ቤተ ክርስቲያን፡- የክርስቶስ አካልና ሙሽራ፥ የሚጠብቃት ሽልማቷ

ሀ. ሰባቱ የክርስቶስና የቤተ ክርስቲያኑ ተምሳሌቶች 

በክርስቶስና በቤተ ክርስቲያን መካከል ያለውን ግንኙነት ለመግለጥ፥ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሰባት ተምሳሌቶች ተጠቅሰዋል። 

1. መዝሙር 23 ውስጥ የተመለከተው የእረኛና የበግ ተምሳሌት ዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 10 ውስጥ ክርስቶስ እረኛ፥ በርሱ የሚያምኑ ደግም በጎች ህንኩ ስተለኩሰት ክፍል ተጠቅሷል። ከዚህ ምንባብ እንደምንመለከተው፡- (ሀ ክርስቶስ የመጣው በበሩ፥ ማለትም በተወሰነው በዳዊት የዘር ሐረግ አማካይነት ነበር፥ (ለ) እርሱ በጎች የሚከተሉት እውነተኛ እረኛ ነው፥ (ሐ) ክርስቶስ የበጎች በር፥ ማለትም ወደ ድነትም ሆነ ወደ ዋስትና የሚገባበት በር ነው (ዮሐ. 10፡28-29)፣ (መ) ምግብና ሕይወት ለበጎቹ በእረኛው አማካይነት ይቀርባል፥ (ሠ) ከእውነተኛው እረኛ ጋር ሲነጻጻሩ፥ ሌሎቹ እረኞች ለበጎች ሕይወታቸውን የማይሰጡ ቅጥረኞች ናቸው፥ (ረ) በእረኛውና በበጎቹ መካከል ኅብረት አለ። አባት ልጁን እንደሚያውቀውና ልጅም አባቱን እንደሚያውቀው፥ ሰጎቹ እረኛቸውን ያውቁታል፥ (ሰ) ምንም እንኳ በብሉይ ኪዳን ዘመን እስራኤል ሌላ መንጋ የነበረች ብትሆን፥ በአሁኑ ዘመን ያለው መንጋና እረኛ ግን አንድ ብቻ ነው። ይህ ነው እይሁዳውያንም ሆኑ አሕዛብ ድነትን የሚያገኙበት አንድ መንገድ (ዮሐ. 10፡16)፥ (ሸ) ክርስቶስ በእረኛነቱ ነፍሱን ሰጎች አሳልፎ መስጠት ብቻ ሳይሆን፥ ይማልድላቸውና መንፈሳዊ ሕይወት ብሎም የሚያስፈልጋቸውን ምግብ ይሰጣቸው ዘንድ ዘላለም በሕይወት ይኖራል (ዕብ. 1፡25)። መዝሙር 23፡1 ውስጥ፥ “እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፥ የሚያሳጣኝም የለም” ይለዋል። 

2. ክርስቶስ እውነተኛው የወይን ግንድ ሲሆን፥ እማኞች ደግም ቅርንጫፎች ናቸው። ምንም እንኳ ብሉይ ኪዳን ውስጥ እስራኤል በወይን ምሳሌነት ከእግዚአብሔር ጋር የተዛመደች ብትሆን፥ ዮሐንስ ምዕራፍ 15 ውስጥ እንደተገለጠው፥ ክርስቶስ እውነተኛው የወይን ግንድ፥ አማኞች ደግሞ የወይኑ ቅርንጫፎች ናቸው። ምሳሌው ከክርስቶስ ጋር የሚደረገውን ኅብረትና አንድነት ያመለክታል። ከክርስቶስ ጋር በዚህ የማይቋረጥ ግንኙነት እንዲኖሩ ተመከረዋል (15፡10)። በርሱ የመኖር ውጤቶች ደግሞ መንጻት ወይም መገረዝ (ቁ.2)፥ ፍሬያማ ጻሎት (ቁ.7)፥ ዘላቂ ደስታ (ቁ, 11) እና ዘላለማዊ እውነት ናቸው (ቁ, 16)። የወይኑ ግንድና የቅርንጫፎቹ ማዕከላዊ እውነት፥ አንድ እማኝ እውነተኛ የወይን ግንድ ከሆነው ክርስቶስ ጋር ሕያው ግንኙነት ካልኖረው በክርስትና ሕይወት ደስ የማይሰኝ ወይም በአገልግሎቱ ፍሬያማ የማይሆን መሆኑ ነው። 

3. ክርስቶስ የማዕዘን ድንጋይ ሲሆን፥ ቤተ ክርስቲያን በሕንጻው ያሉ ድንጋዮችን ይዛለች። እስራኤል ቤተ መቅደስ ውስጥ ታመልክ ከነበረበት የብሉይ ኪዳን ዘመን ጋር ሲነጻጸር (ዘፀ. 25፡8)፥ ቤተ ክርስቲያን ራሷ ቤት መቅደስ ነች (ኤፌ. 2፡21)። በዚህ ምሳሌ ክርስቶስ የማዕዘኑ ራስ ድንጋይ ሲሆን፥ እማኞች ደግሞ የሕንጻው ድንጋዮች ሆነው ተጎልጠዋል (ኤፌ. 2፡19-22)። የአሁኑ ዘመን የእግዚአብሔር ዓሳማ፥ ቤተ ክርስቲያንን ማነጽ ነው (ማቴ. 16፡18)። ቤተ ክርስቲያንን እንደ ሕንጻ በመገንባቱ ሂደት ውስት፥ እያንዳንዱ ድንጋይ የመለኮታዊ ባሕርይ ተካፋይ በመሆኑ ሕያው ድንጋይ ነው (1ኛ ጴጥ. 2፡5)። ክርስቶስ የማዕዘኑ ራስና መሠረት ሲሆን (1ኛ ቆሮ. 3፡11፤ ኤፌ. 2፡20-22፤ 1ኛ ጴጥ. 2፡6)፥ ሕንጻው በጠቅላላው “ለእግዚአብሔር መኖሪያ ለመሆን በመንፈስ” ይሠራል (ኤፌ. 2፡22)። በሕንጻው ምሳሌ መሠረት፥ እያንዳንዱ አማኝ የማዕዙ ራስና መሠረት በሆነው ክርስቶስ ላይ መደገፉ ግልጥ ነው። በተመሳሳይ ሁኔታ፥ የሕንጻው ድንጋዮች እማኞች ሲሆኑ፥ በነርሱ መደጋገፍና በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት የእግዚአብሔር መቅደስ የሆነው ሕንጻ የሚሠራ መሆኑ ተገልጧል። 

4. በአዲስ ኪዳን ክርስቶስ ሊቀ ካህን፥ አማኞች ደግም ኋማኝካህናት” ሆነው ተገልጠዋል። ቀደም ሲል በዚህ መጽሐፍ ጥናታችን ውስጥ እንደተገለጠው፥ እማኝ ካህን” አራት መሥዋዕቶችን ያቀርባል፤ (ሀ) ራሱን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለእግዚአብሔር በማቅረብ፥ የመሥዋዕትነትን አገልግሎት ይሰጣል (ሮሜ 12፡1-2)። (ለ) ለእግዚአብሔር ምስጋናና ውዳሴ በማቅረብ፥ የአምልኮን አገልግሎት ይሰጣል (ዕብ. 13፡15)። ይህም የምልጃንና ለራሱ ችግሮች መጻለያን ያካትታል (ሮሜ 8፡26-27፤ ቆላ . 4፡12፤ 1ኛ ጢሞ. 2፡1፤ ዕብ. 10፡19-22)። ክርስቶስ ጎልጎታ ላይ የፈሰሰ ደሙን ይዞ እንደ ሊቀ ካህናችን ወደ ሰማይ ገብቷል (ዕብ. 4፡14-16፤ 9፡24፤ 10፡19-22)። አሁን ስለ እኛ በመማለድ ላይ ነው (ሮሜ 8፡34፤ ዕብ. 7፡25)። 

አማኞች እንደ ንጉሣዊ የክህነት አባላት፥ (ሐ) የሰናይ ምግባራትና (መ) የቁሳዊ ነገሮች መሥዋዕት ከማቅረብ ባሻገር፥ ሰውነታቸውን እንደ ሕያውና ቅዱስ መሥዋዕት አድርገው ማቅረብ ያስባቸው መሆኑን መገንዘቡ መልካም ነው (ዕብ. 13፡16)። 

5. ክርስቶስ የቤተ ክርስቲያን ራስ ቤተ ክርስቲያን ደግም እንደ አካል ተደርገው የተገለጡት ምሳሌ በአሁኑ ዘመን የሚሠራውን የእግዚአብሔርን ዓላማ ያሳያል። ይህ ምሳሌ ሰፋ ብሎ ለብቻው በዚሁ ምዕራፍ ወደኋላ ይቀርባል። 

6. ክርስቶስ እንደ መጨረሻው አዳም፥ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ አዲስ ፍጥረት ሆና በተለጠችበት ምሳሌ፥ ክርስቶስ ከሞት በመነሣቱ የአሮጌው ሥርዓት ራስ የነበረውን አዳምን ይተካዋል፤ አዲስ ፍጥረት ለሆኑትም ራስ ይሆናል። ምሳሌው በክርስቶስ ትንሣኤ እርግጠኛነትና በትንሣኤው ባዋቀረው አዲስ ሥርዓት ላይ የተመሠረተ ነው። በአዳም ውስጥ ከመሆን ጋር ሲነጻጸር፥ አማኝ በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት አማካይነት ክርስቶስ ውስጥ መሆኑ ተገልጧል። ባገኘው አዲስ ስፍራ አማካይነትም ክርስቶስ በርሱ ምትክ ጽድቅና አዲስ ሕይወት ለመስጠት ባከናወነው ነገር ሁሉ ተካፋይ ይሆናል። ክርስቶስ የአዲሱ ፍጥረት ራስ ስለሆነ፥ አዲስ የመታሰቢያ ዕለት ማለት በአሮጌው ሥርዓት ይከበር የነበረው የሰንበት ዕለት ተነጻጻሪ የሆነ መታሰቢያ የሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን አስፈላጊ ሆኗል። 

7. ክርስቶስ እንደ ሙሽራ፥ ቤተ ክርስቲያን ደግም እንደ ሙሽሪት መገለጣቸው ለአሁኑም ሆን ወደፊት በክርስቶስና በቤተ ክርስቲያኑ መካከል ለሚኖረው ግንኙነት ትንቢታዊ ምሳሌ ነው። ብሉይ ኪዳን ውስጥ ታማኝነትን እንዳጎደሰች ሚስት ከተገለጠችው እስራኤል በተነጻጻሪነት፥ ቤተ ክርስቲያን በአዲስ ኪዳን የሙሽራዋን መምጣት እንደምትጠባበቅ ሙሽሪት ተገልጣለች። ይህ በዚህ ምዕራፍ ውስጥ በስፋት የምንመለከተው እሳብ ይሆናል። ቤተ ክርስቲያን እንደ ክርስቶስ አካል የተገለጠችበት ምሳሌ የአሁኑን ዘመን የእግዚአብሔር ዓላማ የሚገልጥ ሲሆን፥ የክርስቶስ ሙሽራ የመሆኗ አሳብ ደግሞ ወደፊት ቤተ ክርስቲያን ከክርስቶስ ጋር የሚኖራትን ግንኙነት የሚያመለክት ነው። 

ለ. ቤተ ክርስቲያን እንደ ክርስቶስ አካል 

ቀደም ሲል የተመለከትነው የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት፥ የአዲስ ኪዳንን የቤተ ክርስቲያን መገለጥ በማጣመር የክርስቶስን አካል መሥርቷል። ይህም 1ኛ ቆሮንቶስ 12፡13 ውስጥ እንደተገለጠው፥ በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት አማካይነት የተከናወነ ነው፤ “አይሁድ ብንሆን፥ የግሪክ ሰዎችም ብንሆን፥ ባሪያዎችም ብንሆን ጨዋዎችም ብንሆን፥ እኛ ሁላችን በአንድ መንፈስ አንድ አካል እንድንሆን ተጠምቀናል። ሁላችንም አንዱን መንፈስ ጠጥተናል።” በዚህ ገለጣ ሦስት ዓበይት እውነቶች ቀርበዋል፤ (1) ቤተ ክርስቲያን ራሷን የምታንጽ አካል ናት፥ (2) የአካሉ ክፍሎች ልዩ ልዩ ስጦታዎች የተሰጧቸውና፥ ለልዩ አገልግሎት የተሾሙ ናቸው፤ (3) አካሉ ሕያው አንድነት ነው። 

1. ቤተ ክርስቲያን ራሷን የምታንጽ አካል እንደመሆኗ መጠን፥ ኤፌሶን 4፡11-16 ውስጥ እንደተገለጠው መንፈሳዊ ስጦታዎች ያሏቸውን ግለሰቦች ታካትታለች። በዚሁ መሠረት አንዳንዶቹ ሐዋርያት፥ ሌሉች ነቢያት፥ ወንጌላውያን፥ ወይም መጋቢያንና አስተማሪዎች ናቸው። ማዕከላዊው እውነት አማኞች በተለያዩ ችሎታዎች እግዚአብሔርን እንዲያገለግሉ መሰረታታቸው ብቻ ሳይሆን፥ እግዚአብሔር የሰጣቸውን እንድ ሁነኛ ተግባር ያከናውኑ ዘንድ ብቃት የተሰጣቸው መሆኑ ነው። አንድ አማኝ ተገቢውን አገልግሎት የሚፈጽመው፥ በክርስቶስ አካል ውስጥ የተወሰነለትን ተግባር ሲወጣና የክርስቶስን እካል ፍጹም በማድረጉ ክንውን ተካፋይ ሆኖ ሲገኝ ነው (ኤፌ. 4፡13)። 

2. የክርስቶስ አካላት እንደየስጦታቸው የተወሰነ እገልግሎት እላቸው። በሰው ሰውነት ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ የእካል ክፍሎች ልዩ ልዩ ተግባራትን እንደሚያከናውኑ ሁሉ፥ የክርስቶስ አካል ክፍሎችም እንዲሁ ናቸው። እያንዳንዱ አማኝ እግዚአብሔር የትኛውን ስጦታ እንደሰጠው ለማወቅ ራሱን በጥንቃቄ ሊመረምርና ስጦታውን ለእግዚአብሔር ከብር ሊያውለው ይፃባል። ዋና ዋናዎቹ የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች ሮሜ 12፡3-8 እና 1ኛ ቆሮንቶስ 12፡28 ውስጥ ተገልጠዋል። አማኞች ሁሉ መንፈሳዊ ስጦታዎች ያሏቸው ሲሆን፥ ከአንድ በላይ ስጦታዎች ያሏቸውም አሉ። አንዳንዴ የሚዛመዱበት ሁኔታ ቢኖርም፥ መንፈሳዊ ስጦታዎች ከተፈጥሮ ችሉታ ጋር መደናገር አይኖርባቸውም። ለምሳሌ አንድ ሰው በተፈጥሮው የማስተማር ብቃት ሊኖረው ይችላል። መንፈሳዊ ነገሮችን የማስተማር ስጦታ የሚሰጠው ግን ከእግዚአብሔር ብቻ ነው። 

መንፈሳዊ ስጦታዎችን ፈልጎ ማግኘት አይቻልም። ዳሩ ግን “መንፈስ እንደሚፈቅድ ለእያንዳንዱ ለብቻ እያካፈለ ያደርጋል” (1ኛ ቆሮ. 12፡11)። በሐዋርያት በተመሠረተች ቤተ ክርስቲያን ጀምረው እስካሁን ድረስ የቀጠሉ አንዳንድ ስጦታዎች አሉ። ሌሎች የምልክት ስጦታዎች ግን ከመጀመሪያው የክርስቲያኖች ትውልድ በኋላ ያበቁ ይመስላል። ያም ሆነ ይህ፥ እያንዳንዱ ስጦታ ለእግዚአብሔር ቃል ደንብ ሊገዛ ይገባል። ስጦታ እያንዳንዱ አማኝ የሚጠቀምበትና ኃላፊነት ያለበት ነገር እንጂ፡የትዕቢት መሠረት የሚሆን አገልግሉት አይደለም። 

እጥቢያ አብያተ ክርስቲያን ሰፋፊ አደረጃጀቶችን ቢያዋቅሩም፥ አካል እንደመሆኗ ሥራዋ የሚከናወነው በእያንዳንዱ አባል ችሎታ ላይ በመመሥረት እራሷ በሆነው ክርስቶስ አመራር ነው። አንድ አማኝ በተለይ ስጦታው ባልሆነ ተግባር ላይ እንዲሠማራ መጠየቁ ያለ ቢሆንም፥ ከፍተኛ ተግባሩ ግን በክርስቶስ አካል ውስጥ የተሰጠውን ሥራ ማከናወን ነው። ሕያው መሥዋዕት አድርጎ ራሱን ለጌታ ከሰጠ፥ የእግዚአብሔርን ፍጹም ፈቃድ ሊያውቅ ይችላል (ሮሜ 12 ፡1-2)። 

3. ቤተ ክርስቲያን በክርስቶስ ላንድ የጎችና የተመረጠች ሕያው አካል ናት። አይሁዶችን፥ እንዲሁም አሕዛብንና ከተለያየ ዘርና ባሕል የተሰበሰቡ ሰዎችን ያካተተ የቤተ ክርስቲያን አንድነት ኤፌሶን 1፡23፤ 2፡15-16፤ 3፡6፤ 4፡12-16፤ 5፡30 ውስጥ ተመልክቷል። ቤተ ክርስቲያን እንደ ክርስቶስ አካልነቷ ግሩም አንድነት ስላላት፥ በአይሁዶችና በአሕዛብ መካከል የሚኖረው ልዩነት ከግንዛቤ አይገባም፤ አይሁዶችም ሆኑ አሕዛብ እኩል ዕድልና ጸጋ ያገኛሉ። የክርስቶስ አካል የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር ከእስራኤልና ከአሕዛብ ጋር ከነለረው ግንኙነት ጋር ስትነጻጸር የተለየች ናት። ይህ ለአሁኑ ዘመን ብቻ የተወሰነ ልዩ ሁኔታ ነው። ኤፌሶን ምዕራፍ 3 እንደሚያስተምረን፥ የአካሉ ክፍሎች ከብሉይ ኪዳን ነቢያት ተሰውሮ የኖረውንና ለአዲስ ኪዳን አማኞች የተገለጠውን ድንቅ እውነት ይካፈላሉ። በዚህ መሠረት አሕዛብ በወንጌሉ አማካይነት በክርስቶስ በማመን እንደ አይሁዶች ሁሉ የአንድ አካል ክፍሎች ይሆናሉ (ኤፌ. 3፡6)። ኤፌሶን 4፡4-3 ውስጥ አጽንኦት የተሰጠው የአካል እንድነት ዘላለማዊነት አለው። በአሁኑ ዘመን ለክርስቲያናዊ ኅብረትና አገልግሎት፥ በሚመጣውም ዘመን ለዘላለማዊ ኅብረት መሠረቱ ይሄው አንድነት ነው። 

ሐ. ክርስቶስ እንደ ሙሽራ ቤተ ክርስቲያን እንደ ሙሽሪት 

ከሰባቱ የክርስቶስና የቤተ ክርስቲያን ተምሳሌቶች ትንቢታዊ ጠቀሜታ ያለው፥ የሙሽራውና የሙሽራይቱ ብቻ ነው። ታማኝነቷን ካጎደለችው የያህዌ ሚስት እስራኤል በተነጻጻሪነት ቤተ ክርስቲያን የሙሽራዋን መምጣት እንደምትጠባበቅ ድንግል ሙሽራ ሆና አዲስ ኪዳን ውስጥ ተጠቅሳለች (2ኛ ቆሮ. 11፡2)። የክርስቶስ ሙሽራነት ዮሐንስ 3፡29 ውስጥ በመጥምቁ ዮሐንስ ተገልጦአል። 

የዚህ ጉዳይ ዋና መገለጥ የተሰጠው ግን በክርስቶስ ያመኑ ባሎችና ሚስቶችን ተገቢ ግንኙነት በሚብራራበት ኤፌሶን 5፡25-33 ውስጥ ነው። በዚህ ስፍራ የክርስቶስ ሦስት ተግባራት ተገልጠዋል። ( ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን በመውደድ ነፍሱን ላርስዋ አሳልፎ ሰጥቷል (ቁ.25)። (ለ) በአሁኑ ጊዜ ክርስቶስ በውኃ መታጠብና ከቃሉ ጋር አንጽቶ” በመቀደስ ተግባሩ ላይ ነው (ቁ.26)። (ሐ) “እድፈት ወይም የፊት መጨማደድ ወይም እንዲህ ያለ ነገር ሳይሆንባት ቅድስትና ያለ ነውር ትሆን ዘንድ ክብርት የሆነችን ቤተ ክርስቲያን ለራሱ እንዲያቀርብ ፈለገ” (ቁ.27)። ክርስቶስ በመስቀል ላይ በመሞት ሙሽራ ለሙሽሪት የሚያቀርበውን የጥሎሽ ተምሳሌት ፈጽሟል። በእሁኑ ዘመን፥ የእግዚአብሔርን ቃል ከምእመናን ሕይወት ጋር በማዋሀድና በመቀደስ፥ ሙሽሪትን ለወደፊት ግንኙነቱ እያዘጋጃት ነው። ቤተ ክርስቲያን በምትነጠቅበት የመጨረሻ ዘመን፥ ሙሽራው ወደ ምድር መጥቶ ሙሽራይቱን ወደ ሰማይ ይወስዳታል፤ የራሱን ከብር እንድታንጸባርቅ ቤተ ክርስቲያንን ፍጹም፥ እድፍ ወይም ንድፍ የሌለባት፥ ለቅዱስ ሙሽራ የምትስማማ ቅድስት ሙሽሪት አድርጎ ያቀርባታል። ከዚያ የሚከተለው ቅዱሳን ሁሉ የሚያከብሩት የከርስቶስና የቤተ ክርስቲያን የጋብቻ በዓል ነው። በዓሉ የሚፈጸመው ምናልባት በሺህ ዓመቱ መንግሥት መንፈሳዊ ኅብረት ይሆናል። ይህ የጋብቻ በዓል ክርስቶስ መንግሥቱን ለመመሥረት ወደ ምድር በሚመለስበት ዋዜማ እንደሚሆን ራእይ 19፡7-8 ውስጥ ተጎልጿል። 

በዚህ ተምሳሌት አማካይነት የተገለጠውና ክርስቶስ ለቤተ ክርስቲያኑ ያለው ፍቅር የእግዚአብሔርን ከፍተኛ ፍቅር ያመለክታል። ከዚህ ተምሳሌት የመለኮታዊ ፍቅርን አምስት ሁኔታዎች ለመጥቀስ ይቻላል። 

1. የጸግዚአብሔር ፍቅር ዘላለማዊነት ቀሚመነጨው ናግዚአብሔር ፍቅር ነው ከሚለው እውነተኛ ትምህርት ነው (1ኛ ዮሐ. 4፡8)። እግዚአብሔር ለማፍቀር የቻለው በራሱ ጥረት ወይም ልምምድ አይደለም። ፍቅር የሚጎድለውም አይደለም። ይልቁንም ፍቅር የሕላዌው፥ የኑባሬው ወይም የርሱነቱ ዋነኛ ነገር ነው። ፍቅሩ መኖር የጀመረው እግዚአብሔር መኖር ሲጀምር ነው። ፍቅሩ የሚያበቃ ቢሆን፥ የእግዚአብሔር ማንነት ዋነኛ አካል ያበቃ ነበር። የእርሱ ማንነት የሚታወቀው ከታላቅ ፍቅሩ የተነሣ ነው። 

የእግዚአብሔር ፍቅር አይለወጥም። እስራኤላውያንን፥ በዘላለማዊ ፍቅር ወድጃችኋለሁ” ያላቸው ሲሆን (ኤር. 31 ፡3)፥ ስለ ክርስቶስም፥ በዚህ ዓለም ያሉትን ወገኖቹን የወደዳቸውን እስከ መጨረሻ ወደዳቸው” ተብሎ ተጽፏል (ዮሐ. 13፡1፤ 15፡9)። እግዚአብሔር ለአንድ ሰው ያለው ፍቅር ከፍ ዝቅ የሚል ወይም የሚቋረጥ አይደለም። 

2. የእግዚአብሔር ፉቅር ለማያቋርጥ ተግባሩ ማነሳሻ ነው። የእግዚአብሔር ፍቅር ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በውድ ልጁ መሥዋዕትነት አማካይነት የተገለጠ ቢሆንም (ሮሜ 5፡8፤ 1ኛ ዮሐ. 3፡16)። ይህ መሥዋዕት የሚገለጠው እግዚአብሔር ለሰዎች ያለውን ዘላለማዊ እሳብ ነው። ቁሳዊው ዓለም ከመፈጠሩ በፊት የእግዚአብሔርን ልብ ለማየት ችለን ቢሆን ኖሮ፥ ለዓለም ኃጢአት ለታረደው በጉ ያኔ የተደረጉ ልግስናዎችን ሁሉ ልንመለከት እንችል ነበር (ራእይ 3:6)። አሁንም የእግዚአብሔርን ልብ ለማየት ብንችል፥ ከድነት ርቀው ለጠፉት በልጁ ሞት አማካይነት የገለጠውን ርኅራኄ እንመለከታለን። የክርስቶስ ጊዚያዊ ሞት የመለኮታዊ ፍቅር መግለጫ ትርታ ሳይሆን፥ እግዚአብሔር ከድነት ርቆ ለጠፋው የሰው ልጅ አላለማዊና የማይለወጥ ፍቅሩን ያወጀበት ድርጊት ነበር። 

3. የእግዚአብሔር ፍቅር ግልዎና ንጹሕ ነው። ይህን የእግዚአብሔር ፍቅር ለመግለጥ የሚያስችሉ ሰብአዊ ቃላት አልተገኙም። በመለኮታዊ ፍቅር ውስጥ ከቶውንም ራስ ወዳድነት ስለሌለ፥ እግዚአብሔር በፍጹም ጥቅምን ለራሱ አይሻም። ምንም አይቀበልም፥ ሁሉን ይሰጣል። ሐዋርያው ጴጥሮስ አማኞች እርስ በርሳቸው ከልባቸው አጥብቀው እንዲዋደዱ መክሯቸዋል (1ኛ ጴጥ. 1፡22)። ይሁንና፥ ከበረከቶቹ ባሻገር እግዚአብሔርን ስለማንነቱ ብቻ የሚወዱት ስንቶች ናቸው? የእግዚአብሔር ፍቅር ከዚህ ምንኛ ልዩ ነው? እግዚአብሔር ገንዘባችንን፥ አገልግሎታችንን ወይም ተጽዕኖአችንን እንደሚፈልግ አድርገን በእርግጠኝነት እናስባለን። እግዚአብሔር እኛን እንጂ ከእኛ የሚፈልገው ነገር የለም። ፍጹም ፍቅሩም እኛን ካላገኘ አይረካም። “የተወደዱ” የሚለው ቃል አማኞችን አስመልክቶ ሲነገር ከፍተኛ የገላጭነት ኃይል አለው። ምክንያቱም አማኞች ከእግዚአብሔር ጋር ባላቸው ግንኙነት ዋናው ተግባራቸው መወደድ ነው። 

የእግዚአብሔር ፍቅር ለግልቀቱ ወስን የለውም። በእጽናፈ ዓለማችን እጅግ ውድ የሆነው ነገር የእግዚአብሔር አንድያ ልጅ ደም ነው። እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለምን በጣም ወደደ። ሰዎች “ኃጢአተኞች” እና የእግዚአብሔር “ጠላቶች” ሳሉ ልጁ ለእነርሱ መሠዋቱ ከገደብ ያለፈ ቢመስልም፥ ከዚህም የሚበልጥ” ፍቅር እንዳለ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል። ይህም በክርስቶስ ሞት ዕርቅን ሳገኙና ለጻደቁ ሁሉ እግዚአብሔር የሚያሳየው ፍቅር ነው (ሮሜ 5፡8-10)። በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ካለ የእግዚአብሔር ፍቅር የሚለየን ነገር የለም (ሮሜ 8፡29)። 

5. የግዚአብሔር ፍቅር የማያከትም በጎ ነገር አለው። እግዚአብሔር ኃጢአተኞችን ሳይቀር እንደሚወድ ከሚያሳየው ድንቅ እውነት ሌላ ይህች ዓለም ምንም ተስፋ የላትም። የእግዚአብሔር ፍቅር የስሜት ጉዳይ ሳይሆን በገቢር የሚገለጥ ነው። እግዚአብሔር ካታላቅ ፍቅሩ የተነሣ ለዘላለም ይጠፉ ዘንድ የሚገባቸው ኃጢአተኞችን ለመታደግ ድንቅ እርምጃን ወሰደ። ከፍጹምነቱ የተነሣ ጻድቅ ሰሆነ ፍርዱ የኃጢአተኞችን ኩነኔ ችላ ብሎ ሊያልፍ ባይችልም፥ ፍርዱ ፍጹም እንዲሆን የኃጢአተኞችን መርገም ሰራሱ መሸከም ነበረበት። (“ነፍሱን ስለ ወዳጆቹ ከመስጠት … የሚበልጥ ፍቅር ለማንም የለውም” (ዮሐ. 15፡13)። ይህን ያደረጎው የራሱን ቅድስና ሳይጎዳ ኃጢአተኞችን ለማዳን ይችል ዘንድ ነው (ሮሜ 3:26)። እግዚአብሔር በክርስቶስ የምትክነት ሞት አማካይነት ኃጢአተኞችን የሚያድንበት ነጻነት ስላሰው አሁን ያለ ምንም ውሱንነት ሰሰው ልጅ ሕይወት ይሠራል። ይህን የሚያደርገው፥ ፍጹም የሆነ ፍትህን በማሟላት ኃጢአተኞችን ታላቅ ወደሆነና ክርስቶስን ወደ መምሰል ደረጃ እስኪያደርሳቸው ነው። 

የሚያድን ጸጋ ከፍቅርም የሚልቅ ሲሆን፥ ነጻና ብርቱ የሆነ እግዚአብሔር በኃጢአተኛው ላይ የነበረውን የጽድቅ ብያኔ እንዲያልፍ የሚያደርግ መለኮታዊ ፍቅር ነው። “ጸጋው በእምነት አድኖአችኋል” (ኤፌ. 2፡8ን ከ2፡4 እና ከቲቶ 3፡4-5 ጋር ያነጻጽሩ)። 

እግዚአብሔር ለኃጢአት ከፍተኛ ጥላቻ ያለው አምላክ ነው። ይህም እንደ ፍቅሩ ሁሉ ኃጢአተኛውን ከወደቀበት አዘቅት እንዲያወጣ ይገፋፋዋል። በተመሳሳይ ሁኔታ፥ ይህ ኃጢአትን የመብላት ባሕርዩ ከፍቅሩ ጋር ተቀላቅሎ እግዚአብሔርን ልጁን የሚቀጣ አባት ያደርገዋል። “እኔ የምወዳቸውን ሁሉ እገሥጻቸዋለሁ እቀጣቸውማለሁ” (ራእይ 3፡19)። “ጌታ የሚወደውን ይቀጣዋልና” (ዕብ. 12፡6)። 

ከክርስቶስ ጋር ካለው ሕያው ጥምረት የተነሣ (1ኛ ቆሮ. 6፡17)፥ ክርስቶስ የተወደደውን ያህል አማኝ በአብ ተወዷል (ዮሐ. 17፡23)። ፍጹም ፍቅር በቅጣት ወይም በመከራ ጊዜ አይቀንስም። 

ከነዚህ ቀጥተኛ የእግዚአብሔር ፍቅር መገለጫዎች በተጨማሪ ብዙ ተዘዋዋሪ መገለጫዎችን ለመጥቀስ ይቻላል። አዲስ ኪዳን ውስጥ ስለ ሰብአዊ ፍቅር የተጻፈው በጣም ጥቂት ነው። መጽሐፉ የሚያተኩረው ከዚህ ይልቅ መንፈስ ቅዱስ የተሞላ አማኝ ብቻ ሰሚቀበለው መለኮታዊ የፍቅር ተካፋይነት ላይ ነው። ሮሜ 5፡5 የሚያስተላልፍልኝ መልእክት፥ በተሰጠን በመንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ፍቅር በልባችን የፈሰሰ መሆኑን ነው። መላኮታዊ ፍቅሩ የመንፈስ ፍሬ” ሰለሆነ (ገላ. 5፡22)፥ ምንጩ እርሱ ነው። በመሆኑም፥ መለኮታዊ ፍቅር በአማኙ ልብ ውስጥ በተለያየ መንገድ ይገለጣል። የአንደኛ ዮሐንስ መልእክት የሚያመለክተው ከእግዚአብሔር ከተወለድን፥ እግዚአብሔር እንደሚወድ የምንወድ መሆናችንን ነው። አንደኛ ቆሮንቶስ ምዕራፍ 13 ደግሞ ይህ ፍቅር ከሰብአዊነት የላቀ መሆኑን ይገልጣል። የማይገደበውን የእግዚአብሔር ፍቅር ያህል በዚህ ሕይወት የሚያስደስት ምንም ነገር የለም። 

እግዚአብሔርን ስለ ማፍቀር ጉዳይ ሳይሆን፥ ከእግዚአብሔር ስለሆነ ፍቅር ነው የምንመለከተው። ይህን ፍቅር አስመልክቶ እኝዳንድ ነገሮችን መመልከቱ ተገቢ ያሆናል። 

የእግዚአብሔር ፍቅር ክርስቶስ ካቀረበው ጸሎት የተነሣ የምንለማመደው ነው (ዮሐ. 17፡26)። እግዚአብሔር የጠፋውን ዓለም ይወዳል (ዮሐ. 3፡16፤ ኤፌ. 2፡4)። ክፉ የሆነውን የዓለም አሠራር ግን ይጠሳል (1ኛ ዮሐ. 2፡15-17)። እግዚአብሔር ያዳናቸውን ሰዎች ይወዳል (ዮሐ. 13፡34-35፤ 15፡12-14፤ ሮሜ 5፡8፤ ኤፌ. 5፡25፤ 1ኛ ዮሐ. 3፡16፤ 4 ፣ 12)። እግዚአብሔር የእስራኤልን ሕዝብ ይወዳል (ኤር. 31፡3)። ክርሱ የኮበለሉትንም ይወዳል (ሉቃስ 15፡4፥ 20)። ፍቅሩ ዘላለማዊ ነው (ዮሐ. 13፡1)። የእግዚአብሔር ፍቅር ልጁን እስኪሰጥ ድረስ መሥዋዕትን ጠይቆታል (1ኛ ዮሐ. 3፡16፤ 2ኛ ቆሮ. 8፡9፤ ኤፌ. 5፡2)። ከመለኮት በወጣ ምሥጢራዊ ርኅራኄ ሳቢያ፥ ሐዋርያው ጳውሎስ ለወንድሞቹ ማለትም በሥጋ ዘመዶቹ ለሆኑት፥ ከክርስቶስ ተለይቶ ለመረገም ፈቃደኛ ነበር (ሮሜ 9፡1-3)። 

በጸጋ ዘመን የመጀመሪያው የከርስቶስ ትእዛዝ በመላኮታዊ ፍቅር መመላለስ ነው (ዮሐ. 13፣ 34-35፤ 15፡12-14)። ይህም የእያንዳንዱ ክርስቲያን ከፍተኛ መለያ ሊሆን ይገባል (ገላ. 5፡13፤ ኤፌ. 4፡2፥ 15፤ 5፡2፤ ቆላ. 2፡2፤ 1ኛ ተሰ. 3፡12፤ 4፡9)። ከእግዚአብሔር የተቀበልነው መለኮታዊ ፍቅር በሥጋ ሊዳብርም ሆነ ሊገኝ አይችልም። ይህ ቀላሎቹን ቅድመ ሁኔታዎች አሟልተው በመንፈስ ቅዱስ የተሞሉ ክርስቲያኖች የታወቀ ልምምድ ነው (ገላ. 5፡22)። 

መ. ሙሽራይቱ አጊጣና ተሸልማ 

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከተጠቀሱት ብዙ ዓበይት ፍርዶች መካከል ቤተ ክርስቲያን ፍርድ የምትቀበልበትና የምትሸለምበት የክርስቶስ የፍርድ ወንበር አንዱ ነው። ኃጢአትን በተመለከተ ከጸጋ ሥር ያለ የእግዚአብሔር ልጅ ለፍርድ እንደማይቀርብ መጽሐፍ ቅዱስ ያስተምራል (ዮሐ. 3፡18፤ 5፡24፤ 6፡37፤ ሮሜ 5፡1፤ 8፡1፤ 1ኛ ቆሮ. 11፡32)። ክርስቶስ ለኃጢአት ሁሉ፥ ማለትም ላለፈው፥ ለአሁኑ ወደፊት ለሚሠራ (ቆላ. 2፡13) ፍጹም ተተኪ ሆኖ ስለተሠዋ፥ በእግዚአብሔርም ፊት የሚቆም ከመሆኑ የተነማ አማኝ ከኩነኔ ነጻ ሆኗል። በክርስቶስ በመሆኑም በርሱ ፍጹምነት የተነሣ ተቀባይነት ሳማግኘት (1ኛ ቆሮ. 1፡30፤ ኤፌ. 1፡6፤ ቆላ. 2፡10፤ ዕብ. 10፡14) እና እንደ ክርስቶስ በእግዚአብሔር ለመወደድ በቅቷል (ዮሐ. 17፡23)። ሆኖም ዕለታዊ ሕይወቱንና ለእግዚአብሔር የሚያቀርበውን አገልግሎት በተመለከተ፥ አማኝ በክርስቶስ የፍርድ ወንበር ፊት መልስ ይሰጣል (ሮሜ 14 ፡16፤ 2ኛ ቆሮ. 5፡10፤ ኤፌ.6፡8)። ይህ ክርስቶስ የርሱ የሆኑትን ለመቀበል በሚመጣበት ጊዜ የሚካሄድ ፍርድ ነው (1ኛ ቆሮ. 4፡5፤ 2ኛ ጢሞ. 4፡8፤ ራእይ 22፡12፤ ማቴ. 16፡27፤ ሉቃስ 14፡14)። 

ያላመኑ ሰዎች የመጨረሻ ፍርድ ለመቀበል በታላቁ ነጭ ዙፋን ፍርድ ፊት በሚቆሙበት ወቅት፥ “እንደየሥራቸው›› ብያኔ ይሰጣቸዋል (ራእይ 20፡11-15)። የዚህ ፍርድ ዓላማ እነዚያ ከነጩ ዙፋን ፊት የቆሙ ሰዎች መዳን አለመዳናቸውን መወሰን አይደለም። ይልቁንም ከድነት ርቀው የጠፉት ሰዎች ለጥፋታቸው ሊቀበሉት የሚገባን የፍርድ መጠን መወሰኝ ነው። በተመሳሳይ ሁኔታ፥ የዳኑትም ሰዎች በክርስቶስ የፍርድ ወንበር ፊት በሚቀርቡበት ጊዜ እንደየሥራቸው ይፈረድባቸዋል። ይህ ፍርድ መዳን አለመዳናቸውን የሚወስን ሳይሆን፥ እያንዳንዱ አማኝ ላበረከተው አገልግሎት የሚቀበለውን ወይም የሚያጣውን ሽልማት የሚያጸድቅ ነው። በክርስቶስ የፍርድ ወንበር ፊት የሚቆሙት አማኞች መዳንና በሠላም መጠበቅ ብቻ ሳይሆን፥ ፀደ መንግሥተ ሰማያት የተወሰዱ ናቸው። ይህ የሚሆነው በነርሱ ሰናይ ምግባር ላይ በመመሥረት ሳይሆን፥ በክርስቶስ የአዳኝነት ሥራ በተገኘው መለኮታዊ ጸጋ ነው። ሰጸጋ ሥር እስከሆነ ድረስ የአማኝ ሕይወትም ሆነ አገልግሎት ሁኔታ በምንም ዓይነት ዘላለማዊ ሕይወቱን አያሳውም፤ ሊያሳጣውም አይችልም። ስለሆነም፥ የርሱ የሆንንለትና የምናገለግለው ክርስቶስ በአማኙ ሕይወትና አገልግሎት ላይ መፍረዱ ከድነት የተለየ ነው። 

“በክብሩ ዙፋን ፊት” ለእስራኤልና ለሕዝቦቿ ለተደረገው በጎ ነገር ሽልማት ይሰጣል። ይህ ግን ከግላዊ የድነት ጉዳይ የራቀ ነው (ማቴ. 25፡31ን ከማቴ. 6፡2-6፤ 24:45-46፤ 25፡1-46 ጋር ያነጻጽሩ)። 

የአማኝ ሽልማቶች በክርስቶስ የፍርድ ወንበር ፊት ምን እንደሚመስሉ ላመግለጥ ሦስት ዓበይት ምሳሌዎች ተጠቅሰዋል። 

1. ሮሜ 14፡10-12 ውስጥ የተጠያቂነት ጉዳይ ተጠቅሷል። በዚህ ስፍራ ከሌሎች አማኞች ፍርድ ጋር በተያያዘ የሚከተለው ምክር ተለግሷል፡- “አንተም በወንድምህ ላይ ስል ምን ትፈርዳለህ? ወይስ አንተ ደግሞ ወንድምህን ስለ ምን ትንቃለህ? ሁላችን በክርስቶስ ፍርድ ወንበር ፊት እንቆማለንና። እኔ ሕያው ነኝ፥ ይላል ጌታ፥ ጉልበት ሁሉ ለእኔ ይንበረከካል መላስም ሁሉ እግዚአብሔርን ያመሰግናል ተብሎ ተጽፎአልና። 

እንግዲያስ እያንዳንዳችን ስለ ራሳችን ለእግዚአብሔር መልስ እንሰጣለን”። 

በዚህ ምንባብ የሌላውን ክርስቲያን የሥራ ጥራት ለመገምገም እንዳንጥር ታዘናል። ይህ ግን ኃጢአትን መገሠጽና መፍረድ የለብንም ማለት ሳይሆን፥ አሳቡ የሚያመለክተው የአማኙን ሥራ እሴት ወይም የሕይወቱን ጥራት ነው። ብዙውን ጊዜ ክርስቲያኖች በራሳቸው ግንዛቤ የራሳቸው ሕይወት የተሻለ መስሎ ይታይ ዘንድ ሌሎችን እጥብቀው ይተቻሉ። በሌላ አነጋገር፥ ራሳቸውን ከፍ ለማድረግ ሲሉ ሌላውን ይንቃሉ። 

በዚህ ምንባብ የተገለጠው እውነት፥ እያንዳንዱ አማኝ ለእግዚአብሔር መልስ የሚሰጥ መሆኑ ነው። ምሳሌው መጋቢን ወይም የማስተዳደር አደራ የተጣለበትን ሰው ይመሰክታል። አንድ ክርስቲያን በሕይወቱ ያገኘው ነገር ሁሉ ከእግዚአብሔር በስጦታ የተቀበለው ነው። ይህም ምሁራዊ ችሎታ፥ ተፈጥሮአዊ ስጦታ፥ አካላዊ ጤንነት፥ መንፈሳዊ ጸጋ፡ወይም ሀብት ሊሆን ይችላል። በዚህ ረገድ፥ ብዙ ከተሰጠው ብዙ ይጠበቅበታል። 1ኛ ቆሮንቶስ 6፡19-20 ውስጥ እንደተመለከተው፥ አማኞች “በዋጋ ተገዝታችኋልና የራሳችሁ አይደላችሁም” ተብለዋል። እግዚአብሔር ለሰጠን ነገር ሁሉ መጋቢዎች እንደመሆናችን፥ በክርስቶስ የፍርድ ወንበር ፊት ለግላችን ስለተሰጠን አደራ መልስ እንሰጣለን እንጂ ለሌሎች በተሰጣቸው ላይ አይደለም የሚፈረድብን። በፍርዱ ወቅት ዋናው ነገር ስኬት ወይም ዝና ሳይሆን፥ እግዚአብሔር ለሰጠን ነገር ታማኞች ሆነን መገኘታችን ነው። 

2. 1ኛ ቆሮንቶስ 3፡9-15 ውስጥ የእማኙ ሕይወት በክርስቶስ መሠረትነት ላይ እንደተገነባ ሕንጻ ተቆጥሯል። ይህን መልእክት በመረዳቱ ረገድ፥ የሚከተሉትን ነጥቦች ልብ ማለቱ ተገቢ ነው። 

(ሀ) ክፍሉ የሚያካትተው የዳኑትን ሰዎች ብቻ ነው። “እኛ” እና “እናንተ” የሚሉት ተውላጠ ስሞች የዳኑትን ሲያካትቱ ያልዳኑትን ያገላሉ። እንደዚሁም፥ «ማንም›› የሚለው ቃል ደግሞ የሚያመለክተው፥ በዓለቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ሕንጻውን የሚሠሩትን ብቻ ነው። 

(ለ) ሐዋርያው ጳውሎስ የቆሮንቶስ ሰዎች የዳኑበትን ወንጌልና የዳኑት የሚቆሙበትን ዓለት ካገለጠላቸው በኋላ፥ ራሱን መሠረት ከሚጥል ጠቢብ አናጺ ጋር ያነጻጽራል። ጠበቅ አድርጎ በማነጻጸርም እያንዳንዱ እማኝ ከእግዚአብሔር እንፏተሰጠው ጻጋ በመሠረቱ ላይ ላዕላይ መዋቅሩን በመሥራት ላይ መሆኑን ገልጧል። እያንዳንዱ አማኝ በዚያው መሠረት ላይ እንዴት እንደሚገነባ እንዲጠነቀቅ ነው ማስገንዘቢያው። አማኝ በእሳት የሚፈተን የአገልግሎት ወይም የሥራ ሕንጻ የሚገነባ መሆኑ ነው የተመለከተው። እሳቱ ያ አገልጋይ በጌታ ፊት ሲቀርብ የሚያርፉበት የጌታ ዓይኖች ሳይሆኑ አይቀሩም (ራእይ 1፡14)። 

(ሐ) አማኝ መሠረት በሆነው ክርስቶስ ላይ የሚገነባው ሥራ እሳት የሚበላው የእንጨት፥ የሣር ወይም የአገዳ ሊሆን ይችላል። ወይ ደግሞ እሳት የማይደፍረው የወርቅ፥ የብርና ከከበሩ ማዕድናት የተሠራ ሊሆን ይችላል። ወርቅና ብርን በተመለከተ እሳት ያጠራቸዋል እንጂ አይጎዳቸውም። 

(መ) በክርስቶስ ላይ ያነጸው “ሥራ” የሚጸናለት አማኝ ሽልማት ያገኛል። “ሥራው” የሚቃጠልበት ግን ምንም አያገኝም። የሚያጣው ሽልማቱን እንጂ በተፈጸመው የክርስቶስ ሥራ ያገኘውን ድነት አይደለም። ምንም እንኳን ሥራው በእሳት ውስጥ አልፎለት ባይሸለም እሱ ይድናል። 

3. 1ኛቆሮንቶስ 9፡16-27 ውስጥ በተለይም ከቁጥር 24-27 የክርስትናሕይወትንና አገልግሎትን ጥራት ለመግለት የውድድርና የሽልማት ምሳሌ ተሰጥቷል። ሐዋርያው የራሱን የወንጌል ሰባኪነት አገልግሎት በመጥቀስ፥ “እንግዲህ፥ ሽልማቴ ምንድነው?” ሲል ይጠይቃል። የዚህ ጥያቄ እውነተኛ መልስ የሚገኘው ለእግዚአብሔር ከሰው እገልግሎት ጥራት ነው። በመሆኑም፥ ሐዋርያው ጳውሎስ በሥራዎቹ የተገለጠውን ታማኝነት ይዘረዝራል (ቁ. 18-23)። የዚህን ዘገባ እውነተኛነት የሚክድ አይኖርም። ከዚያም ክርስቲያናዊ አገልግሎትን አማኞች ሁሉ ከሚካፈሉት የሩጫ ውድድር ጋር ያነጻጽረዋል፤ በውድድሩም ሽልማቱን የሚያገኘው ከፍተኛ ጥረት ያደረገው አንድ ሰው ብቻ ነው። 

በክርስቲያናዊ አገልግሉትም እንደዚሁ እማኙ ሙሉ ሽልማቱን ያገኝ ዘንድ ባሰው ጉልበት ሊጠቀም ይገባል፤ ሁሉንም መቅደም እንደሚገባው ቆጥሮ ሊሮጥ ይገባል። ሯጭ የሚጠፋን አክሊል ለማግኘት ሰአግባቡ መሮጥ እንዳለበት ሁሉ፥ ክርስቲያኑም የማይጠፋውን አክሊል ለማግኘት መትጋት አለበት። ሐዋርያው በማያገባና በተከፈለ አሳብ ሳቢያ የተጣላ እንዳይሆን ሥጋውን ሲገዛ የኖረ መሆኑ ተገልጿል። በዚህ ስፍራ የተጣልሁ እንዳልሆን” ተብሎ የተተረጎመው ቃል በግሪክኛ “ዶኪሞስ” የሚል እሉታዊ ፍች አለው። የዶኪሞስ” አዎንታዊ ፍች ተቀባይነት ማግኘት” ተብሎ ተተርጉሟል (ሮሜ 14፡18፤ 16፡10፤ 1ኛ ቆሮ. 11፡19፣ 2ኛ ቆሮ. 10፡18፤ 2ኛ ጢሞ. 2፡15)። የተጣልሁ እንዳልሆን” የሚለው “ተቀባይነትን እንዳላጣ” ተብሎ ሊተረጎም ይገባል። የሐዋርያው ድነት በምንም ዓይነት አጠያያቂ ስላልሆነ፥ ለዘላለም ከእግዚአብሔር እስያለሁ የሚል ሥጋት አልነበረበትም። እጎልግሎቱ ተቀባይነት እንዳያጣበት ነበር ፍርሃቱ። 

ለክርስቲያኑ የሚሰጠው ሽልማት እንዳንድ ጊዜ “ዋጋ” (ሽልማት) ሲባል (1ኛ ቆሮ. 9፡24)። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ “አክሊል” ተብሏል (1ኛ ቆሮ. 9፡25፤ ፊልጵ. 4፡1፤ 1ኛ ተሰ. 2፡19፤ 2ኛ ጢሞ. 4፡8፤ ያዕ. 1፡12፤ 1ኛ ጴጥ. 5፡4፤ ራእይ 2፡10፤ 3፡11)። እነዚህ አክሊሎች አምስት የተለያዩ ክርስቲያናዊ አገልግሎቶችንና መከራን በመወከል በአምስት ሊከፈሉ ይችላሉ። የእግዚአብሔር ልጅ የሆነ ክርስቲያን ሽልማቱን እንዳያጣ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶታል (ቆሳ. 2፡18፤ 2ኛ ዮሐ. 8፤ ራእይ 3፡11)። 

የሽልማቶች ትምህርት በጸጋ የሚገኘው ድነት አስፈላጊ አካል ነው። እግዚአብሔር የአማኙን ሰናይ ምግባር ለድነቱ ስለማይቆጥርለትና ሊቆጥርለትም ስለማይችል፥ የአማኙ መልካም ሥራዎች መለኮታዊ እውቅና ማግኘታቸው ተገቢ ነው። ድነትን ያገኘ ሰው በስጦታ ለተበረከተለት ሕይወት ለእግዚአብሔር የሚከፍለው የሰውም። ይሁንና ፍጹም በሆነ መሰጠት ለእግዚአብሔር የመኖር ዕዳ አለበት። ለዚህ ፍጹም መሰጠቱ ተስፋ የተገባለት ሽልማት ሰሰማይ ይጠብቀዋል። 

ለአማኙ የሚሰጡ ሽልማቶች በአክሊሎች ተምሳሌትነት ሊገለጡም ራእይ 4፡10 እንደሚለው፥ እክሊሎቹ በሰማይ አዳኝ በሆነው ክርስቶስ እግር ሥር ይጣሳሉ። እንግዲህ፥ በታማኝነት አገልግሎቱን ለተውጣ አማኝ የሚሰጠው ሽልማት ምን ይሆን? 

በምድር ላይ በታማኝነት ማገልገል በሰማይ መልካም የአገልግሎት ስፍራ የማግኘት ሽልማት ያለው ይመስላል። ራእይ 22፡3 እንደሚለው፥ ባሪያዎቹ ያገለግሉታል።* አማኞች የወደዳቸውንና ለነርሱ ራሱን የሰጠ ዳኛቸውን በፍቅር በማገልገል የላቀ እርካታ ያገኛሉ። ማቴዎስ 25፡14-3ዕ ውስጥ ክርስቶስ ስለ መክሊት ባቀረበው ማብራሪያ፥ እምስትና ሁለት መክሊቶችን የተቀበሉት ሰዎች (ጌታቸው የሰጣቸውን እጥፍ ያደረጉ)፥ የሚከተለውን ምስጋና አግኝተዋል፤ “መልካም፥ አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ በጥቂቱ ታምነሃል፥ በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ” (ማቴ. 25፡21፥ 23)። ይህ ፍርድ በቀጥታ ከቤተ ክርስቲያን ጋር የሚዛመድ ሳይመስልም። መመሪያው ዘላለማዊ ሽልማት ለሚያገኙ ለሁሉም ዘመን አማኞች ሊሠራ ይችላል። በዚህ ምድር ጌታን በታማኝነት ማገልገል በዘላሰሙ መንግሥት የተሻለ አገልግሎት እንድንሰጥ ያደርገናል። 

የክርስቶስን የፍርድ ወንበር ዋነኛ መልእክት የሚያስተላልፈው 2ኛ ቆሮንቶስ 5፡10-14፥ ከክርሰቶስ የፍርድ ወንበር ፊት ክፉ ሥራዎች ከደግ ሥራዎች እንደሚለዩ ይገልጣል። አማኙም በመልካም ሥራው ይሸለማል። ቀደም ሲል እንደተጠቀሰው፥ ፍርድ የሚሰጠው በኃጢአት ላይ አይደለም አማኙ ቀደም ብሎ ጸድቋልና። በአሁኑ ጊዜ ንስሐ ባልገቡ አማኞች ላይ ከሚሰጠው ቅጣት ጋር የተያያዘ ጉዳይም አይደለም (1ኛ ቆሮ. 11፡31-32፤ 1ኛ ዮሐ. 1፡9)፤ ምክንያቱም እማኝ በዚህ ወቅት በእግዚአብሔር ፊት ፍጹም ስለሆነ ነው። 

ስለዚህ፥ ቀሪው ብቸኛ ጉዳይ እግዚአብሔር የሚመዝነው የእማኙ የሕይወትና የአገልግሎት ጥራት ነው። አንድ ቀን እያንዳንዱ አማኝ ስለ ሕይወቱ መልስ ለመስጠት በእግዚአብሔር ፊት የመቆሙ እውነት ለአሁኑ ዘመን ታማኝነትን፥ ተገቢውን ግምገማና ከዘላለም እኳያ ቅድሚያ ለሚሰጣቸው ነገሮች ቅድሚያ የመስጠቱ ጉዳይ ሊበረታታ ይገባል።

ምንጭ፡- “ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ ጭብጦች” መጽሐፍ በዶክተር ሉዊስ ስፔሪ ቼፈር የተጻፈ እና በተክሉ መንገሻ የተተረጎመ ነው፡፡ እግዚአብሔር ስለ እነዚህ ቅዱሳን ድንቅ ስራ የተመሰገነ ይሁን፡፡ ማሳሰቢያ፡- ይህን ጽሁፍ መቀየርም ሆነ ለሽያጭ ማዋል በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡

Leave a Reply

Discover more from

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading