የሕይወት እንጀራ

ኦሪት ዘፍጥረት

ዘፍጥረት 37-50 የዮሴፍ ታሪክ

የዚህ የኦሪት ዘፍጥረት የመጨረሻ ክፍል ዓላማ የእስራኤል ሕዝብ የከነዓንን ምድር ይወርሱ ዘንድ ቃል የተገባላቸው ሆነው ሳሉ፥ እንዴት ወደ ግብፅ እንደወረዱ ማሳየት ነው። ለኦሪት ዘጸአትም በመግቢያነት የሚያገለግል ነው። ምክንያቱም ኦሪት ዘጸአት እስራኤላውያን በግብፅ 400 ዓመታት ከቆዩ በኋላ ወደ ተስፋይቱ ምድር ለመመለስ እንዴት እንደወጡ የሚያሳይ መጽሐፍ ነው። ታሪኩ የተፈጸመው በሙሴ ዘመን ገደማ ስለሆነ፥ ከሌሎቹ የእስራኤል አባቶች ታሪክ […]

ዘፍጥረት 37-50 የዮሴፍ ታሪክ Read More »

ዘፍጥረት 25-36 የይስሐቅና የያዕቆብ ታሪክ

እስካሁን ድረስ በኦሪት ዘፍጥረት ጥናታችን ውስጥ ሁለት ዋና ዋና ክፍሎች እንዳሉ ተመልክተናል። በመጀመሪያ፥ ከአይሁድ ሕዝብ አጀማመር በፊት ያሉትን ጊዜያት በአጭሩ የሚያካትተውን – ከዘፍጥ. 1-11 ያለውን ክፍል፥ በሁለተኛ፥ ደረጃ ደግሞ የአይሁድ ሕዝብ ራስ የሆነውን የአብርሃምን ታሪክ የሚያሳየውን – ከዘፍጥ. 12-24 ተመልክተናል። በተጨማሪ ለአብርሃም በተአምራት የተወለደለትን ይስሐቅ የተባለውን ልጁን ታሪክ መመልከት ጀምረናል። ዛሬ ደግሞ የአብርሃም ልጅና የልጅ

ዘፍጥረት 25-36 የይስሐቅና የያዕቆብ ታሪክ Read More »

የአብርሃም ታሪክ (ዘፍጥረት 12-24)

ዛሬ የኦሪት ዘፍጥረትን ሁለተኛ ዋና ክፍል ማጥናት እንጀምራለን። ዘፍጥረት በሁለት ዋና ዋና ክፍሎች እንደሚመደብ መመልከታችንን ታስታውሳለህ። ዘፍ. 1-11 የሚያተኩረው ከእስራኤል አባቶች በፊት በነበረው ዘመን ላይ ሲሆን፥ ዘፍ. 12-50 ደግሞ አራቱን የእስራኤል ዋና ዋና አባቶች ታሪክ ያሳየናል። እነርሱም፡- አብርሃም፥ ይስሐቅ፥ ያዕቆብና ዮሴፍ ናቸው። በዛሬው ትምህርታችን የአይሁድ ሕዝብና በእግዚአብሔር ላይ እውነተኛ እምነት ያላቸው ሰዎች ሁሉ አባት የሆነውን

የአብርሃም ታሪክ (ዘፍጥረት 12-24) Read More »

ዘፍጥረት 4-11 የኃጢአት በመላው ዓለም መሠራጨት

ከዘፍጥረት 4-11 ባለው ክፍል ውስጥ ሦስት ዋና ዋና ክንዋኔዎች አሉ። አንደኛ፥ አዳምና ሔዋን የመጀመሪያውን ክፋትና ኃጢአት ከሠሩበት ሰዓት ጀምሮ መስፋፋቱንና ከእነርሱ በኋላ የሚመጡትን ዝርያዎቻቸውን በሙሉ ማጥፋቱን ቀጠለ። ሁለተኛ፥ ከአዳም ጀምሮ እስከ አብርሃም ድረስ ያለውን የድነት (ደኅንነት) መስመር ማሳየት ነው። ሦስተኛው፥ እንደ ዓለም ፈቃድ መኖርን ትተው በእግዚአብሔር ፊት በጽድቅ የኖሩ የተለያዩ ሰዎችን ማሳየት ነው።  ፩. ኃጢአትና

ዘፍጥረት 4-11 የኃጢአት በመላው ዓለም መሠራጨት Read More »

የአዳምና የሔዋን ኃጢአት (ከዘፍ. 3)

የውይይት ጥያቄ፥ ከዘፍ. 3 በሰው መጀመሪያ ኃጢአት በተሳተፉት ላይ የደረሰባቸውን እርግማን ዘርዝር። ዘፍ. 3 ስለ ሰው የመጀመሪያ ኃጢአት ይናገራል። ይህም በእግዚአብሔር ላይ የፈጸመው የመጀመሪያው ዓመፅ ነበር። እግዚአብሔር በመጀመሪያ አዳምና ሔዋንን ሲፈጥር፥ በሥነ- ምግባር ፍጹም ነበሩ። የኃጢአት ተፈጥሮ ስለሌላባቸው ኃጢአት ሊያደርጉ የሚችሉበት ምክንያት አልነበረም። ምሁራን ይህንን «የንጽሕና ደረጃ» ብለው ይጠሩታል፤ ምክንያቱም በዚህ ጊዜ አዳምና ሔዋን ኃጢአት

የአዳምና የሔዋን ኃጢአት (ከዘፍ. 3) Read More »

ዘፍጥረት 1-2 የዓለም አፈጣጠር

መጽሐፍ ቅዱስ የሳይንስ ማስተማሪያ ወይም የታሪክ መጽሐፍ አይደለም። መጽሐፍ ቅዱስ ሳይንስንም ሆነ ታሪክን የሚመለከት መረጃ የያዘ ቢሆንም ዓላማው ግን ይህ አይደለም። የመጽሐፍ ቅዱስ ዓላማ እግዚአብሔር ራሱንና ፈቃዱን ለሰው ልጅ መግለጥ ነው። እግዚአብሔር ዛሬም ቢሆን ለሰው ልጆች የሚናገርበት ዋናው መንገድ መጽሐፍ ቅዱስ ነው። አንዳንዱ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት መረጃ ሳይንስንና ታሪክን የሚመለከት ጉዳይ ቢኖረውም፥ ሳይንስና ታሪክ መርምረው

ዘፍጥረት 1-2 የዓለም አፈጣጠር Read More »

የኦሪት ዘፍጥረት ታሪክ ቅደም ተከተልና አስተዋጽኦ፣ ልዩ ባሕሪያት እና ዓላማ

የኦሪት ዘፍጥረት ታሪክ ቅደም ተከተልና አስተዋጽኦ የውይይት ጥያቄ፥ የሚከተሉትን ጥቅሶች ተመልከት ዘፍ. 2፡4፤ 5፡1፤ 6፡9፣ 10፡1፤ 11፡10፤ 11፡27፤ 25፡12፤ 25፡19፤ 36፡1፥ 9፤ 37፡2። ሙሴ፡- «የ…..ታሪክ ይህ ነው» የሚላቸውን የተለያዩ ነገሮችን ዘርዝር። ሙሴ ኦሪት ዘፍጥረትን በሚጽፍበት ጊዜ ግልጽ የሆነ አስተዋጽኦ ነበረው። መጽሐፉን ያቀናበረው «የ…ይህ ነው» በሚሉት ቃላት ዙሪያ ነበር። ብዙ ምሁራን ይህንን አከፋፈል የኦሪት ዘፍጥረትን አስተዋጽኦ

የኦሪት ዘፍጥረት ታሪክ ቅደም ተከተልና አስተዋጽኦ፣ ልዩ ባሕሪያት እና ዓላማ Read More »

የኦሪት ዘፍጥረት መግቢያ

የውይይት ጥያቄ፥ «ዘፍጥረት» የሚለውን ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ውስጥ ተመልከት። ስለ ጸሐፊው፥ ስለ ተጻፈበት ዓላማና ስለ መጽሐፉ አስተዋጽኦ ያገኘኸው ነገር ምንድን ነው? ከብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ውስጥ ልናጠናቸውና ልንረዳቸው ከሚገቡን እጅግ ጠቃሚ መጻሕፍት አንዱ ዘፍጥረት ነው። ብዙ ክርስቲያኖች በዘፍጥረት ውስጥ የሚገኙትን ታሪኮች ቢያውቁም እንኳ አብዛኛዎቹን ጥልቅ ትምህርቶች ግን አያጠኗቸውም። የዚህ መጽሐፍ ዓላማ ዘፍጥረትን በጥልቀት ማጥናት

የኦሪት ዘፍጥረት መግቢያ Read More »