የሕይወት እንጀራ

የሉቃስ ወንጌል አወቃቀር እና አስተዋጽኦ

፩. የሉቃስ መጽሐፍ አወቃቀር

የሉቃስ ወንጌል በአራት ዐበይት ክፍሎች ይከፈላል።

ሀ. የኢየሱስ ልደትና የልጅነት ጊዜ (ሉቃስ 1-2)

ለ. የኢየሱስ አገልግሎት በገሊላ (ሉቃስ 3፡1-9፡50)

ሐ. የኢየሱስ አገልግሎት ወደ ኢየሩሳሌም ሲሄድ (ሉቃስ 9፡51–19፡27)

መ. የኢየሱስ አገልግሎት በኢየሩሳሌም (ሉቃስ 19፡28-24፡53)

፪. የሉቃስ መጽሐፍ አስተዋጽኦ

1. የሉቃስ ወንጌል መግቢያ (ሉቃስ 1፡1-4)

2. ኢየሱስ በምድር ላይ ላለው አገልግሎት ያደረገው ዝግጅት (ሉቃስ 1፡5-4፡13)

ሀ. የመጥምቁ ዮሐንስና የኢየሱስ መወለድና የልጅነት ጊዜ (ሉቃስ 1፡5-2፡52)

ለ. የመጥምቁ ዮሐንስ አገልግሎት (ሉቃስ 3፡1-20)

ሐ. የኢየሱስ መጠመቅና በመንፈስ ቅዱስ መሞላት (ሉቃስ 3፡21–4፡13)

3. የኢየሱስ አገልግሎት በገሊላ (ሉቃስ 4፡14-9፡9)

ሀ. ኢየሱስ መልካሙን የምሥራች ዐወጀ (ሉቃስ 4፡14–5፡16)

ለ. ኢየሱስ ከሃይማኖት መሪዎች ጋር ተጋጨ (ሉቃስ 5፡17-6፡11)

ሒ ኢየሱስ ለድሆች መልካሙን የምሥራች ዐወጀ (ሉቃስ 6፡12-8፡3)

መ. ኢየሱስ መሢሕ መሆኑን ገለጠ (ሉቃስ 8፡4-9፡50)

4. ኢየሱስ ወደ ኢየሩሳሌም ሄደ (ሉቃስ 9፡51-19፡28)

ሀ. ኢየሱስ በይሁዳ አገለገለ (ሉቃስ 9፡51-13፡21)

ለ ኢየሱስ በጲሪያና አካባቢዋ አገለገለ (ሉቃስ 13፡22-19፡27)

5. የኢየሱስ የመጨረሻው አገልግሎት በኢየሩሳሌም (ሉቃስ 19፡28-24፡53)

ሀ. የኢየሱስ አገልግሎት ከስቅለቱ በፊት (ሉቃስ 19፡28–22፡46)

ሊ የኢየሱስ መያዝ፣ መመርመርና መሰቀል (ሉቃስ 22፡47-23፡56)

ሐ. የኢየሱስ ትንሣኤና ዕርገት (ሉቃስ 24)

የጌታ ጸጋ ከእርስዎ ጋር ይሁን፤ ሀሳብዎን ለመስማት ዝግጁ ነን።

Discover more from የሕይወት እንጀራ

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading