ቤተ ክርስቲያን፡- ዓላማና ተልእኮዋ

በአሁኑ ዘመን እግዚአብሔር በቤተ ክርስቲያን አማካይነት ጥበቡንና ጸጋውን ለሰማያዊ ሠራዊት በመግለጥ ላይ ነው (ኤፌ. 3፡10)። ቤተ ክርስቲያን የእግዚአብሔር ጸጋ ምን ሊሠራ እንደሚችል ለመግለጥ ምስክር ሆና ትቀርባለች (ኤፌ. 2፡7)። በዚህ ጠለቅ ባለ አገላለጥ መሠረት የቤተ ክርስቲያን መለኮታዊ ተልእኮ ከአጠቃላዩ አካል ይልቅ ለእያንዳንዱ አማኝ የተሰጠ ነው። እንደ ቤተ ክርስቲያን ራስነቱ ክርስቶስ እያንዳንዱን አማኝ በጌታ ፈቃድ መንገዶች የመምራት ብቃት አለው። ይህ የሚሆነው ከግል ስጦታዎቹና እግዚእብሔር ለግሰሰቡ ሕይወት ካለው ዓላማ ጋር በተስማማ መልኩ ነው። ይህ ሁሉ ታዲያ እግዚእብሔር በአሁኑ ዘመን ለቤተ ክርስቲያን ካለው እጠቃላይ ዓሳማ ጋር በመስማማት ይካሄዳል። ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በአጠቃላይ እግዚአብሔር የአሁኝ መለኮታዊ ዓላማውን ሰመፈጸም ላይ ሲሆን፥ ይህም ልክ በቅዱሳት መጻሕፍት እንደተጻፈው በመከናወን ላይ ነው፡፡ 

ሀ. ዓለም ውስጥ የአሁኑ መለኮታዊ ዓላማ 

የዚህ ዘመን መለኮታዊ ዓላማ ዓለምን መለወጥ አይደለም። ይልቁንም በኢየሱስ ክርስቶስ አምነው የክርስቶስን አካል፥ ማለትም ቤተ ክርስቲያንን የሚመሠርቱ ሰዎች መጥራት ነው። ዓለም የምትለወጥና በምድር ላይ የጽድቅ መንግሥት የሚመሠረት መሆኑ እውነት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን ይህ እውነት በክርስቲያን አገልግሎት የሚመጣ አይደለም። ይህ የሚፈጸመው ክርስቶስ ሲመላስና የእርሱ በአካል መገኘትና የዓለምን ሥርዓት በመለወጥ ኃይሉ በግልጥ በሚሠራበት ወቅት ነው። 

የሰማይ አምላክ በምድር ላይ ዘላለማዊ መንግሥት የሚመሠርተው (በዳን. 2፡44-45)፥ የክርስቶስ ተምሳሌት ያለው ድንጋይ መፈንቀል የሚያመለክተው አሳብ ፍጻሜ ካገኘ በኋሳ ነው። ጌታ ተመልሶ ከክብር ዙፋኑ ላይ ከተቀመጠ በኋላ ሰቀኙ የሚቆሙ በጎቹን ወደተዘጋጀላቸው ምድራዊ መንግሥት ይመራቸዋል (ማቴ. 25፡31-34)። በተመሳሳይ ሁኔታ፥ ክርስቶስ በምድር ላይ ለሺህ ዓመታት የሚነግሠው ከሰማይ ሲመጣ በግልጥ ከታየ ሰኋላ ነው (ራእይ 19፡11-20፡9ን ከሐዋ. 15 ፡13-19፤ 1ኛ ቆሮ. 15፡20-25 ጋር ያነጻጽሩት)። 

የዚህን ዘመን ልዩ ገጽታዎች አስመልክቶ (ማቴ. 13፡1-50) ጌታችን ሦስት ዓበይት ሁኔታዎችን ገልጧል፡- (1) እስራኤል በዓለም ያላት ስፍራ ለእርሻ ውስጥ እንደተሸሽገ መዝገብ ይሆናል (ማቴ. 13፡44)፤ (2) ክፋት እስከ ዘመኑ ፍጻሜ ይቀጥላል (ማቴ. 13፡4፥ 25፥ 33+ 48)፤ (3) በስንዴ፥ የከበረ ዋጋ ባላት ዕንቁና በመልካም ዓሣ የተመሰሉት የመንግሥት ልጆች ይሰበሰባሉ (ማቴ. 13፡30፥ 45፥ 46፥ 48)። 

– ከነዚህ ሦስት የዘመኑ ባሕርያት የመጨረሻው ወይም የመንግሥት ልጆች መሰባሰብ በአሁኑ ዘመን የእግዚአብሔር ዋነኛ ዓላማ መሆኑ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት ሮሜ 11፡25 ውስጥ እንደተገለጠው፥ የአሁኑ ዘመን የእስራኤል ዕውርነት የሚቆየው፥ እስከ ቤተ ክርስቲያን ዘመን ፍጻሜ (ኤፌሶን 1፡22-23ን ተመልከት)፥ ማለትም እግዚአብሔር አሕዛብን እየጠራበት ያለው ልዩ የበረከት ዘመን እስከሚያበቃ ብቻ ነው። 

እንደዚሁም “የዓመፅ ምሥጢር” ወይም በአሁኑ ዘመን የሚታየው ክፋት የእግዚአብሔር መንፈስ ስፍራ እስኪሰቅለት ድረስ ማዕቀብ ያሰበት ቢሆንም፥ የሚቀጥል መሆኑ ተገልጧል (2ኛ ተሰ. 2፡7)። መንፈስ ቅዱስ የሚሄደው የቤተ ክርስቲያንን ጥሪ ከፈጸመ በኋላ ብቻ እንደመሆኑ፥ የእግዚአብሔር ቀጣይ ዓላማ በዓለም ክፋትን ማሻሻል ሳይሆን፥ የሚያምኑትን ሁሉ መለየት ነው። የእስራኤል ቃል ኪዳኖች ገና ይፈጸማሉ (ሮሜ 11፡27 ፥ ክፋት ከምድር ይወገዳል (ራእይ 21፡1)። የአሁኑ የእግዚአብሔር ዓላማ ቤት ክርስቲያንን ወደ ሙላቱ ማድረስ ነው። 

ሐዋርያት ሥራ 15፡13-19 ውስጥ እንደተገለጠው፥ የያዕቆብ ንግግር ፍሬ አሳብ ኢየሩሳሌም ውስጥ በተካሄደው የመጀመሪያ ጉባኤ ፍጻሜ ላይ ተብራርቷል። ጉባኤው የተጠራው ከአሁኑ የእግዚአብሔር ዓሳማ ጋር በሚመሳሰለው ጥያቄ ላይ ውሳኔ ለመስጠት ነበር። በመጀመሪያይቱ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በብዛት የሚገኙት አይሁዶች በመሆናቸው፥ ይህ አዲስ ወንጌል ወደ አሕዛብ መድረሱን እየተመለከቱ አይሁድነታቸው ምን የተለየ ነገር እንዳለው ግራ አጋብቷቸው ነበር። ያዕቆብ የጴጥሮስን ልምምድ በመመርኮዝ ጴጥሮስ አሕዛብ በነበረው ቆርኔሌዎስ ቤት በመገኘት ያከናወነው ነገር የሚያመለክተው፥ እግዚአብሔር ሕዝብን ለራሱ ይሰበስብ ዘንድ መጀመሪያ አሕዛብን በመጎብኘት ላይ እንዳለ የሚያሳይ ነው ብሏል። ያዕቆብ ከዚያ በኋላ፥ ጌታ እንደሚመለስና ለእስራኤልም ሆነ ለአሕዛብ ዓላማዎቹን ሁሉ እንደሚያሟላ በመግለጥ ንግግሩን ቀጥሏል። 

ይህ ሁሉ ጥናት ለዚህ ጉዳይ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ቢኖር፥ በአሁኑ ዘመን ግለሰብ አማኝ ዓለምን ለማሻሻል በእግዚአብሔር ያልተሾመ መሆኑን ነው። የአማኝ መጠራት ለክርስቶስና ለሚያድን ጸጋው በዓለም ሁሉ ምስክር ይሆን ዘንድ ነው። በዚህ የወንጌል ስብከት አገልግሎት አማካይነት ነው የእግዚአብሔር መንፈስ የዘመኑን ድንቅ ዓላማ ከግቡ የሚያደርሰው። 

ለ. የቤተ ክርስቲያን አመሠራረት 

ኢየሱስ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያኑን እንደሚመሠርት ተንብዮ ነበር (ማቴ. 16፡18)። ሐዋርያው ጳውሎስም ቤተ ክርስቲያንን “ሕንጻ ሁሉ እየተጋጠመ በጌታ ቅዱስ ቤተ መቅደስታ ወደ መሆን ከሚያድግበት ሕያው ድንጋይ ጋር አነጻጽሯታል። “በእርሱም እናንተ ደግሞ ለእግዚአብሔር መኖሪያ ለመሆን በመንፈስ ቅዱስ አብራችሁ ትሠራላችሁ” (ኤፌ. 2፡21-22)። የአማኙ የነፍሳት ምርኮኛ የክርስቶስን አካል የማነጹ አገልግሎትም የሚቀጥል ይሆናል። ይህ ለዘላለም ሳይሆን “ሁላችን የእግዚአብሔርን ልጅ በማመንና በማወቅ ወደሚገኝ አንድነት፥ ሙሉ ሰውም ወደ መሆን፥ የክርስቶስም ሙላቱ ወደሚሆን ወደ ሙላቱ ልክ እስክንደርስ ድረስ ነው (ኤፌ. 4፡13)። የክርስቶስ የሙላቱ ልክ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው፥ ሰዎች ክርስቶስን ወደ መምሰል ማደጋቸውን ሳይሆን፥ የክርስቶስ እካል ወደ ፍጻሜው ማደጉን ነው (ኤፌ. 1፡22-23)። ኤፌሶን 4፡16 ውስጥም የአካሉ ክፍሎች ልክ እንደ ሰብአዊ አካል ሕያው ሕዋሳት፥ የማያቋርጥ የነፍሳት ምርኮ ተግባር እንደሚፈጽሙና በዚህም አካሉን የሚያሳድጉ የመሆኑ እውነት ተገልጧል። 

ሐ. የአማኙ ተልእኮ 

ክርስቶስ የዚህ ዘመን መግለጫ በሆነው ዙር የመዝራት ምሳሌ፥ ከእራቱ እጅ እንዱ “ስንዴን እንደሚያስገኝ ተንብዮአል (ማቴ. 13፡1-23)። ምንም እንኳ የወንጌሉ ስብከት ከሕይወትም ሆነ ከሞት ጋር የሚዛመድ ቢሆን (2ኛ ቆሮ. 2፡16)፥ የእግዚአብሔር ልጅ የሆነ እማኝ የጠፉትን ለመመለስ በጊዜውም አለጊዜውም እንዲተጋ ተልኳል። እምነት ከመስማት፥ መስማትም ከእግዚአብሔር ቃል እንደሆነ በመገንዘብ (ሮሜ 10፡17)፥ ወደ ዓለም ሁሉ እኝዲሄድና ለፍጥረት ሁሉ ወንጌልን እንዲሰብክ ተሹሟል (ማር. 16፡15)። በተጨማሪም፥ ሰከርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ዮነበረው እግዚአብሔር የማስታረቅን ቃል የሰጠን መሆኑ 2ኛ ቆሮንቶስ 5፡19 ውስጥ ተገልጧል። እንግዲህ እግዚአብሔር በእኛ እንደሚማልድ ስለ ክርስቶስ መልእክተኞች ነን፤ ከእግዚአብሔር ጋር ታረቁ ብለን ስለ ክርስቶስ እንለምናለን” (2ኛ ቆሮ. 5፡20)። 

ይህ አገልግሎት አማኞች ሁሉ ሊፈጽሙት የሚገባና፥ በብዙ መንገዶች ተግባር ላይ የሚውል ነው። 

1. ወጎጌልን ለዚሁ ዓላማ ስምንሰጠው ገንዘብ አማካይነት ላልዳነ ሰው ማሰራጨት ይላል። ነፍሳትን ለክርስቶስ ለመማረክ የሚሹ ትጉህ አማኞች መኖራቸው የተረጋገጠ ቢሆንም፥ ለዚህ ዓላማ ከፍጻሜ መድረስ የሚፈለግባቸውን የገንዘብ ስጦታ ለማቅረብ ደግሞ ቸል የሚሉ መኖራቸውም እውን ነው። መልእክተኛው እስካልተላከ ድረስ አያሄድም። የሚልከውም በመሄድ ከሚያገለግል ጋር ዘላለማዊ ብድራትን ይካፈላል። 

2. ወንጌል ላልዳነ ሰው የጸሎት መልዕ ህኖ ሊቀርብ ይችላል። “ማናቸውንም ነገር በስሜ ብትለምኑ እኔ አደርገዋለሁ” (ዮሐ. 14፡14) ያለው ጌታ ለጸሎት መልስ በመስጠት ሠራተኞችን ወደ መከሩ እንደሚልክ የሚያረጋግጥ ነው። የእግዚአብሔር ልጅ ለሆነ አንድ አማኝ ከጸሎት የላቀ ፍሬያማ እገልግሎት እንደሌለ በቀላሉ ተረጋግጧል። በዚህ አገልግሎት ነፍሳት እንደሚድኑ የሚገነዘቡ ግን በጣም ጥቂት ብቻ ናቸው። 

3. ወኝጌል ላልዳነ ሰው በቃል ሊቀርብለት ይችላል። ሁሉም ለዚህ ተግባር የተላኩ እንደመሆናቸው፥ የሚከተሉትን ነገሮች በሚገባ ማስተዋል ወሳኝ ነው። (ሀ) መልእክተኛው መንፈስ ቅዱስ በሚያኖረው ስፍራ ሁሉ ለመሆን መፍቀድ አለበት፤ (ላ) እንዲያውጅ የተሾሙባቸውን የጸጋ ወንጌል እውነቶች መማር አለበት! (ሐ) በመንፈስ ቅዱስ መሞላት አለበት። ይህ ካልሆነ ለሚጠፉ ነፍሳት ምርኮ አገልግሎት ያለ ፍርሃትና ያለ ድካም እንዲነሣሣ የሚገፋፋ ፍቅር ሊኖረው አይችልም። ክርስቶስ፥ “መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ … ምስክሮቼ ትሆናላችሁ” (ሐዋ. 1፡8) ብሏል። ይህ የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ከሌለ፥ ወንጌሉን የመመስከር አደራ አይኖርም። በመንፈስ ቅዱስ የተሞላ አማኝ ግን መለኮታዊ ርኅራኄ ከውስጡ እየፈሰሰ ዝም ሊል አይችልም (ሐዋ. 4 ፡20)። 

4. በተጨማሪም ወንጌል እንደ ሥነ-ጽሑፍ፥ ሬድዮ፥ ቴሌቪዥንና መንፈሳዊ መዝሙሮች በመሳሰሉት መንገዶች ሊቀርብ ይችላል። ዘዴው ምንም ይሁን ምን፥ እውነቱ መንፈስ ቅዱስ በሚገለገልበት መንገድ ሁሉ ሊቀርብ ይገባል። 

5. እግዚአብሔር ወንጌልን ለማሰራጨት በሌሎች ብዙ መንገዶች እንደሚጠቀም ጥርጥር የለውም። ምንም እንኳ እያንዳንዱ ክርስቲያን ወንጌልን በቀጥታ በመስበክ እኩል ስኬታማ ባይሆንም፥ ወንጌል ለሰው ሁሉ መሰበኩን በማረጋገጡ ረገድ የሚጋራው ኃላፊነት አለ፡፡

ምንጭ፡- “ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ ጭብጦች” መጽሐፍ በዶክተር ሉዊስ ስፔሪ ቼፈር የተጻፈ እና በተክሉ መንገሻ የተተረጎመ ነው፡፡ እግዚአብሔር ስለ እነዚህ ቅዱሳን ድንቅ ስራ የተመሰገነ ይሁን፡፡ ማሳሰቢያ፡- ይህን ጽሁፍ መቀየርም ሆነ ለሽያጭ ማዋል በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡

Leave a Reply

Discover more from

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading