የድነት ዋስትና

በክርስቶስ ኢየሱስ የሚያምኑ ብዙ ሰዎች የድነት ዋስትና ያላቸው ስለመሆኑ እርግጠኞች ናቸው። ብዙ ጊዜ የሚነሣው ጥያቄ ግን፥ “አንድ ጊዜ የዳነ ሰው ድነቱን ሊያጣ ይችላልኝ?” የሚል ነው። ድነትን የማጣቱ ፍርኃት የአንድን አማኝ የአእምሮ ሠላም በከፍተኛ ደረጃ ስለሚጎዳና ለወደፊት ተስፋውም ወሳኝ ጉዳይ ስለሆ፥ ጥያቄው የድነት አስተምህሮ እጅግ ጠቃሚ ክፍል ነው። 

አንድ ጊዜ የዳነ ሰው ድነቱን ሊያጣ ይችላል የሚለው አሳብ የተመሠረተው፥ የድነት ዋስትናን አጠያያቂ በሚያስመስሉ የተወሰኑ የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባቦች ላይ ነው። በቤተ ክርስቲያን ታሪክ፥ ሁለት ተቃራኒ የአተረጓጎም ዘዴዎች ተከስተዋል። እነዚህም የዘላለማዊ የድነት ዋስትና አስተሳሰብን የሚደግፉ የካልቪን ትምህርት ተከታዮችና፥ ይህን ፅንሰ-አሳብ የሚቃወሙ የአርሜኒዮስ ትምህርት ተከታዮች የሚያስተምሯቸው አስተምህሮዎች ናቸው። 

ሀ. የአርሚኒያውያን የድነት ዋስትና አመለካከት 

የአርሜኒያውያንን አመለካከት የሚከተሉ ሰዎች በቅድመ ሁኔታዎች ላይ የተመሠረተ የዋስትና አስተምህሮን ያረጋግጣሉ ብለው ያመኑባቸውን ሰማኒያ አምስት ያህል የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች ዘርዝረዋል። ከነዚህም መካከል ይበልጥ ጠቃሚዎቹ የሚከተሉት ናቸው፡- ማቴዎስ 5፡13፤ 6፡23፤ 7፡16-19፤ 13፡1-8፤ 18፡23-35፤ 24፡4-5፥ 11-13፥ 23-26፤ 25፡1-13፤ ሉቃስ 8፡11-15፤ 11፡24-28፤ 12፡42-46፤ ዮሐ. 6፡66-11፤ 8፡31-32፥5 1፤ 13፡8፤ 15፡1-6፤ ሐዋ. 5፡32፤ 11፡21-23፤ 13፡43፤ 14፡21-22፤ ሮሜ 6፡11-23፤ 8፡12-17፤ 11፡20-22፤ 14፡15-23፤ 1ኛ ቆሮ. 9፡23-27፤ 10፡1-21፤ 11 ፡29-32፤ 15፡1-2፤ 2ኛ ቆሮ. 1፡24፤ 11፡2-4፤ 12፡21-13፡5፤ ገላ. 2፡12-16፤ 3፡4-4፡1፤ 5፡1-4፤ 6፡7-9፤ ቈላ. 1፡21-23፤ 2፡4-8፥ 18-19፤ 1ኛ ተሰ. 3፡5፤ 1ኛ ጢሞ. 1፡3-7፥ 18-20፤ 2፡11-15፤ 4፡1-16፤ 5፡5-15፤ 6፡9-12፥ 17-21፤ 2ኛ ጢሞ. 2፡11-18+ 22-26፤ 3፡13-15፤ ዕብ. 2፡1-3፤ 3፡6-19፤ 4፡1-16፤ 5፡8-9፤ 6፡4-20፤ 10፡19-39፤ 11፡13-16፤ 12፡1-17፥25-29፤ 13፡7-17፤ ያዕቆ. 1፡12-26፤ 2፡14-26፤ 4፡4-10፤ 5፡19-20፤ 1ኛ ጴጥ. 5፡9፥ 13፤ 2ኛ ጴጥ. 1፡5-11፤ 2፡1-22፤ 3፡16-17፤ 1ኛ ዮሐ. 1፡5-3፡11፤ 5፡4-16፤ 2ኛ ዮሐ. 6-9፤ ይሁዳ 5-12፥ 20-21፤ ራእይ 2፡7፥ 10-11 

17-26፤ 3፡4-5፥ 8-22፤ 12፡11፤ 17፡14፤ 21፡7-8፤ 22፡18-19። 

እነዚህን ምንባቦች ማጥናቱ አያሌ ጠቃሚ ጥያቄዎችን ያስነሣል። 

1. ይህን ጉዳይ አስመልክቶ መጽሐፍ ቅዱስን ዮሚተረጉምን ሰው የሚገጥመው ጠቃሚ ጥያቄ ምናልባት እውነተኛው አማኝ ማነው? ቀሚለው ይሆናል። ብዙ ሰዎች የዘላለማዊ ዋስትና አስተምህሮን የሚቃወሙት አንድ ሰው ድነትን ሳያገኝ የአእምሮ እምነት ሊኖረው ይችላል በማለት ነው። 

የዘላለማዊ ዋስትናን እሳብ የሚደግፉት ደግሞ አንድ ሰው በሕይወቱ ውጫዊ ለውጥ ሊታይ እንደሚችል ይስማማሉ። ሰውዬው የቤተ ክርስቲያን አባል በመሆን ወይም በመጠመቅ ክርስቶስን የመቀበል ውጫዊ እንቅስቃሴ ሊያሳይ፥ ከዚህም አልፎ በአኗኗሩ ላይ የተወሰነ ለውጥ ያሳይ ይሆናል፤ ዳሩ ግን በክርስቶስ እውነተኛ ድነት ላይኖረው ይችላል። 

የዳነውን ካልዳነው ለመለየት የሚያስችል ደንብ መዘርዘር ባይቻልም፥ በእግዚአብሔር አእምሮ ምንም ዓይነት አጠያያቂ ነገር እንደማይኖር ግልጥ ነው። አማኙ ከሁሉም በፊት ክርስቶስን እንደ አዳኙ የተቀበለ ለመሆኑ እርግጠኛ መሆን አለበት። በዚህ ረገድ ክርስቶስን መቀበል ስለ ድነት መንገድ የተወሰነ እውቀት ሊያካትት የሚችል የፈቃደኝነት ተግባር እንደሆነና፥ በተወሰነ ደረጃም በስሜት ሊገለጥ እንደሚችል መረዳቱ ጠቃሚ ነው። መሠረታዊው ጥያቄ ግን፥ “እውን ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኜ አድርጌ ተቀብያለሁን?” የሚለው ነው። ይህ ጥያቄ ታማኝ መልስ ካላገኘ፥ ለዘላለማዊ የድነት ዋስትናም ሆነ፥ ለድነት ማረጋገጫ ምንም ዓይነት መሠረት ሊኖር አይችልም። የዘላለማዊ ዋስትናን ፅንሰ- እሳብ የሚቃወሙ ሰዎች ለይስሙላ የሆነ እምነት ለማዳን አይችልም ይላሉ። የዘላለማዊ ዋስትና ደጋፊዎችም ይህን እሳብ ይደግፋሉ። እዚህ ላይ በአግባቡ የሚሰነዘረው ጥያቄ፥ በትክክል የዳነና የዘላለም ሕይወት ያገኘ ሰው ድነቱን ያጣል ወይ? የሚለው ነው። 

2. ዘላለማዊ ዋስትናን የሚቃወሙ ወገኖች የሚጠቅሷቸው ምንባቦች፥ ስለ ሰብአዊ ተግባራት ወይም ስለ ድነት መረጃ የሚናገሩ ናቸው። እውነተኛ ድነት ያገኘ ሰው በክርስቶስ ያገኘውን አዲስ ሕይወት በባሕርዩና በሥራ መግለጥ አለበት። ይሁንና፥ አንድን ሰው በሥራው መፍረድ ሊያታልል ይችላል። አንዳንድ ጊዜ ክርስቲያኖች ያልሆኑ ሰዎች በአንጻራዊነት ከክርስትና ሕይወት ሥነ-ምግባር ጋር የሚነጻጸር ተግባር ሊያከናውኑ ይችላሉ። በሌላ በኩል ደግሞ እውነተኛ ክርስቲያኖች የሆኑ አንዳንድ ሰዎች በሥጋዊነትና በኃጢአት ተጠምደው ድነትን ካላገኙ ሰዎች በማይለዩበት ሁኔታ ኃጢአት አዘቅት ውስጥ ይሰጥሙ ይሆናል። ሉቃስ 11፡24-26 ውስጥ የተጠቀሰው ዓይነት ሰዶ የግብረ ገባዊነት ተሐድሶ እውነተኛ ድነት እንዳልሆነና፥ ወደ ቀድሞው ሕይወት መመለስም ድነትን ማጣት እንዳልሆነ ሁሉም ይስማማሉ። 

ክርስቲያናዊ የእምነት ምስክርነት በፍሬው መረጋገጥ እንዳለበት አያሌ የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባቦች ያስገነዝባሉ። ከእግዚአብሔር የሆነ ድነት ሰተራ ሁኔታዎች ውስጥ እንኳን በፍሬው ምንነቱን ያስመሰክራል (ዮሐ. 8፡31፤ 15፡6፤ 1ኛ ቆሮ. 15፡1-2፤ ዕብ. 3፡6-14፤ ያዕ. 2፡14-26፤ 2ኛ ጴጥ. 1፡10፤ 1ኛ ዮሐ. 3፡10)። ይህም ሆኖ፥ ሁሉም ክርስቲያኖች፥ ሁልጊዜ የድነትን ፍሬዎች አያሳዩ ይሆናል። በመሆኑም፥ ድነት በሥራ መረጋገጥ እንዳለበት የሚናገሩ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች የአማኙን ዋስትና አስተምህሮ የሚቃረኑ እይደሉም። ዋናው ጥያቄ እግዚአብሔር ሰውዬውን እንደዳነ ይቆጥረዋል ወይ? የሚለው ነው። 

3. የአማኙን ዋስትና እልባነት ለማሳየት የተጠቀሱ ብዙ ምንባቦች፥ በክርስቶስ ዮማመኑ ጉዳይ ተራ ወይም የይምሰል እንዳይሆን ያስጠነቅቃሉ። አይሁዳውያን መሥዋዕቶችን የማቅረቡ ዘመን ስላለፈ ወደ ክርስቶስ እንዲመለሱ፥ ካልሆነ ግን እንደሚጠፉ አዲስ ኪዳን ውስጥ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል (ዕብ. 10፡26)። እንደዚሁም፥ ያልዳኑ አይሁዶችና አሕዛብ አብርሆትን ከሚሰጣቸውና ከሚለውጠው የመንፈስ ቅዱስ ሥራ “እንዳይወድቁ” ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል (ዕብ. 6፡4-9)። መንፈሳዊ ያልሆኑ አይሁዶች በሚመጣው መንግሥት ተቀባይነት እንደማይኖራቸው ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል (ማቴ. 25፡1-13)። ከእስራኤላውያን ቡድን አንጻር የአሕዛብ ቡድንም፥ ባለማመን ምክንያት በአሁኑ ዘመን ያሳቸውን የበረከት ስፍራ እንዳያጡ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል (ሮሜ 11፡21)። 

4. እንዳንድ ምንባቦች የሚያነሡት ክድነት ጥያቄ ይልቅ የሽልማትን ጉዳይ ነው። በክርስቶስ አምኖ የዳነ ሰው ሽልማቱን ያጣ ይሆናል (1ኛ ቆሮ. 3፡15፤ ቈሳ. 1፡21-23)። ለክርስቶስ የሰጠው አገልግሎትም ዋጋ አይኖረውም (1ኛ ቆሮ. 9፡27)። 

5. እውነተኛ ክርስቲያን በኃጢአት ምክንያት ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን ኅብረት ያጣ ይሆናል (2ኛ ዮሐ. 1፡6)። እንዲሁም ከድነቱ የተነሣ በዚህ ሕይወቱ ሊያገኛቸው የሚገባውን የመንፈስ ቅዱስ ፍሬ ማፍራትን (ገላ. 5፡22-23) እና ለክርስቶስ ውጤታማ አገልግሎት አበርክቶ እንደመርካት ያሉ መልካም ነገሮችን ይነፈጋል። 

6. እውነተኛ ታማኝ ለኮብላይነቱ፥ ልጅ በአባቱ እንደሚቀባ ሁሉ፥ ይቀጣ ይሆናል (ዮሐ. 15፡2፤ 1ኛ ቆሮ. 11፡29-32፤ 1ኛ ዮሐ. 5፡16)። ቅጣቱም እስከ ሥጋዊ ሞት ሊደርስ ይችላል። ይሁንና፥ ይህ ቅጣት የድነት ማጣት ምልክት ሳይሆን፥ አማኙ የሰማይ አባቱ የሚቀጣው የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን የሚያመለክት ነው። 

7. መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚለው፥ አንድ አማኝ ክጸጋ ይወድቅ ይሆናል (ገላ. 5 ፡1-4)። ይህ በአግባቡ ከተተረጎመ አማኝ ድነቱን የሚያጣ መሆኑን ሳይሆን፥ በአኗኗሩ ከጸጋ መመዘኛ እንደሚወርድና ወደ ሕግ ባርነት ሰመመለስ በክርስቶስ ያገኘውን እውነተኛ ነጻነት የሚያጣ መሆኑን ነው። ስለሆነም፥ አማኝ የሚወድቀው ከድነት ተግባር ሳይሆን፥ ከአኗኗር መመዘኛ ነው። 

8. ብዙ ችግር የሚመጣው፥ ያለአገባባቸው የሚጠቀሱ ምንባቦች በተለይም ከሌላ ሥፍራዘመን ጋር የሚዛመዱ ምንባቦችን ከመጥቀስ የተነሣ ነው። በአዲስ ኪዳን ትምህርት ላይ ተመሥርቶ እውነተኛ ዳግም ልደት ያገኘ የብሉይ ኪዳን ቅዱስ፥ የአሁኑን ዘመን ያህል ዋስትና እንዳሰው ለመገመት ቢቻልም፥ ብሉይ ኪዳን ስለ ዘላለማዊ ዋስትና ግልጥ አመለካከት አያስጨብጥም። ቢሆንም፥ ካለፈው ወይም ከሚመጣው ሥፍረ-ዘመን ጋር የሚዛመዱና እንደ ሕዝቅኤል 33፡7-8 ያሉ ምንባቦች በአገባባቸው መሠረት ሊተረጎሙ ይገባል። እስራኤላውያን ሕግን ሰመታዘዝ ስለሚያገኙት በረከትና፥ ባለመታዘዝ ስለሚደርስባቸው መርገም የሚናገረውን ዘዳግም 28ን የመሰሉ ዋና ዋና ምንባቦችም ጥንቃቄ ሊደረግላቸው ይገባል። ሌሎቹ ምንባቦች የሚያመለክቱት በመጨረሻው ዘመን የሚነሡትን ሐሰተኛና ዳግም ልደት ያላገኙ አሰተማሪዎችን ነው (1ኛ ጢሞ. 4፡1-2፤ 2ኛ ጴጥ. 2፡1-22፤ ይሁዳ 17-19)። እንዲህ ያሉ ሰዎች የስም ክርስቲያኖች ሲሆኑም፥ ዳግም የተወለዱ አይደሉም። 

9. የዋስትናን አለመኖር ለማገናዝብ ሲባል በስሕተት የተተረጎሙና ማቴዎስ 24፡13 ውስጥ ብስከ መጨረሻው የሚጸና እርሱ ግን ይድናል” የሚለውን የመሰሉ ብዙ ጥቅሶች ቀርበኞል። ይህ የሚያመለክተው፥ ከበደል ወይም ከኃጢአት መዳንን ሳይሆን፥ ከጠላቶችና ከስደት ነጻ መሆንን ነው። ከላይ የተመለከተው ጥቅስ የሚያመለክተው፥ ከታላቁ መከራ ተርፈው በኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ምጽአት የሚድኑትን አማኞች ነው። ብዙ እውነተኛ ክርስቲያኖች ከክርስቶስ ዳግም ምጽአት በፊት በሰማዕታትነት እንደሚሞቱና እርሱ እስኪመለስ ድረስ በሕይወት እንደማይቆዩ መጽሐፍ ቅዱስ በግልጥ ያስተምራል (ራእይ 7፡14)። ጥቅሶች ለዋስትናም ሆን ዋስትና አልባነትን ለመግለጥ እንዴት በተሳሳተ መንገድ ሊያገለግሉ እንደሚችሉ ከዚህ ምንባብ ለመረዳት ይቻላል። 

10. አማኝ ዋስትና ያለው ወይም የሌለው መሆን የሚወሰነው፥ የድነቱን ሥራ የሚሠራው ማነው? ለሚለው ጥያቄ ስሚሰጠው የመጨረሻ መልስ ላይ ነው። አንድ ጊዜ እውነተኛ ድነት ያገኘ አማኝ ለዘላለም ድኗል፥ የሚለው ፅንሰ-አሳብ ድነት በየትኛውም የአማኙ መልካም ሥራ ላይ ያልተደገፈና በርሱ ጥረት የማይቀጥል የእግዚብሔር ሥራ እንደሆነ ከሚያስረዳ መርሕ ላይ ይመሠረታል። የሚያከናውነው ሰው ከሆነ፥ ድነቱ ዋስትና የለውም። እግዚአብሔር የሚሠራው ከሆነ ዋስትና አለው። 

አንድ ጊዜ የዳነ ሰው ድነቱ ለዘላለም አብሮት እንደሚኖር የሚያሰረዳው ፅንሰ-አሳብ፥ ቢያንስ አሥራ ሁለት መጽሐፍ ቅዱሳዊ ድጋፎች አሉት። ከነዚህም መካከል አራቱ ከአብ፥ አራቱ ከወልድና አራቱ ከመንፈስ ቅዱስ ሥራዎች ጋር ይገናኛሉ። 

ለ. አብ በድነት ያለው ሥራ 

መጽሐፍ ቅዱስ ዕቅድመ ሁኔታዎች ላይ ያልተመሠረተውንና በክርስቶስ ለሚያምን ሁሉ የዘላለም ድነት ተስፋ ዮሚሰጠውን የእግዚአብሔርሉዓላዊ ቃል ይገልጣል (ዮሐ. 3፡16፤ 5፡24፤ 6፡37)። በግልጥ እንደሚታወቀው፥ እግዚአብሔር የገባውን ተስፋ ለመፈጸም ይችላል፤ የማይለወጥ ፈቃዱም ሮሜ 8፡29-30 ውስጥ ተገልጧል። 

2. የእግዚአብሔር ሉዓላዊ ኃይል ሰዎችን ለማዳንና ለዘላለምም ለመጠበቅ ይችላል (ዮሐ. 10፡29፤ ሮሜ 4፡21፤ 8፡31 ፥ 38-39፤ 14፡4፤ ኤፌ. 1፡19-21፤ 3፡20፤ ፊልጵ, 3፡21፤ 2ኛ ጢሞ. 1፡12፤ ዕብ. 7፡25፤ ይሁዳ 24)። እግዚአብሔር የተስፋ ቃሉኝ የመፈጸም ታማኝነት ብቻ ሳይሆን፥ የፈቀደውን ሁሉ የሚፈጽምበት ኃይልም አለው። በክርሰቶስ የሚያምኑትን ማዳን የእግዚአብሔር ፈቃድ መሆኑንም መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል። 

3. ወሰን የለሹ የእግዚአብሔር ፍቅር የእግዚአብሔርን ዘላለማዊ ዓላማ የሚመለከት ብቻ ሳይሆን፥ ዓላማው እንደሚፈጸም የሚያረጋግጥም ነው (ዮሐ. 3፡16፤ ሮሜ 5፡7-10፤ ኤፌ. 1፡4)። እግዚአብሔር ለዳኑት ያለው ፍቅር ላልዳኑት ካለው እንደሚልቅ ሮሜ 5፡8-11 ውስጥ የተገለጠ ሲሆን፥ ዘላለማዊ ዋስትናቸውንም ያረጋግጥላቸዋል። አሳቡ ግልጥና ቀጥተኛ ነው። እግዚአብሔር ገና ኃጢአተኞችን እና “ጠላቶቹ” እያሉ ሰዎችን ለማዳን ልጁን ከሰጣቸው፥ በሚቤዥ ጸጋው በፊቱ ከጻደቁና ከታረቁት በኋላማ “ይበልጥ” ይወዳቸዋል። 

እግዚአብሔር ሊተመን የማይቻል ዋጋ የገዛቸውን ሰዎች በፍጹም ፍቅር ወዷቸዋል። በመሆኑም በሉዓላዊነቱ ያለው ኃይል እስኪሟጠጥ ድረስ እንኳ እነዚህን ሰዎች ከእጁ የማያመጣቸው፥ ወይም የማይጥሳቸው ለመሆኑ ይህ ፍቅሩ ዋስትና ነው (ዮሐ. 10፡28-29)። ለንጽጽር ያህል ይህ ተባለ እንጂ፥ ጎናናው የእግዚአብሔር ኃይል ፍጻሜ የለውም። የአብ የተስፋ ቃል፥ ሰማይወሰነው ኃይሉና ፍጹም ፍቅሩ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ራሱን ለእግዚአብሔር የሰጠ ሰው፥ እግዚአብሔር ወደ ሕይወቱ ያመጣውን ድነት እንዳያጣ ያደርጉታል። 

4. የእግዚአብሔር ጽድቅ በክርስቶስ ያመኑ ሰዎችን ዘላለማዊ ዋስትና ያረጋግጣል። ምክንያቱም ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለሙ ሁሉ ኃጢአት በመሞቱ፥ የእግዚአብሔር ጽድቅ የሚጠይቀው ነገር ሁሉ ሙሉ ለሙሉ ተፈጽሟል (1ኛ ዮሐ. 2፡2)። እግዚአብሔር ኃጢአትን ይቅር የሚለውና የዘላለም ድነት ተስፋ የሚሰጠው፥ በፍጹም ጽድቅ ላይ በመመሥረት ነው። ኃጢአተኛውን ይቅር የሚለውም እንዲያው በግዴለሽነት አይደለም። ለኃጢአት ይቅርታ የሚሰጠውም ፍጹም ጻድቅ በመሆኑ ነው። ይህም ከክርስቶስ መስቀል በፊት በብሉይ ኪዳን ዘመን የነበሩትን ብቻ ሳይሆን፥ ከክርስቶስ መሰቀል በኋላ የኖሩትንም ሁሉ ያካትታል (ሮሜ 3፡25-26)። የእግዚአብሔር ጽድቅ አጠያያቂ ካልሆነ በቀር፥ የአማኝ ዘላለማዊ ዋስትና አያጠያይቅም። በመሆኑም፥ እግዚእብሔር ለተሰፋው ታማኝ መሆኑ፥ ፍጹም ኃይሉ፥ ፍቅሩና ጽድቁ ተዳምረው ለአማኙ ድነት ፍጹም ዋስትና ናቸው። 

ሐ. የወልድ ሥራ 

1. ኢየሱስ ክርስቶስ በኃጢአተኞች ምትክ በመስቀል ላይ መሞቱ ለአማኝ ፍጹም ዋስትና ነው። የክርስቶስ ሞት ኮናኝ ለሆነው የኃጢአት ኃይል በቂ መልስ ነው (ሮሜ 8፡34)። ሰው ከእግዚአብሔር ያገኘውን ድነት ያጣል የሚለው አባባል የሚመሠረተው፥ እማኝ ይሠራዋል በሚለው ኃጢአት ላይ ነው። እንዲህ ያለው አስፈላጊ ነው የሚባል ነገር ግምት የሚመነጨው፥ ክርስቶስ አማኙ ወደፊት የሚፈጽማቸውን ኃጢአቶች ሁሉ ከመስቀሉ ላይ እንዳልተሸከመና እግዚአብሔርም ነፍስን ካዳነ በኋላ ያልተጠበቀ ተከታታይ ኃጢአት ከእማኙ ሕይወት ውስጥ አቆጥቁጦ ቢያይ እንደሚያዝንና እንደሚገረም ካሰብ ነው። በአንጻሩ ግን የእግዚአብሔር ሁሉን አዋቂነት ፍጹም ስለሆነ እማኝ የሆነ ልጁን ኃጢአት ወይም ሕይወቱን የሚያጨልመውን ምስጢር አስቀድሞ ያውቃል። ለእነዚህም ኃጢአቶች በቂ የሆነው የክርስቶስ የመሥዋዕትነት ደም የፈሰሰ ሲሆን፥ እግዚአብሔርም በዚያ ደም ስርየትን አድርጓል (1ኛ ዮሐ. 2፡2)። 

ላዳነም ሆነ ላልዳነ ሰው ኃጢአት ብቁ ሆኖ ከሚገኘው የክርስቶስ ደም የተነሣ፥ እግዚአብሔር የድነት ተስፋ የሌላቸውን ፍጹም የማዳኑኝ ያህል፥ ጸጋውንም እንዳለ ለመቀጠል ነጻ ነው። ለዘላለም ይጠብቃቸዋል። ይህን የሚያደርገው፥ ለነርሱ በማሰብ ብቻ ሳይሆን፥ የራሱን ፍቅር ለማርካትና ጸጋውን ለመግለጥ ጭምር ነው (ሮሜ 5፡8፤ ኤፌ. 2፡7-10)። ኵነኔ ሁሉ ለዘላለም የተወገደው፥ ድነትና ድኖ መኖር በእግዚአብሔር ልጅ መሥዋዕትነትና ምግባር ላይ ብቻ የሚደገፉ በመሆናቸው ነው (ዮሐ. 3፡18፤ 5፡24፤ ሮሜ 8፡1፤ 1ኛ ቆሮ. 11፡31-32)። 

2. የክርስቶስ ትንሣኤ ፥ ሰሞቱ ላይ Pተደረገ የእግዚአብሔር ማኅተም እንደመሆ ኑ፥ ለአማኛች የትንሣኤንና የሕይወትን ዋስትና ይሰጣል (ዮሐ. 3፡16፤ 10፡28፤ ኤፌ.2፡6)። ከክርስቶስ ትንሣኤ ጋር የተያያዙት ሁለት ዋነኛ እውነቶች የአማኙን ዘላለማዊ ዋስትና ያረጋግጣሉ። የእግዚአብሔር ስጦታ ዘላለማዊ ሕይወት ሲሆን (ሮሜ 6፡23)፥ ያም የክርስቶስ የትንሣኤ ሕይወት ነው (ቈላ. 2 ፡12፤ 3፡1)። ይህ ሕይወት ክርስቶስ ዘላለማዊ እንደሆነ ሁሉ ዘላለማዊ ነው። ክርስቶስ ሊያከትም ወይም ሊጠፋ እንደማይችል ሁሉ፥ ይህ ሕይወት ሊያከትም ወያም ሊጠፋ አይችልም። የእግዚአብሔር ልጅ የሆነ ሰው በክርስቶስ ትንሣኤ፥ በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትና የዘላለምን ሕይወትን በማግኘት አማካይነት የአዲሱ ፍጥረት አካል ሆኗል። ፍጡር የእግዚአብሔር ክቡር የፈጠራ ሥራ እንደመሆኑ የተፈጥሮን ሂደት ሊቀይር አይችልም። በኋለኛው አዳም በተመሰለው ክርስቶስ ውስጥ ሰመሆኑም፥ ሊቀየር አይችልም፥ ክርስቶስ ሊወድቅ አይችልምና ኦይወድቅምም። ምንም እንኳ በክርስትና ሕይወትና ልምምድ ውስጥ መውደቅ ያለ ሲሆን፥ ሁኔታዎቹ አማኝ በክርስቶስ ያለውን ስፍራ እያቀይሩትም። የእማኝ ስፍራ ከእግዚአብሔር ጸጋ፥ እንዲሁም ከክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ የተነሣ የተቀደሰ ነው። 

3. ክርስቶስ ጠበቃችን በመሆን በሰማያት የሚያከናውነው ተግባርም ዘላለማዊ ዋስትናችንን ያረጋግጣል (ሮሜ 8፡34፤ ዕብ. 9፡24፤ 1ኛ ዮሐ. 2፡1)። ክርስቶስ የእማኝ ጠበቃ ወይም ሕጋዊ ወኪል ነው። ስለዚህ የጌታ የመስቀል ላይ ሥራ ለሥርየትና እግዚአብሔር ከኃጢአተኛው ለሚጠይቃቸው ነገሮች መሟላት ብቁ ነው። ስለሆነም በክርስቶስ አማካይነት ለኃጢአተኛው ከእግዚአብሔር ጋር መታረቅ በቂ ዋጋ እንደተካፈለ ሰመቁጠር ይማልዳል። የክርስቶስ ሥራ ፍጹም ስለሆነ፥ ማንኛውም እውነተኛ አማኝ ኢየሱስ ክርስቶስ በሰማይ እንደ አማኙ ተወካይ ሳቀረበው ሥራ ፍጹምነት ዋስትና ሥር ሊያርፍ ይችላል። 

4. የክርስቶስ የአማላጅነት ሥራ ሰጠቃነቱ ተግባር ተጨማሪ ማረጋጋጫ ይሆናል (ዮሐ. 17፡1-26፤ ሮሜ 8፡34፤ ዕብ. 7፡23-25)። በአሁኑ ጊዜ ክርስቶስ በሰማያት በክብሩ የሚያበረክተው አገልግሎት በምድር ከሚገኙ እማኞች ጋር የተያያዘ ነው። ክርስቶስ እንደ ጠበቃችን የመማለድና የማገልገል ተግባራትን ያከናውናል። እንደ አማላጅነቱ የአማኙን ድካም፥ አለማወቅና አለመብሰል ያያል። እነዚህ ከአማኙ በደለኛነት ጋር የማይዛመዱ ናቸው። ክርስቶስ በዚህ አገልግሎቱ በዓለም ለሚገኙ ወገኖቹ መሻት መጸለይ ብቻ ሳይሆን {ሉቃስ 22 ፣ 31-32፤ ዮሐ. 17፡9፥ 15፥ 20፤ ሮሜ 8፡34)፥ ዘላለማዊ የድነት ዋስትና ይሰጣቸዋል (ዮሐ. 14፡19፤ ሮሜ 5፡10፤ ዕብ. 7፡25)። ይህም ሰርሱ ብቃት ላይ በተመሠረተው የማይለወጥ ክህነት አማካይነት የሚከናውን ነው። 

ክርስቶስ በሞቱ፥ በትንሣኤው፥ በጠበቃነቱና በአማላጅነቱ ያከናወነው ተግባር በእንድነት ሲወሰድ፥ በመስቀልና በሰማይ ለወከለው አማኝ ፍጹም ዋስትናን ይሰጣል። ድነት ሰው ለእግዚአብሔር የሚሠራው ሳይሆን፥ እግዚአብሔር ለሰው የሚሠራው ከሆነ፥ ውጤቱ የተረጋገጠ እውነት ነው። አማኝ “ወደ ኩነኔ እንደማይመጣ” የሚናገረው የዮሐንስ 5:24 የተስፋ ቃልም ያለ ጥርጥር ይፈጸማል። 

መ. የመንፈስ ቅዱስ ሥራ 

1. እማኝ የመለኮታዊ ባሕርይ ተካፋይ የሚሆንበት የዳግም ልደት ወይም የአዲስ ልደት ክንውን የማይለወጥ ሂደት ያለው የእግዚአብሔር ሥራ ነው (ዮሐ. 1፡13፤ 3፡3-6፤ ቲቶ 3፡4-6፤ 1ኛ ጴጥ. 1፡23፤ 2ኛ ጴጥ. 1፡4፤ 1ኛ ዮሐ. 3፡9)። የተፈጠረኝ ፍጡር እንዳልተፈጠረ ማድረግ እንደማይቻል ሁሉ፥ አዲስ ልደት ያገኘንም እንዳልተወለደ እድርጎ መመለስ አይቻልም። ተግባሩ የሚከናወነው በሰው ሳይሆን በእግዚአብሔር ከሆነና፥ ሙሉ ለሙሉ በጻጋ ላይ ከተመሠረተ፥ ለዘላለም የማይቀጥልበት ምክንያት እይኖርም። 

2. ስአሁኑ ዘመን በውስጡ የሚያድረው መንፈስ ቅዱስ የእግኙ ዘቂ ሀብት ነው ( ዮሐ. 7፡37-39፤ ሮሜ 5፡5፤ 8፡9፤ 1ኛ ቆሮ. 2፡12፤ 6፡19፤ 1ኛ ዮሐ. 2፡27)። ከበዓለ ኀምሳ ቀን በፊት እውነተኛ አማኞች ሁሉ የድነት ዋስትና ቢኖራቸውም፥ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ አልሆንም ነበር። በአሁኑ ዘመን ግን፥ ምንም እንኳ ኃጢአተኛና የተበላሸ ሲሆን፥ የአማኙ ሰውነት የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ መሆኑ፥ እግዚአብሔር አማኙን ማዳን የጀመረውን ዓላማ ከግቡ የሚያደርስ ለመሆኑ ማረጋገጫ ነው። መንፈስ ቅዱስ ንስሐ ባልተገባበት ኃጢአት የሚያዝን (ኤፌ. 4፡30) እና የሚጠፋ ወይም የሚዳፈን ቢሆንም {1ኛ ተሰ. 5፡19)፥ እነዚህ ሁኔታዎች አማኝ ድነቱን እንዲያጣ የሚያደርጉ መሆናቸውን በፍጹም አያሳይም። ይልቁንም የአማኙ ድነት አለመቋረጥና ልቡ ውስጥ የሚሠራው የመንፈስ ቅዱስ እውነት ከእግዚአብሔር ጋር ወደሚስማማ ኅብረት እንዲመለስ የሚያነሣሣ መሠረት ሆኖ ቀርሷል። 

3. አማኝ ከክርስቶስና ከክርስቶስ አካል ጋር ለዘላለሙ የተጣመረበት ቀመንፈስ ቅዱስ የጥምቀትራ ሌላው ያዋስትና ማረጋገጫ ነው። አማኝ በመንፈስ ቅዱስ የማጥመቅ ሥራ፥ ክርስቶስ ራስ ወደሆነበት አካል ይጨመራል (1ኛ ቆሮ. 6፡17፤ 12፡13፤ ገላ. 3፡27)። ስለዚህም አማኝ በክርስቶስ አካል ውስጥ ነው ይባላል። ክርስቶስ ውስጥ መሆኑ ዋንኛና ቀጣይነት ያለውን ኅብረት ያመለክታል። በዚህ ኅብረት አማካይነት በስፍራና በግንኙነት የኩነኔ መሠረት የሚሆኑ አሮጌ ነገሮች ይወገዱና ሁሉም ስፍራዎችና ግንኙነቶች አዲስና ከእግዚአብሔር የተገኙ ሆነው ይለወጣሉ (2ኛ ቆሮ. 5፡17፥ 18)። የእግዚአብሔር ልጅ የሆነ ሰው “በተወደደው” ጌታ አማካይነት ለዘላለም ተቀባይነትን ስላገኘ በተቀበለው ጌታ ውሰጥ ለዘላለም የመሆኑ እውነት የጸና ነው። ያስገኘለት ስፍራ የውስጡ ያለውንና የቆመበትን ስፍራ ያህል ዋስትና አለው። 

4. የመንፈስ ቅዱስ በአማኙ ውጥ መኖር እስከመቤት፥ እስክ አማኙ መለወጥ ወይም ትንሣኤ ድረስ የእግዚአብሔር ማኅተም እንደሆን ተጎልሟል (2ኛ ቆሮ. 1፡22፤ ኤፌ. 1፡13-14፤ 4፡30)። ይህ የመንፈስ ቅዱስ ማኅተም የእግዚአብሔር ሥራ ነው። ስለሆነም፥ እግዚአብሔር አማኙን በመንግሥተ ሰማይ እንከን የሌስው አድርጎ እስከሚያቀርብበት ጊዜ ድረስ የአማኙ ዋስትና የታተመ መሆኑን ያመለክታል። ይህ አንድ ጊዜ የዳነ አማኝ ድነቱን የማያጣ መሆኑን እርግጠኛ እንድንሆን ያደርጋል። 

በአጠቃላይ የአማኝ ዘላለማዊ ዋስትና በድነቱ ሁኔታ ላይ የሚመሠረትና የሰው ሳይሆን የእግዚአብሔር ሥራ ነው። የሰው ብርታት ወይም ታማኝነት ላይ ሳይሆን፥ በእግዚአብሔር ኃይልና ታማኝነት ላይ ይመሠረታል። ድነት በሥራ የሚገኝ ወያም ሥራ እንደ ሰናይ ምግባር ታይቶ ለእምነት ሽልማት የሚሰጥ ቢሆን ኖሮ፥ የሰው ዋስትና ምን ያህል አጠያያቂ ይሆን እንደነበር ለመገመት ይቻላል። ከዚህ ይልቅ በጻጋ፥ ብሎም በእግዚአብሔር የተስፋ ቃላትና ሥራ ላይ የሚመሠረት በመሆኑ፥ እማኝ ስለ ዋስትናው እርግጠኛ ሊሆንና ከጳውሎስ ጋር “በእናንተ መልካሙን ሥራ የጀመረው እስከ ኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ድረስ እንዲፈጽመው ይህን ተረድቼአለሁ” (ፊልጵ. 1፡6) ሊል ይችላል። 

ከዚህ ታላቅ እውነት በመነሣት እግዚአብሔር የራሱ የሆኑትን ለመጠበቅ ያለው ዓላማ ከቶውንም አይታጠፍም ብሎ ለማጠቃለል ይቻላል። ለዚህ ፍጻሜ መገኘት እንቅፋት የሚሆኑ ነገሮችን ሁሉ እግዚአብሔር ራሱ አስወግዷቸዋል። አማኙን ከእግዚአብሔር ይለይ የነበረው ኃጢአትም ተወግዷል። ኃጢአታችንን የተሸከመልን ጌታም እማኝ በድነቱ ይዘልቅ ዘንድ በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት የሞቱን ብቃት እያሳየ በመማለድ ላይ ነው። የአማኙ ፈቃድ (ፊልጵ. 2፡13)፥ በመለኮታዊ ቁጥጥር የተያዘ ሲሆን፥ በእግዚአብሔር ጸጋና ጥበብ የሚቻል ወይም የቀላለ ይሆናል (1ኛ ቆሮ. 10፡13)። 

በዚህ ምዕራፍ ጅነትንና በድነት መጠበቅን እንደተለያዩ መለኮታዊ ተግባራት ሲገለጡም፥ እንዲህ ያሉ ልዩነቶች መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሉም። እንደ መጽሐፍ ቅዱስ አገላለጥ፥ በጸጋ ሥር የሚታቀድ፥ የሚሰጥ ወይም ተግባራዊ የሚሆን ድነት ሁሉ ሙሉ ለሙሉ ፍጹምና ዘላለማዊ ነው። 

ምንጭ፡- “ዋና ዋና የመጽሐፍ ቅዱስ ጭብጦች” መጽሐፍ በዶክተር ሉዊስ ስፔሪ ቼፈር የተጻፈ እና በተክሉ መንገሻ የተተረጎመ ነው፡፡ እግዚአብሔር ስለ እነዚህ ቅዱሳን ድንቅ ስራ የተመሰገነ ይሁን፡፡ ማሳሰቢያ፡- ይህን ጽሁፍ መቀየርም ሆነ ለሽያጭ ማዋል በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡

Leave a Reply

Discover more from

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading