ህ. የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ሲብራራ
ከመንፈስ ቅዱስ የማዳን ተግባራት፥ ማለት ዳግም ከመወለድ፥ በእማኝ ውስጥ ከማደር፥ ኮማተም እና ከማጥመቅ ሥራ ጋር ሲነጻጸር፥ የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ከከርስቲያን ልምምድ፥ ኃያል እና አገልግሎት ጋር ነው የሚገናኘው። ከድነት ጋር የተያያዘው የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ለአንዴና ለዘላለም የሚከናወን ሲሆን፥ የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ግን የሚደጋገም ልምምድ መሆኑ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙ ጊዜ ተገልጧል።
የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ከጰንጠቆስጤ ዕለት በፊት በጣም ውሱን በሆነ ደረጃ በአንዳንድ ግለሰቦች ላይ ታይቷል (ዘፀ. 28፡3፤ 31፡3፣ 35፡31፤ ሉቃስ 1፡15፥ 41፥ 67፤ 4፡1)። የእግዚአብሔር መንፈስ ሰግለሰቦች ላይ መውረዱና የአገልግሎት ኃይል የሞላበት ሁኔታ መኖሩ የሚያጠራጥር አይደለም። በአጠቃላይ ሲታይ ግን ካጳንጠቆስጤ ዕለት በፊት በመንፈስ ቅዱስ የተሞሉት ጥቂት ናቸው። የመንፈስ ቅዱስ ሥራም እግዚአብሔር በልዑል ዓላማው መሠረት በግለሰቦች አማካይነት ከሚያከናውነው አንዳንድ ልዩ ሥራዎች ጋር የተያያዘ ይመስላል። የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ከጰንጠቆስጤ ዕለት በፊት ሕይወቱን ለጌታ ለሰጠ ሰው ሁሉ ክፍት የነበረ መሆኑን የሚያመለክት ነገር የለም።
ከጰንጠቆስጤ ዕለት ወዲህ ያለው ጊዜ መንፈስ ቅዱስ በአማኞች ሁሉ የሚሠራበት እዲስ ዘመን ሆኗል። በዚህ ዘመን አማኝ ሁሉ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ ካምሆኑም በላይ፥ ቅድመ ሁኔታዎችን ካሟላ ሰመንፈስ ቅዱስ ሊሞላ ይችላል። ይህን እውነት አዲስ ኪዳን ውስጥ ያሉ አያሌ መግለጫዎች ያረጋግጣሉ (ሐዋ. 2፡4፤ 4፡8፥ 31፤ 6፡3፥ 5፤ 7፡55፤ 9፡17፤ 11፡24፤ 13፡9፥ 52፤ ኤፌ. 5 ፡18)።
የመንፈስ ቅዱስ ሙላት፥ መንፈስ ቅዱስ በአማኝ ልብና ሕይወት ውስጥ ሊሠራ የሚፈልገውን ያለመከልከል ሲሠራ በእማኝ ሕይወት ውስጥ የሚከሰት ሁኔታ ነው ማለት ይቻላል። ድርጊቱ መንፈስ ቅዱስን ይበልጥ የመቀበል ሳይሆን፥ የእግዚአብሔር መንፈሰ ራሱ አማኙን ይሰልጥ የራሱ ማድረጉ ነው። የመንፈስ ቅዱስ ሙላት በዚህ ዘመን ከጰንጠቆስጤ ዕለት በፊት እንደነበረው በተወሰኑ ሰዎች ላይ ለልዩ ሥራ መከናወን የሚሆን ሳይሆን፥ አማኞች ሁሉ ሊያገኙት የሚቻላቸውና በእርሱ ለሚያምን ሁሉ ከእግዚአብሔር የቀረበ የክርስቲያን ልምምድ ነው። ክርስቲያን ሁሉ በመንፈስ ቅዱስ እንዲሞላ ታዟል (ኤፌ. 5፡18)፤ በመንፈስ ቅዱስ አለመሞላት ግን ከፊል አለመታዘዝ ነው።
ክርስቲያን ባሕርይና ዕለታዊ ሕይወቱ ውስጥ በግልጥ የሚታይ ልዩነት አለ። ጥቂቶች መንፈስ የሞላሳቸው ሆነው ይታወቃሉ። የዚህ ጸጋ ተጠቃሚዎች ቁጥር ጥቂት የመሆኑ ምክንያት፥ ከእግዚአብሔር ልግስና ማነስ ሳይሆን፥ ሰዎች ራሳቸውን ሳያዘጋጁና የእግዚአብሔር መንፈስ ሕይወታቸውን እንዲሞላው ሳይፈቅዱ መቅረታቸው ነው።
በመንፈስ ቅዱስ መሞላት ከመንፈሳዊ እድገት ጋር ሊነጻጸር ይገባል። ድነትን ካገኘ አጭር ጊዚው የሆነ አዲስ ክርስቲያን በመንፈስ ቅዱስ ሊሞላና የመንፈስ ቅዱስ ኃያልም በሕይወቱ ሊገለጥ ይችላል። በክርስትና ሕይወት መብሰል፥ በእውቀት ማደግ፥ በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት የማያቋርጥ ልምምድ እና መንፈሳዊ ነገሮችን በመለየት ማደግ ነው። ይህ የሚገኘው፥ እስከ ሕይወት ፍጻሜ በሚያድግ መንፈሳዊ ልምምድ ይሆናል። አዲስ የተወለደ ሕፃን ሙሉ ጤናማ ሊሆን እንደሚችል፥ አዲስ ክርስቲያንም በመንፈስ ቅዱስ ይሞላ ይሆናል። ነገር ግን ልክ አዲስ እንደተወለደ ሕፃን አዲሱን ክርስቲያንም ወደ እድገት የሚያደርሰው በሕይወቱ የሚያገኘው ልምምድ ነው። ለዚህ ነው ብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባቦች ስለ መንፈሳዊ እድገት አበክረው የሚናገሩት። የስንዴ ቡቃያ እስከ መከር ያድጋል (ማቴ. 13፡30)። እግዚአብሔር መንፈሳዊ ስጦታዎች ባሏቸው ሰዎች አማካይነት ቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ ይሠራል። ይህን የሚያደርገው፥ ቅዱሳኑን ለአገልግሎት ብቁ ለማድረግ፥ በእምነት በእውቀትና በመንፈሳዊ ሁኔታ ለማሳደግ እንዲሁም የክርስቶስ አካል የሆነችውን ቤተ ክርስቲያን ለመቀደስ ነው (ኤፌ. 4፡11-16)። ጴጥሮስ አዲስ የተወለዱ ሕፃናት ለእድገታቸው መንፈሳዊ ወተት እንደሚያሻቸው ይናገራል (1ኛ ጴጥ. 2:2)። “በጌታችንና በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና እውቀት እደጉ” (2ኛ ጴጥ. 3፡18) በማለትም ክርስቲያኖችን ይመክራል።
በመንፈስ ቅዱስ ሙላትና በመንፈሳዊ እድገት መካከል ግልጥ የሆነ ግንኙነት አለ። በዚሁ መሠረት በመንፈስ ቅዱስ ካልተሞላ ከርስቲያን ይልቅ የተሞላው በፍጥነት በመንፈስ ያድጋል። በመንፈስ ቅዱስ መሞላትና ውጤቱ የሆነው መንፈሳዊ እድገት፥ እግዚአብሔር ለሕይወቱ ያለውን ፈቃድ ለማግኘት፥ የእርሱንም እቅድ በመፈጸም ረገድ በክርስቲያን ሕይወት የሚከናወኑ ሁለት ዋና ዋና ነገሮች ናቸው (ኤፌ. 2፡10)።
በዚህ መሠረት የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ለማንኛውም አማኝ የሚደረግ ነው። ይህ የሚሆነው ግን አማኙ ሕይወቱን ሙሉ በሙሉ ውስጡ ለሚኖረው መንፈስ ቅዱስ ሲያስገዛ ይሆናል። ይህ ሲሆን መንፈስ ቅዱስ ግለሰቡን ይቆጣጠረዋል፥ ኃይልም ይሰጠዋል። የመንፈስ ቅዱስ ሙላት የሚገለጥባቸው ሁኔታዎችና የሚሰጠው መለኮታዊ ኃይል ደረጃም ያላያዩ ይሆናል። በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ማዕከላዊ አሳብ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለ ምንም መከልከል በአማኙ ውስጥና በርሱ በኩል ይሠራል የሚል ነው። እግዚአብሔር ለዚያ ሰው ያለው ፍጹም ፈቃድ እንዲህ ይከናወናል።
የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ፅንሰ አሳብ አዲስ ኪዳን ውስጥ በርከት ባሉ ጥቅሶች ተመልክቷል። እጅግ በላቀ ሁኔታ የታየው፥ ሉቃስ 4፡1 ውስጥ “መንፈስ ቅዱስ ሞልቶበት፥ በተባለው በኢየሱስ ነው። መጥምቁ ዮሐንስ እናቱ ማኅፀን ውስጥ እንዳለ በመንፈስ ቅዱስ በመሞላቱ በሌሎች ያልተላመደ ልምምድ በረው (ሉቃስ 1፡15)። እናቱ ኤልሳቤጥና አባቱ ዘካርያሰም ለጊዜው በመንፈስ ቅዱስ ተሞልተው ነበር (ሉቃስ 1፡41፥ 67)። ይህን የመሰለው የመንፈስ ቅዱስ ሙላት፥ ለጥቂት ሰዎች ብቻ የሚደረግና ሰብሉይ ኪዳን በተደረገው አኳኋን የሚከናወን የልዑል እግዚአብሔር እሠራር ነው።
በጰንጠቆስጤ ዕለት ግን በዚያ የነበሩት ሁሉ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልተዋል። ሰጥንታዊቱ ቤተ ክርስቲያን፥ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለማድረግ የፈለጉ ሁሉ፥ በጴጥሮስ እንደሆነው (ሐዋ. 4:8) በተደጋጋሚ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልተዋል። ለእግዚአብሔር ኃይልና ብርታት የጸለዩ ክርስቲያኖች (ሐዋ. 4፡31)፥ ጳውሎስም ከተለወጠ በኋላ (ሐዋ. 9፡17) እንዲሁ ተሞልቷል። አንዳንዶች፥ ማለት የመጀመሪያዎቹ ዲያቆናት፥ (ሐዋ. 6፡3)። ሰማዕቱ እስጢፋኖስ (ሐዋ. 7:55) እና በርናባስ (ሐዋ. 11፡24) በተከታታይ በመንፈስ ቅዱስ እንደተሞሉ ተናግሯል። ጳውሎስ በተደጋጋሚ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቷል (ሐዋ. 13፡9)፤ ሌሎች ደቀ መዛሙርትም እንዲሁ (ሐዋ. 13: 52)። በእያንዳንዱ ሁኔታ በመንፈስ ቅዱስ የተሞሉት ራሳቸውን ለእግዚአብሔር የሰጡ ክርስቲያኖች ብቻ ናቸው።
የብሉይ ኪዳን አማኞች በአንዳንድ ሁኔታዎች ተግሣጽ ቢሰጣቸውም በመንፈስ ቅዱስ እንዲሞሉ ሰፍጹም አልታዘዙም። የእግዚአብሔር ሥራ መከናወኑን አስመልክቶ ዘሩባቤል በመንፈሴ እንጂ በኃይልና በብርታት አይደለም፡(ዘካ. 4፡6) ተብሏል። በዚህ ዘመን ክርስቲያን ሁሉ ኤፌሶን 5፡18 ውስጥ እንደተመለከተው በመንፈስ ቅዱስ እንዲሞላ ታዟል። “መንፈስ ቅዱስ ይሙላባችሁ እንጂ፥ በወይን ጠጅ አትስከሩ፥ ይህ ማባከን ነውና።” ድነት በእምነት እንጂ በሥራ እንደማይገኝ፥ በመንፈስ ቅዱስ መሞላትም በሰብአዊ ጥረት የሚሆን አይደለም። ያ የሚሆነው፥ አንድ ሰው እግዚአብሔር በሕይወቱ ይህን የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ይሠራ ዘንድ ሲፈቅድ ነው። ከመጽሐፍ ቅዱስ እንደምንረዳው፥ አንድ ክርስቲያን በመንፈስ ቅዱስ ሳይሞላ ድነትን ሊያገኝ ይችላል። በዚህ መሠረት የመንፈስ ቅዱስ ሙላት የድነት አንዱ አካል አይደለም ማለት ነው። የመንፈስ ቅዱስ ሙላት አንድ አማኝ በዳነ ጊዜ ለአንዴና ለዘላለም በሕይውቱ ከተከናውነው ሥራ ጋር ሊገናዘብ ይችላል። አንድ ሰው ድነትን ሲያገኝ በመንፈስ ቅዱስ ሊሞላ ቢችል እንኳን፥ ክንውኑ ሕይወቱን ከሰጠ ክርስቲያን ውስጥ በተደጋጋሚ የሚፈጸም ነው። በመሆኑም ይህ ተደጋጋሚ የመንፈስ ቅዱስ ሙላት የክርስቲያኖች የዘወትር ልምምድ ሊሆን ይገባል።
በመንፈስ ቅዱስ መሞላት በተደጋጋሚ መፈጸም ያለበት መሆኑ ኤፌሶን 5፡18 ውስጥ “መንፈስ ይሙሳሳችሁ” በሚለው ቃል ተገልጧል። ቃሉ “ሁልጊዜ በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ” የሚል ቀጥተኛ ፍቺ ነው ያለው። ይህ ቃል ምንባቡ ውስጥ ሰውነትንና አእምሮን ከሚጎዳ ስካር ጋር ተነጻጽሯል። ስለዚህ የመንፈስ ቅዱስ ሙላት አንድ ጊዜ ለዘላለም የሚሆን ነገር አይደለም። በተደጋጋሚ የሚከናወን ነገር ሆኖ ሳለ፥ አልፎ አልፎ እንደሚሰማው ሁለተኛ የጸጋ ሥራ መባሉ ግን ተገቢ አይደለም። ለመጀመሪያ ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ልምምድ ያለ ጥርጥር ለክርስቲያን አስደናቂ ሁኔታ ነው። የክርስትና ልምምድንም ወደ አዲስ ከፍታ የሚያወጣ የመሠረት ድንጋይ ሊሆንም ይችላል። ያም ሆነ ይህ ክርስቲያን ለማያቋርጥ የመንፈስ ቅዱስ ሙላት በእግዚአብሔር ነው የሚተማመነው፤ በትላንትናው መንፈሳዊ ኃይል የሚኖር ክርስቲያን የለም።
በመንፈስ ቅዱስ ከመሞላት ምንነት በመነሣት በክርስቲያኖች መንፈሳዊ ልምምድና በእግዚአብሔር ዓላማ እንዲሁም ፍላጎት መጣጣም መካከል ሰፊ ልዩነት የሚኖረው በመንፈስ ቅዱስ ከመሞላት ወይም ካለመሞላት የተነሣ ነው ብሎ ለመደምደም ይቻላል። የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለመፈጸም የሚፈልግ አማኝ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ እንዲሆን ከእግዚአብሔር ወደተሰጠው መብት መግባትና ሕይወቱንም ለእግዚአብሔር መንፈስ ሙሉ በሙሉ ማስረከብ ይኖርበታል።
ለ. ለመንፈስ ቅዱስ ሙላት የሚያስፈልጉ ሁኔታዎች
በመንፈስ ቅዱስ መሞላት የሚያስፈልጉ ሦስት ቀላል ትእዛዛት ተጠቅሰዋል። እነርሱም የሚከተሉት ናቸው።
የመጀመሪያዎቹ ሁለት ክፍሎች አሉታዊ ትእዛዞች ሲሆኑ፥ ሦስተኛው አዎንታዊ ነው። 1ኛ ተሰሎንቄ 5፡19 ውስጥ “መንፈስን አታጥፉ” የሚል ትእዛዝ ተሰጥቷል። ኤፌሶን 4፡30 ውስጥ ደግሞ ክርስቲያኖች “ለቤዛ ቀን የታተማችሁበትን ቅዱሱን የእግዚአብሔርን መንፈስ አታሳዝኑ” ተብለዋል። ሦስተኛው ትእዛዝ ጎላትያ 5፡16 ውስጥ የተጠቀሰው ሲሆን “ነገር ግን እላለሁ ፥ በመንፈስ ተመላለሱ፥ የሥጋንም ምኞት ከቶ አትፈጽሙ” ይላል። ስለ መንፈስ ቅዱስ ሙላት የሚያስረዱ ሌሎች ክፍሎች ቢኖሩም፥ እነዚህ ሦስቱ ዋና ዋናዎችን ያጠቃልላሉ።
1. መንፈስን አታጥፉ” ተብሎ 1ኛተስሎንቄ 5፡19 ውስጥ fተሰጠው ትእዛዝ፥ እገሰቡ በደንብ የተለጠ ሳይሆንም፥ መንፈስ ቅዱስን ስእሳት ምሳሌነት ዮሚያሳይ መሆን ግለጥ ነው። “ማጥፋት” ማለት መንፈስ ቅዱስ በአማኝ ውስጥ ፈቃዱን እንዳይፈጽም ማፈን ወይም ነጻነትና ፈቃድ መከልከል ማለት ነው። በቀላሉ ሲገለጥ መንፈስ የራሱን ፈቃድ እንዳያደርግ (“እምቢ” ማለት ወይም ፈቃደኛ አለመሆን ሊሆን ይችላል።
በእግዚአብሔር ላይ ማመፅ የሰይጣን የመጀመሪያ ኃጢአት ነበር (ኢሳ. 14፡14)፤ እናም አንድ ክርስቲያን ክርስቶስ በጌቴሴማኒ እንዳደረገው “የእኔ ፈቃድ አይሁን የአንተ እንጂ” ( ሉቃስ 22: 42) በማለት ፈንታ የእኔ ፈቃድ ይሆናል”፥ በሚልበት ጊዜ መንፈስ ቅዱስን ማጥፋቱ ነው።
አንድ አማኝ የመንፈስ ቅዱስ ሙላትን ለመለማመድ ይችል ዘንድ በመጀመሪያ ሕይወቱን ለጌታ ማስረከብ አለበት። አንድ ሰው ሁለት ጌቶችን ሊያገላግል እንደማይችል ክርስቶስ ገልጧል (ማቴ. 6፡24)። ክርስቲያኖችም ራሳቸውን ስእግዚአብሔር እንዲሰጡ በተከታታይ ተመክረዋል። የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቲያን ሕይወት የሚከናወንበትን ጠቅላላ ሁኔታ ጳውሎስ ሮሜ 6፡13 ውስጥ ሲያስተዋውቅ፥ “ብልቶቻችሁን የዓመፃ የጦር ዕቃ አድርጋችሁ ለኃጢአት አታቅርቡ፤ ነገር ግን ከሙታን ተለይታችሁ በሕይወት እንደምትኖሩ ራሳችሁን ለእግዚአብሔር አቅርቡ። ብልቶቻችሁንም የጽድቅ የጦር ዕቃ አድርጋችሁ ለእግዚአብሔር አቅርቡ” ብሏል። ምርጫው በእያንዳንዱ ክርስቲያን ፈት ተቀምጧል። ራሱን ለእግዚአብሔር ወይም ኃጢአት ሊሰጥ ይችላል።
ሮሜ 12:1-2 ውስጥም ተመሳሳይ ምንባብ አለ። ጳውሎስ በእንድ ክርስቲያን ሕይወት ድነትና ቅድስና የሚያድግበትን ሁኔታ ለሮሜ ሰዎች ሲገልጥ፥ “እንግዲህ ወንድሞች ሆይ፥ ሰውነታችሁን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝና ሕያው ቅዱስም መሥዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ በእግዚአብሔር ርኅራኄ እለምናችኋለሁ፥ እርሱም ለአእምሮ የሚመች አገልግሎታችሁ ነው። የእግዚአብሔር ፈቃድ፥ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ፥ ይህን ዓለም እትምሰሉ” እያለ ያሳስባል። ሮሜ 6፡13 እና 12፡1 ውስጥ “ራሳችንን ለእግዚአብሔር ማቅረብ የሚለው የግሪኩ አባባል ያለው ስሜት “ለአንዴና ለዘላለም ራስን ለእግዚአብሔር መስጠት” የሚል ነው። በመሆኑም በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት የሚቻለው፥ ክርስቲያን መላ ሕይወቱን ሕያው መሥዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር የማስረከቡን ቀዳሚ እርምጃ የወሰደ እንደሆን ብቻ ነው። ክርስቲያን ለዚህ ዕድል የሚዘጋጀው፥ መሥዋዕቱን ቅዱስና በእግዚአብሔር ዘንድ ብቁ በሚያደርገው ድነቱ አማካይነት ነው። ለዚህ ድነትን ለሚቀበል ሰው ኢየሱስ ክርስቶስ የሞተለት ስለሆነ፥ እግዚአብሔር ከዚያ ሰው ይህን ሁኔታ መጠበቁ ተገቢ ነው።
ክርስቲያን ራሱን ለእግዚአብሔር በሚያቀርብበት ጊዜ፥ የውስጥ ሰውነቱ በመንፈስ ቅዱስ የሚለወጥበትና፥ ክዚህ የተነሣ የእእምሮ መታደስን በማግኘቱ የመንፈሳዊ እውነቶችን ክቡርነት የሚገነዘብበት ሂደት ነው። ራሱን ለጌታ በማቅረቡ ይህን ዓለም የማይመስልን ሕይወት ይኖራል። የእግዚአብሔር ፈቃድ ያልሆነውን ከ እግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር” ሮሜ 12፡2 ለመለየት ይችላል።
ራስን መስጠት የሚያመለክተው አንድን የተለየ ጉዳይ ሳይሆን፥ በማንኛውም ረገድ እግዚአብሔር ለሕይወቱ ያለውን ፈቃድ ያ ሰው መውሰዱ ነው። ስለዚህ ራስን መስጠት ማለት፥ እግዚአብሔር አማኙ እንዲያደርግ የሚፈልገውን ነገር ሁሉ ለማድረግ ፈቃደኛ መሆን ማለት ነው። የእግዚአብሔርን ፈቃድ በሕይወቱ መፈጸም እና እርሱ ሲመራ ማንኛውንም ነገር መቼም የትም እና እንደ ምንም ለማድረግ ፈቃደኛ ሆኖ መገኘት ነው። “መንፈስን አታጥፋ” የሚለው ትእዛዝ የሚያመለክተው፥ ይህ ሁኔታ ራስን በመስጠት የሚጀምርና የሚቀጥል ልምምድ መሆኑን ነው።
ባለማቋረጥ ራሱን ለእግዚአብሔር ለመስጠት የሚመኝ ክርስቲያን፥ ድርጊቱ ከብዙ ሁኔታዎች ጋር የሚዛመድ ሆኖ ያገኘዋል። ራስን መስጠት ከሁሉ በፊት ለእግዚአብሔር ቃል ትምህርትና እውነት መገዛት ነው። ታላቁ መምህር መንፈስ ቅዱስ ሲሆን፥ አንድ አማኝ እውነትን በተረዳ ቁጥር ላወቀው እውነት መግዛት አለበት። ለእግዚአብሔር ቃል አለመገዛት የመንፈስ ቅዱስ ሙላትን ይከላከላል።
ራስን መስጠት ካምሪት ጋርም ይያያዛል። በብዙ ሁኔታዎች የእግዚአብሔር ቃል ክርስቲያን ሊወስነው የሚጎባውን ነገር በግልጥ አያስረዳም። ስለዚህ አንድ አማኝ በእግዚአብሔር ቃል መመራት አለበት፥ የእግዚአብሔር መንፈስም ቃሉ በሚገልጠው ላይ በመመሥረት ምሪት ይሰጣል። በመሆኑም በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት ለመንፈስ ቅዱስ ምሪት መታዝ ያሻል (ሮሜ 8፡14)። አንዳንድ ጊዜ ክርስቲያን አንድ ነገር ያደርግ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ ያዘው፥ በሌላ ሁኔታ ደግሞ ይከለክለው ይሆናል። አንዱ ምሳሌ በአገልግሎቱ መጀመሪያ ወቅት እስያና ቢታኒያ ውስጥ እንዳይሰብክ የተከለከለው ጳውሎስ ነው። በኋላ ግን ወደነዚሁ ስፍራዎች እንዲሄድና እንዲሰብክ ታዟል (ሐዋ. 16፡6-7፤ 19፡10)። የመንፈስ ቅዱስ ሙላትና ጌታ መመራት የማይነጣጠሉ ናቸው።
አንድ ክርስቲያን የማይፈልገው ሁኔታና ልምምድ ውስጥ የሚከተው ቢሆን እንኳን ለእግዚአብሔር ምሪት መገዛት አለበት። ስለዚህ ጉዞው ሥቃይ ያለበትና ደስ የሚያሰኝ ቢሆንም እንኳ፥ ለእግዚአብሔር ፈቃድ መገዛት ማለት ምን ማለት መሆኑን አማኝ መገንዘብ እለበት።
በመንፈስ ቅዱስ የመሞላትና ለእግዚአብሔር የመሰጠት ታላቅ ምሳሌ ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ ነው። ፊልጵስዩስ 2፡5-11 ውስጥ ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ምድር በመምጣቱና ለዓለም ኃጢአት በመሞቱ፥ እግዚአብሔር ወደመረጠው መሄድንና እብ የመረጠውን ሥራ መፈጸምን ያሳያል። በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት የሚመኝ አማኝ ይህን የመሰለ መሰጠትና ታዛዥነት ሊኖረው ይገባል።
2. በመንፈስ ቅዱስ ከመምላት ጋር በተያያዘ ሁኔታ፥ እማኝ “መንፈስ ቅዱስን እንዳያሳዝን” (ኤፌ. 4፡30 ተመክሯል። ይህ ከፍል ኃጢአት ወደ ከርስቲያኑ ሕይወት መግባቱንና ራሱንም ለጌታ እለመስጠቱን ያመለክታል። በመሆኑም ክርስቲያን በመንፈስ ቅዱስ የተሞላ ሕይወት እንዲኖረው፥ መንፈስ ቅዱስን የሚያሳዝን ኃጢአት እንዳይሠራ ታዟል። አማኝ ውስጥ ያለ የእግዚአብሔር መንፈስ ሲያዝን፥ ከአማኙ ጋር ያለው አንድነት፥ ምሪት፥ ትምህርቱ እና የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ይታገዳል። ምንም እንኳን መንፈስ ቅዱስ በአማኙ ውስጥ ሲኖር፥ ሥራውን ለማከናወን ነጻ አይደለም።
የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ልምምድ በአማኙ አካላዊ ሁኔታ ሳቢያም ይታጎል ይሆናል። የደከመ፥ የራበው ወይም ሕመምተኛ ክርስቲያን የመንፈስ ቅዱስ ፍሬ የሆኑት ትከክለኛ ደስታና ሰላም በሕይወቱ እይታዩ ይሆናል። በመንፈስ ቅዱስ ስላ መሞላት የሚናገረው ሐዋርያ ራሱ 2ኛ ቆሮንቶስ 1፡8.9 ውስጥ “ስለ ሕይወታችን እንኳ ተስፋ እስክንቆርጥ ድረስ ከአቅማችን በላይ ያለ ልክ ከብዶብን ነበር ብሏል። ስለዚህ በመንፈስ ቅዱስ የተሞላ ክርስቲያንም ውስጣዊ መሽበር ይገጥመው ይሆናል። ይሁን እንጂ የአማኙ ችግር የከፋ ሰሆን መጠን፥ በመንፈስ ቅዱስ የመሞላቱና ለእግዚአብሔር ፈቃድ የመገዛቱ አስፈላጊነት የጎላ ይሆናል፤ የመንፈስ ቅዱስ ኃይል በግለሰቡ ሕይወት ይገለጥ ዘንድ ነው።
አንድ ክርስቲያን መንፈስ ቅዱስን ያሳዘነ መሆኑ ሲሰማው፥ መፍትሔው ኤፌሶን 4፡30 ውስጥ እንደተጻፈው መንፈሱን የሚያሳዝነውን ድርጊት ማቆም ነው። ይህ ሊፈጸም የሚችለው 1ኛ ዮሐንስ 1፡9 ውስጥ የተጠቀሰውን በመታዘዝና አንድ የእግዚአብሔር ልጅ ያደርገው ዘንድ የተገባን ነገር በማድረግ ነው፡– “በኃጢአታችን ብንናዘዝ፥ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያድነን የታመነና ጻድቅ ነው። ይህ ጥቅስ የሚመለከተው በሰማይ አባቱ ዘንድ ኃጢአት የፈጸመን የእግዚአብሔር ልጅ ነው። የክርስቶስ ሞት ለኃጢአት ሁሉ ሥርየት በቂ ሰመሆኑ፥ የመመለሻው ወይም ይቅርታ የማግኛው መንገድ ክፍት ነው (1ኛ ዮሐ. 2፡1-2)።
ስለዚህ አንድ አማኝ ከእግዚአብሔር ጋር ወዳለው አንድነት የመመለሻው መንገድ፥ የኢየሱስ ክርስቶስ ሞት የይቅርታ መሠረት መሆኑን በመገንዘብ ነው። ይህ ብቻም አይደል፥ ከእግዚአብሔር አብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋ እንደገና የቀረበ ግንኙነት ለመጀመር መፈለግ ወይም መወሰንም ያስፈልጋል። ይህ ሁኔታ በፍርድ ቤት የሚታይ የፍትሕ ጉዳይ ሳይሆን፥ በአባትና ልጅ መካከል ጠፍቶ የነበረውን ግንኙነት እንደገና መቀጠል ነው። እግዚአብሔር ኃጢአትን ይቅር የሚል ቅን ፈራጅና ታማኝ መሆኑን ጥቅሱ ያረጋግጣል። አንድ ክርስቲያን እግዚአብሔርን እንደበደለ አምኖ በቅንነት ንስሐ ሲገባ ሰግንኙነቱ መካከል እንደ ግድግዳ የቆመው በደል ይገዳል። የኃጢአት ንስሐ በአንዳንድ ሁኔታዎች በደል ወደተሠራባቸው ሰዎች መሄድንና ችግሩን ማስተካከልን የሚጠይቅ ቢሆንም፥ ዋናው ጉዳይ ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረትን በመመሥረት ተከናውኗል።
አንድ ክርስቲያን ሲናኝ ሰመለኮት በኩል ያለው ነገር ወዲያውኑ እንደሚስተካከልለት ዋስትና አለው። ክርስቶስ የእማኙ አማሳጅ ወይም አስታራቂና በመስቀል ላይ የሞተለት እንደመሆኑ፥ በሰማይ ያለውን አስፈላጊ ማስተካከያ ሁሉ አስቀድሞ እከናውኗል። ዕለዚህ ወደ አንድነቱ የመመለሱ ጉዳይ በሰብአዊው በኩል የሚከናወን ንስሐና ራስን የመስጠት ተግባር ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ አማኝ መንፈስ ቅዱስን በተከታታይ በማሳዞን ሳቢያ የመጣበት ክፉ ሁኔታ መኖሩንም ያስጠነቅቃል። ዕብራውያን 12፡5-6 ውስጥ እንደተመለከተው ይህ ምናልባት እማኙን ለማስተካከል ሲባል ከእግዚአብሔር የሚመጣ ቅጣት ሊሆን ይችላል። ክርስቲያን ራሱን ባያስተካክል እግዚአብሔር በመለኮታዊ ማስተካከያው ጣልቃ እንደሚገባ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶታል (1ኛ ቆሮ. 11፡31-32)። ክርስቲያን በማንኛውም ሁኔታ ከእግዚአብሔር ጋር ካለው እንድነት ሲርቅ ወዲያውኑ የሚያጣው ነገር አለ። ልክ ታማኝ አባት ባጠፋ ልጁ ላይ እንደሚያደርገው ሁሉ ተከታታይና ከባድ ቅጣት የማስከተል አደጋም ይኖራል።
3. በመንፈስ ቅዱስ መመላለስ፥ ከላይ ከተመለከትናቸው ትእዛዛት ጋር ሲነጻጸር እዎንታዊ ሳይሆን አሉታዊ ነው። በመንፈስ ቅዱስ መመላለስ ማለት (ገላ. 5፡16) ከመንፈስ ቅዱስ የሚገኘውን ኃይልና በረከት እንድንቀበል የሚያስገነዝብ ትእዛዝ ነው። ክርስቲያን ሁልጊዚ በመንፈስ ምሪት እንዲጓዝ ታዟል።
የክርስቲያን መንፈሳዊ ሕይወት ደረጃ በጣም ከፍተኛ ነው፤ ያለ እግዚአብሔር ኃይል የአምላክን ፈቃድ ሊፈጽም አይችልም። በመሆኑም በውስጡ ያለው መንፈስ ቅዱስ በሚገባ እንዲመላለስ ይመራዋል።
በመንፈስ ቅዱስ መመላለስ እምነትን ያካተተ ነው። በመሆኑም መንፈስ ቅዱስ የሚያደርገውን ብቻ ለማድረግ በርሱ ላይ መታመን ያሻል። ክርስቶስ እንደወደደን እንድንዋደድ (ዮሐ. 13፡34፤ 15፡12) እና አእምሮ ሁሉ ለክርስቶስ እንዲገዛ የታዘዘበት (2ኛ ቆሮ. 10፡5)፥ ከፍተኛ ደረጃ ያላቸው የዚህ ዘመን ትእዛዛት ያለ መንፈስ ቅዱስ እርዳታ አይቻሉም። በተመሳሳይ ሁኔታ፥ ሌሎች የመንፈሳዊ ሕይወት መገለጫዎች ማለት እንደ መንፈስ ፍሬዎች (ገላ. 3፡22-23)፥ “ሁልጊዜ ደስ ይበላችሁ፥ ሳታቋርጡ ጸልዩ” (1ኛ ተሰ. 5፡16-17) እና “ሰሁሉ አመስግኑ፥ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ እናንተ ነውና” (1ኛ ተሰ. 5፡18)የሚሉት እሳሶች ሰው በመንፈስ ካልተመላለሰ በቀር ለማድረግ የማይቻሉት ናቸው።
ክርስቲያን ኃጢአት በሞላበት ዓለምና የማያቋርጥ ክፉ ተጽዕኖ ባለበት ሁኔታ ውስጥ ስለሚኖር፥ በመንፈሳዊ ሕይወት ክፍተኛ ደረጃ ላይ ለመድረስ በጣም ያስቸግረቸዋል (ዮሐ. 17፡15፤ ሮሜ 12፡2፤ 2ኛ ቆሮ. 6፡14፤ ገላ. 6፡14፤ 1ኛ ዮሐ. 2፡15)። በተመሳሳይ ሁኔታ ክርስቲያን በሰይጣን ተቃውሞ ይደርስበታል። ከዚህ የእግዚአብሔር ጠላት ጋርም በማያቋርጥ ውጊያ ውስጥ ነው (2ኛ ቆሮ. 4፡4፤ 11፡14፤ ኤፌ. 6፡12)።
ክርስቲያን ከዓለምና ከሰይጣን ከሚመጣበት ተቃውሞ በተጨማሪ፥ በውስጡም ጠላት አለበት። ያም አሮጌውን ሰው ወደ አለመታዘዝ ሕይወት ሊመልሰው የሚሻ ኃጢአታዊ ተፈጥሮ ነው (ሮሜ 5፡21፤ 6፡6፤ 1ኛ ቆሮ. 5፡5፤ 2ኛ ቆሮ. 7፡1፤ 10፡2-3፤ ጎሳ. 5፡16-24፤ 6፡8፤ ኤፌ. 2፡3)። ኃጢአታዊው ተፈጥሮ ክርስቲያን ውስጥ ካለው አዲስ ተፈጥሮ ጋር የማያቋርጥ ውጊያ ሰለሚያደርግ፥ እርሱን ድል ለማድረግ የሚቻለው፥ ሁል ጊዜ በእግዚአብሔር መንፈስ ላይ በመታተዝ ብቻ ነው። ለዚህ ነው ምንም እንኳን አንዳንዶች ክርስቲያን ወደ ኃጢአት የዕሽ ፍጹምነት ይደርሳል ብለው በተሳሳተ ሁኔታ ሲገልጡ፥ ይህ ኃይል ሰሕይወት ውስጥ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ያከናውን ዘንድ የአማኙ ባለማቋረጥ በመንፈስ ቅዱስ መመላለስ አስፈላጊ የሚሆነው። በአካልና በመንፈስ ፍጹም የመሆኑ ነገር በሰማይ ነው አማኙን የሚጠብቀው፤ ስለሆነም እስከሞት ወይም እስከመነጠቅ ድረስ መንፈሳዊ ውጊያው ይቀጥላል።
እነዚህ እስካሁን የተመለከትናቸው እውነቶች አንድ ክርስቲያን መንፈስ ቅዱስ ሕይወቱን እንዲቆጣጠርና እንዲመራው በመፍቀድ በርሱ ኃይልና ምሪት መመላለስ ያለበት መሆኑን የሚያመለክቱ ናቸው።
ሐ. በመንፈስ የመሞላት ውጤቶች
አንድ ሰው ራሱን ለእግዚአብሔር አሰረክቦ በመንፈሰ ቅዱሰ በሚሞላበት ጊዜ የሚከተሉት እጅግ አስደናቂ ውጤቶች በሕይወቱ ይታያሉ።
1. በመንፈስ ቅዱስ ኃይል የሚመላለስ ክርስቲያን የሚያድግ እና የመንፈስ ቅዱስ ፍሬዎች የሚታዩበት የሕይወት ቅድስና ይታይበታል (ገላ. 5፡22-23)። ይህ ሕይወት የመንፈስ ቅዱስ ኃይል በአማኝ ላይ የመሥራቱ ምሳሌያዊ መገለጫ ነው። የመንፈስ ቅዱስ ኃይል መገለጫ ብቻ ሳይሆን፥ አማኝ ወደፊት በሰማይ ክርሰቶስን በመምሰል ለሚገለጥበት ወቅት ምድራዊ ዝግጅት ነው።
2. ከመንፈስ ቅዱስ ዋና ዋና አገልግሎቶች አንዱ፥ ለአማኙ መንፈሳዊ እውነትን ማስተማር ነው። አማኝ የእግዚአብሔርን ቃል ፍፁም እውነት ሊረዳ የሚችለው፥ በመንፈስ ቅዱስ ምሪትና አብርሆት ብቻ ነው። የእግዚአብሔር መንፈስ ለአንድ ሰው የድነትን እውነት ለመግለጥ አስፈላጊ የመሆኑን ያህል (ዮሐ. 16፡7-11)፥ ክርስቲያኑንም ወደ እውነት ሁሉ ይመራዋል (ዮሐ. 16፡12-14)። የእግዚአብሔር ጥልቅ ነገሮች እና በመንፈስ ቅዱስ የተማረ ሰው ብቻ የሚረዳው እውነት፡በመንፈሰ ለሚመላለስ ሰው ብቻ ነው የሚስጠው (1ኛ ቆሮ. 2፡9-3፡2)።
3. መንፈስ ቅዱስ እንድኝ ክርስቲያን ሊመራና የእግዚአብሔርን ቃል አጠቃላይ እውነት ክርስቲያኑ ላለበት ልዩ ሁኔታ ሊያውለው ይችላል። ሮሜ 12፡2 ውስጥ “የእግዚአብሔር ፍቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ” ሲል ይህንኑ ማለቱ ነበር። ብሉይ ኪዳን ውስጥ እንደነበረው የአብርሃም አገልጋይ ክርስቲያንም “እኔ በመንገድ ሳለሁ እግዚአብሔር መራኝ” (ዘፍጥ. 24፡27) ማለትን ሊለማመድ ይችላል። ይህ ዓይነቱ አመራር ከእግዚአብሔር መንፈስ ጋር ተገቢው አንድነት ባላቸው ክርስቲያኖች የታወቀ ልምምድ ነው (ሮሜ 8፡14፤ ገላ. 5፡18)።
4. የድነት ሦስትና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ከሚኖር አንድነት ሦሚገኝ ሌላ ጠቃሚ ውጤት ነው። በሮሜ 8፡16 መሠረት የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን ያ መንፈስ ራሱ ከመንፈሳችን ጋር ይመሰክራል” (ይህን አባባል ከገላ. 4፡6፤ 1ኛ ዮሐ. 3፡24፤ 4፡13 ጋር ያነጻጽሩት)። ክርስቲያን ስለ ደኅንነቱ እርግጠኛነት ሊኖረው የሚገባ መረዳት ልክ አንድ ሰው በአካል ስለመኖሩ እርግጠኛ የመሆኑን ያህል ነው።
5. አንድ ሰው እግዚአብሔርን ለማፍቀርናለርሱ ለመስገድ የሚችለው፥ በመንፈስ ቅዱስ ሲመላለስ ነው። ኤፌሶን 5፡18 ውስጥ ከተጠቀሰው ምክር ቀጥሎ ያሉት ምንባቦች የሚገልጡት፥ ትከከለኛውን አምልኮና ከእግዚአብሔር ጋር ሊኖር የሚገባን አንድነት ነው። ከእግዚአብሔር ጋር አንድነት የሌለው ሰው ባማረ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ቢያመልክና ሥርዓቶችን ሲፈጽም፥ እግዚአብሔርን በእውነት እመለከ ማለት እይደለም። እምልኮ ክርክስቶስ ላሳምራዊቱ ሴት “እግዚአብሔር መንፈስ ነው፥ የሚሰግዱለትም በመንፈስና በእውነት ሊሰግዱለት ያስፈልጋቸዋል” (ዮሐ. 4፡24) እንዳለው ከልብ የሚሆን ነገር ነው።
6. በእንድ አማኝ ሕይወት እጅግ ጠቃሚ ከሆኑ ነገሮች እንጂ ከጌታ ጋር በጸሎት አማካይነት ያለው ንድነት ነው። የእግዚአብሔር መንፈስ ጸሎትን ሲያግዝና ሲመራ፥ ጸሎት ሥርዓት ያለውና ትክክለኛ ይሆናል። ጸሎቱ በእግዚአብሔር ቃል መሠረት እንዲሆን ከተፈለገም ቃሉ ሊጠና ይገባል። መንፈስ ቅዱስ ካልረዳ በቀር እውነተኛ ምስጋናና አምልኮ አይቻልም። አማኝ ከሚያቀርበው ጻሉት በተጨማሪ መንፈስ ቅዱስም እንደሚማልድለት ሮሜ 8፡26 ይገልጣል። ብርቱ የጸሎት ሕይወት የሚገኘው በመንፈስ ቅዱስ ከመመላለስ ነው።
7. እስካሁን ከተጠቀሱት መንፈሳዊ ብቃቶች በተጨማሪ፥ የአማኙ የአገልግሎት ሕይወት፥ የተፈጥሮና የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎቹ ልምምዶች በአጠቃላይ ከመንፈስ ቅዱስ ኃይል የሚገኙ ናቸው። ክርስቶስ ይህን በተመለከተ ዮሐንስ 7፡38-39 ውስጥ ሲጠቅስ፥ የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ከሰው ልብ የሚወጣና እንደሕያው ውኃ ምንጭ የሚፈስ መሆኑን አስገንዝቧል። ስለዚህ አንድ ክርስቲያን ታላላቅ የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች ሊኖሩት፥ ነገር ግን በመንፈስ ቅዱስ ኃይል የማይመላለሰ በመሆኑ ሊጠቀምባቸው የማይቻለው ይሆን ይሆናል። በአንጻሩ ደግሞ ጥቂት መንፈሳዊ ስጦታዎች ያሏቸው ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ኃይል በመመላለሳቸው እግዚአብሔር በጣም የሚጠቀምባቸው ሊሆኑ ይችላሉ። ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ሙላት የሚያስተምረውን ክርስቲያን በሚገባ ሊረዳ፥ በተግባር ሊተረጉመው፥ ሊጠቀምበት የሚገባ በጣም አስፈላጊ የሆነ እንዱ እውነት ነው።
ምንጭ፡- “ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ ጭብጦች” መጽሐፍ በዶክተር ሉዊስ ስፔሪ ቼፈር የተጻፈ እና በተክሉ መንገሻ የተተረጎመ ነው፡፡ እግዚአብሔር ስለ እነዚህ ቅዱሳን ድንቅ ስራ የተመሰገነ ይሁን፡፡ ማሳሰቢያ፡- ይህን ጽሁፍ መቀየርም ሆነ ለሽያጭ ማዋል በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡