዚያት ለማስጠንቀቅ – ዓሞጽ 3፡7፤ ራዕ 1፡-22