፩. የሉቃስ መጽሐፍ አወቃቀር
የሉቃስ ወንጌል በአራት ዐበይት ክፍሎች ይከፈላል።
ሀ. የኢየሱስ ልደትና የልጅነት ጊዜ (ሉቃስ 1-2)
ለ. የኢየሱስ አገልግሎት በገሊላ (ሉቃስ 3፡1-9፡50)
ሐ. የኢየሱስ አገልግሎት ወደ ኢየሩሳሌም ሲሄድ (ሉቃስ 9፡51–19፡27)
መ. የኢየሱስ አገልግሎት በኢየሩሳሌም (ሉቃስ 19፡28-24፡53)
፪. የሉቃስ መጽሐፍ አስተዋጽኦ
1. የሉቃስ ወንጌል መግቢያ (ሉቃስ 1፡1-4)
2. ኢየሱስ በምድር ላይ ላለው አገልግሎት ያደረገው ዝግጅት (ሉቃስ 1፡5-4፡13)
ሀ. የመጥምቁ ዮሐንስና የኢየሱስ መወለድና የልጅነት ጊዜ (ሉቃስ 1፡5-2፡52)
ለ. የመጥምቁ ዮሐንስ አገልግሎት (ሉቃስ 3፡1-20)
ሐ. የኢየሱስ መጠመቅና በመንፈስ ቅዱስ መሞላት (ሉቃስ 3፡21–4፡13)
3. የኢየሱስ አገልግሎት በገሊላ (ሉቃስ 4፡14-9፡9)
ሀ. ኢየሱስ መልካሙን የምሥራች ዐወጀ (ሉቃስ 4፡14–5፡16)
ለ. ኢየሱስ ከሃይማኖት መሪዎች ጋር ተጋጨ (ሉቃስ 5፡17-6፡11)
ሒ ኢየሱስ ለድሆች መልካሙን የምሥራች ዐወጀ (ሉቃስ 6፡12-8፡3)
መ. ኢየሱስ መሢሕ መሆኑን ገለጠ (ሉቃስ 8፡4-9፡50)
4. ኢየሱስ ወደ ኢየሩሳሌም ሄደ (ሉቃስ 9፡51-19፡28)
ሀ. ኢየሱስ በይሁዳ አገለገለ (ሉቃስ 9፡51-13፡21)
ለ ኢየሱስ በጲሪያና አካባቢዋ አገለገለ (ሉቃስ 13፡22-19፡27)
5. የኢየሱስ የመጨረሻው አገልግሎት በኢየሩሳሌም (ሉቃስ 19፡28-24፡53)
ሀ. የኢየሱስ አገልግሎት ከስቅለቱ በፊት (ሉቃስ 19፡28–22፡46)
ሊ የኢየሱስ መያዝ፣ መመርመርና መሰቀል (ሉቃስ 22፡47-23፡56)
ሐ. የኢየሱስ ትንሣኤና ዕርገት (ሉቃስ 24)