ሀ. በክርስቶስ መስቀል አማካይነት በሰይጣን ላይ የተሰጠ ፍርድ
በሰይጣንና በእግዚአብሔር መካከል ግጭት የተፈጠረው፥ አዳምና ሔዋን ከመፈጠራቸው ረዥም ጊዜ በፊት ሰይጣን መጀመሪያ ከነበረበት ቅዱስ ስፍራ በወደቀ ጊዜ ነበር (የዚህን መጽሐፍ ምዕራፍ 22 ይመልከቱ)። በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ፥ በሰይጣን ላይ የተለያዩ ፍርዶች ተሰጥተዋል። ከነዚህም አንዱ በኤደን ገነት ውስጥ በእባቢቱ ላይ የተሰጠው ፍርድ ሲሆን፥ የሚያመላክተው በሰይጣን ላይ የሚደርሰውን (የሚመጣውን) የመጨረሻ ውድቀት ነው (ዘፍጥ. 3፡15)። በዚያ ስፍራ የሴቲቱ ዘር የሰይጣንን ራስ እንደሚቀጠቅጥና ሰይጣንም የርሱን ተረከዝ እንደሚቀጠቅጥ ተገልጧል። ይህም የክርስቶስን መስቀል ያስከተለውንና በእግዚአብሔርና በሰይጣን መካከል የነበረውን ግጭት ያመለክታል። ክርስቶስ በመስቀል ላይ ቢሞትም ከሞት ተነሥቷል። ይህም “ዕኮናውን ትቀጠቅጣለህ” የሚለውን ቃል ያመለክታል። በአንጻሩ ግን ሰይጣን ፍጹም መሸነፉን የሚያመለክት ከፍተኛ ቁስል ደርሶበታል። ያም “ራስህን ይቀጠቅጣል” የተባለው ነው። ክርስቶስ በሞቱ በሰይጣን ላይ ዘላቂ ድል ተቀዳጅቷል።
ይህ እውነት ክርስቶስ መንፈስ ቅዱስ በመጣ ጊዜ፡- “ስለ ፍርድም የዚህ ዓለም ገዢ ስለተፈረደበት ነው” ባለበት ዮሐንስ 16፡11 ውስጥ ተመልክቷል። ሰይጣን በእግዚአብሔር ላይ በማመፁ በመስቀል ላይ ተፈርዶበታል። በሞት ፍርድ ሥር የነበረውን የሰው ዘር ለማዳን ሲባልም የክርስቶስ ሞት አስፈላጊ ሆነ።
ቀደም ሲል በክርስቶስ ሕይወት የታየ ሌላ ክሥተትም ክርስቶስ ሰይጣንን ያሸነፈው መሆኑን አመልክቷል። ወንጌሉን ለመስበክና ተአምራት ላማድረግ የተላኩት ሰባ ሰዎች ተመልሰው፥ “ጌታ ሆይ፥ አጋንንት እንኳ በስምህ ተገዝተውልናል” አሉ (ሉቃስ 10፡17)። ክርስቶስም ሲመልስሳቸው “ሰይጣንን እንደ መብረቅ ከሰማይ ሲወድቅ አየሁ። ብሏል (ቁ. 18)። ይህ የሰይጣንን የመጨረሻ ውድቀት የሚያመላክት ትንቢታዊ ገላጣ ነበር።
ለ. የሰይጣን ከሰማይ መጣል
ከክርስቶስ ዳግም ምጽአት አርባ ሁለት ወራት ቀደም ብሎ በሺህ ዓመቱ መንግሥት መጀመሪያ አካባቢ፥ የቅዱሳን መላእክት አለቃ በሆነው ሚካኤልና ሰይጣን (“ዘንዶው” ተብሎ የተገለጠው) መካከል በሰማይ ጦርነት ይካሄዳል (ራእይ 12፡7-9)። ሰይጣን በሚዋጋበት ጊዚ “መላእክቱ” ማለትም የወደቁት መላእክት ከጎኑ ይቆማሉ። ሰይጣንና የወደቁት መላእክት በውጊያው ይሸነፋሉ፤ “ዓለሙንም ሁሉ የሚያስተው፥ ዲያብሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀደመው እባብ ተጣለ፤ ወደ ምድር ተጣለ፤ መላእክቱም ከእርሱ ጋር ተጣሉ” (ራእይ 12፡9)።
ራእይ 12፡10 ውስጥ እንደተገለጠው፥ ዕይጣን ባለማቋረጥ ወንድሞችን በመክሰስ በአምላካችን ፊት ቀንና ሌሊት ያሳጣቸው ነበር። መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ሰኢዮብ የተጠቀሰው የሰይጣን የክስ ተግባር፥ በመጨረሻ በራሱ በሰይጣን ላይ የሚደርሰውን የኋላ ኋላ ፍርድ በማመልከት ይጠቃለላል። ከዚህ ነጥብ ጀምሮ፥ ከክርስቶስ ዳግም ምጽአት ሰግምት እርባ ሁለት ወራት በፊት (ራእይ 12፡6 ይመልከቱ) ትንቢታዊ ፕሮግራም መሠረት ሰይጣንና ክፉ መላእክት ላረዥም ጊዜ ከሰማይ ይወገዳሉ። ክርስቶስን ለመፈተን ባልቻለ ወቅት መታየት የጀመረው የሰይጣን ሽንፈት ክርስቶስና ተከታዮቹ አጋንንትን ባስወጡበት ክንውን ገሃድ ለመሆን ችሏል። ክርስቶስ የመስቀል ላይ ሞት የተረጋገጠው የሰይጣን ድል መሆን በፍጥነት ወደ ፍጻሜው በመገስገስ ላይ ነው። ቀደም ሲል ጥፋተኛ ሆኖ የተገኘውና ፍርድ የተሰጠው ሰይጣን አሁን ፍርዱ ተፈጻሚ ይሆንበታል።
ሐ. የሰይጣን ታሥሮ ወደ ጥልቁ መጣል
በክርስቶስ ዳግም ምጽአት ወቅት ፍርድ የሚሰጠው በተሳዳቢዋ ዓለምና በአለቆቿ ሳይ ብቻ ሳይሆን፥ በሰይጣንና በወደቁት መላእክት ላያም ነው። በራእይ 20፡1-3 ውስጥ ዮሐንስ የሚከተለውን ጽፏል፡- “የጥልቁንም መክፈቻና ታላቁን ሰንሰለት በእጁ የያዘ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ። የቀደመውንም እባብ ዘንዶውን እርሱም ዲያብሎስና ሰይጣን የተባለውን ያዘው፥ ሺህ ዓመትም አሠረው፥ ወደ ጥልቅም ጣለው፥ አሕዛብንም ወደፊት እንዳያስት ሺህ ዓመት እስኪፈጸም ድረስ በእርሱ ላይ ዘግቶ ማኅተም አደረገሰት፤ ከዚያም በኋላ ለጥቂት ጊዜ ይፈታ ዘንድ ይገባዋል።”
በዚህ ራእይ፥ ስለ ሰይጣን ፍርድ ተጨማሪ ነገር ተገልጧል። የሰይጣን መታሠር ወደ ጥልቁ መጣልና የተዘጋበት መሆኑ ብቻ ሳይሆን፥ ይህ ፍርድ የተሰጠበት ምክንያትም ለዮሐንስ ተነግሮታል። የዚህ ፍርድ ዓላማ የሺህ ዓመቱ መንግሥት አገዛዝ እስኪፈጸም ሰይጣን ሕዝቦችን እንዳያስት ነው። እውነቱ ለዮሐንስ በራእይ የተገለጠ ስለሆነ የዚህ ራእይ ፍች ግልጥ ነው። ሰይጣን አዳምና ሔዋን ከተፈጠሩበት ጊዜ አንሥቶ ያደርግ እንደነበረው ዓለምን ሊያታልል አይችልም።
በክርስቶስ ምድራዊ የሺህ ዓመት አገዛዝ ወቅት የሰይጣን መታሠር ግልጥ እውነትነት፥ የሺህ ዓመቱ መንግሥት ገና የሚሆን እንጂ አሁን ያለ የእግዚአብሔር አገዛዝ ላለመሆኑ ሌላው ጠቃሚ ማረጋገጫ ነው። ቀደም ሲል እንደተመለከትነው (ምዕራፍ 23)። ሰይጣን አሁን ያልታሠረ መሆኑ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ግልጥ ሆኗል። ራእይ 19-20 ውስጥ ያለው ቃል በቀጥታ መፈጻም ካለበት፥ መጀመሪያ የክርስቶስ ምጽአት፥ ከዚያ ቀጥሉ ወዲያው የሰይጣን መታሠር ተግባራዊ ሊሆን የግድ ነው። ራእይ ምዕራፍ ሀያ ውስጥ ከርሱ ቀደም ብለውና በኋላ ከሚፈጸሙት ክሥተቶች ጋር የሺህ ዓመቱ መንግሥት ስድስት ጊዜ ተጠቅሷል። በግልጥ እንደሚታየው፥ ሰይጣን የሚታሠረው የሺህ ዓመቱ መንግሥት ጊዜ ከመጀመሩ በፊት ነው።
ስለወደቁት መላእክት እዚህ ምንም ሳይጠቀስ፥ ከሰይጣን ጋር ከአርባ ሁለት ወራት በፊት ከሰማይ እንደተጣሉ ሁሉ አብረውት እንደሚታሠሩ ለመገመት ይቻላል። መጨረሻው ላይ ለአጭር ጊዜ ሲፈታ ከሚሆነው በቀር፥ በሺህ ዓመቱ መንግሥት ውስጥ ሰይጣን ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ ሲያደርግ የሚያሳይ መረጃ የለም።
መ. የሰይጣን የመጨረሻ ፍርድ
በራእይ 20፡7 ውስጥ “ሺሁም ዓመት ሲፈጸም ሰይጣን ከእሥራቱ ይፈታል” ይሳል። ቀጠል አድርገን ስናነብ ደግሞ የሚከተለውን አሳብ እናገኛለን፡- “በአራቱም በምድር ማዕዘን ያሉትን አሕዛብ፥ ሰግንና ማጎግን እንዲያስታቸው ለሰልፍም እንዲያሰከትታቸው ይወጣል፤ ቁጥራቸውም እንደ ባሕር አሸዋ የሚያህል ነው። በውጫዊ ጎጽታቸው ብቻ ክርስቶስን እንከተላለን ይሉ የነበሩ ሰዎች በሰይጣን እየተመሩ አሁን እውነተኛውን ማንነታቸውን ያሳያሉ። እነዚህ በሺህ ዓመቱ መንግሥት ዘመን የተወለዱ ልጆች ናቸው፤ ምንም እንኳ በሁኔታዎች አስገዳጅነት በክርስቶስ አምነናል ቢሉ፥ አሁን ግን በግልጥ ዓመፅ የቅዱሳንን ሰፈር እና የተወደደችውን ከተማ ማለትም ኢየሩሳሌምን ይወራሉ። ዕድል-ፈንታቸው ቅፅበታዊ ፍርድ ሲሆን፥ ራእይ 20፡9 ውስጥ እንደሚለው፥ “እሳት ከሰማይ ከእግዚአብሔር ዘንድ ወርዳ በሳቻቸው።”
ከዚያም ወዲያውኑ «ያሳታቸውም ዲያብሎስ፥ አውሬውና ሐሰተኛው ነቢይ ወዳሉበት ወደ እሳቱና ወደ ዲኑ ባሕር ተጣል፥ ለዘላለምም እስከ ዘላለም ቀንና ሌሊት ይሣቀያሉ” (ቁ. 10)። እግዚአብሔር ለዲያብሎስና ለመላእክቱ ያዘጋጃቸው የመጨረሻ
መቅጫ የእሳት ባሕር እንደመሆኑ፥ የሰይጣን መጨረሻ በዚሁ ይደመደማል (ማቴ. 25፡4 )።
የወደቁ መላእክትም ሰይጣን መጀመሪያ በእግዚአብሔር ላይ የወጠነው ዓመፅ ተካፋዮች ስለነበሩ ፍርድ ተሰጥቷቸዋል (ኢሳ. 14፡12-17፤ ሕዝ. 28፡12-19)። 2ኛ ጴጥሮስ 2፡4፥ “እግዚአብሔር ኃጢአትን ላደረጉ መላእክት ሳይራራላቸው ወደ ገሃነም ጥሎ በጨለማ ጉድጓድ ለፍርድ ሊጠበቁ አሳልፎ” እንደሰጣቸው ይናገራል። “ገሃነም” የሚለው ቃል የሚያመለክተው፥ ኃጢአተኛ ወደ ዘላለማዊ የቅጣት ስፍራ ከመሄዱ በፊት ለጊዜው የሚቆይበትን ስፍራ ማለትም “ሲኦልን” ሳይሆን፥ ዘላለማዊውን የቅጣት ስፍራ ነው (ራእይ 20፡13-14)።
– የመላእክትም ፍርድ ይሁዳ መጽሐፍ ቁጥር 6 ውስጥ እንዲህ ተመልክቷል። “መኖሪያቸውን የተዉትን እንጂ የራሳቸውን አለቅነት ያልጠበቁትን መላእክት በዘሳሰም እሥራት ከጨለማ በታች እስከ ታላቁ ፍርድ ቀን ድረስ ጠብቋቸዋል።” ይህ አሳብ ስለ ሰይጣንና መላእክቱ ውድቀትና ፍርድ ከሚናገሩት ሴሎች የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባቦች ጋር ሲያያዝ፥ የሚያስተላልፈው ግልጥ መልእክት አለ። ይሄውም ምንም እንኳ ሰይጣንና አንዳንድ ክፉ መላእክት የተወሰነ ነጻነት ቢሰጣቸው፥ በቅዱሳን መላእክትና በእግዚአብሔር ሰዎች ላይ የማያቋርጥ ጦርነት ቢከፍቱም፥ የታሠሩና ነጻነት የተነፈጋቸው ሌሎች መላእክት የሚኖሩ መሆናቸውን ነው። ይሁን እንጂ፥ ክፉዎቹ መላእክት ሁሉ “ለታላቁ ፍርድ ቀን” የተወሰኑ ናቸው። ይህ “የታላቁ ፍርድ ቀን” በሺህ ዓመቱ መንግሥት ፍጻሜ ሰንሰይጣንና በወደቁት መላእክት ሁሉ ላይ የሚሰጥ ነው።
ምንም እንኳ በእግዚአብሔር ፈቃድ ሰይጣንና የወደቁ መላእክት በዓለም ላይ ከፍተኛ ኃይልና ተጽዕኖ ሲያሳድሩና ባለማቋረጥ እግዚአብሔርን ሲቃወሙ፥ የኋላ ኋላ ሽንፈታቸውና ዘላለማዊ ፍርዳቸው አይቀሬ ነው። እንደ ኢዮብ የሰይጣን ጥቃት የደረሰባቸው ክርስቲያኖች የኋላ ኋላ ድላቸው የተረጋገጠ እንደሚሆንና፥ እግዚአብሔር በራሱ ጊዜ በጠላቶቹ ላይ የሚፈርድባቸው መሆኑን በመረዳት ሊያርፉ ይችላሉ። በሰይጣንና በመላእክቱ ላይ የሚሰጠው ፍርድ ዘላለማዊ የመሆኑ ግንዛቤ የመጣው፥ አውሬውና ሐሰተኛው ነቢይ ሰሺህ ዓመቱ መንግሥት መጀመሪያ እሳት ባሕር ውስጥ ተጥለው እስከ መንግሥቱ ፍጻሜ እዚያው ከመሆናቸው የተነሣ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ በግልጥ እንደሚናገረው፥ ሁለት ዓበይት ፍርዶች ብቻ አሉ። እነዚህም ማለቂያ የሌለው ሰማያዊ በረከት መቀበልና ዘላለማዊ የሆነው የእሳት ባሕር ሥቃይ ናቸው።
ምንጭ፡- “ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ ጭብጦች” መጽሐፍ በዶክተር ሉዊስ ስፔሪ ቼፈር የተጻፈ እና በተክሉ መንገሻ የተተረጎመ ነው፡፡ እግዚአብሔር ስለ እነዚህ ቅዱሳን ድንቅ ስራ የተመሰገነ ይሁን፡፡ ማሳሰቢያ፡- ይህን ጽሁፍ መቀየርም ሆነ ለሽያጭ ማዋል በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡