የትንቢተ ኢሳይያስ ዓላማ
የትንቢተ ኢሳይያስ በብሉይ ኪዳን ውስጥ ከሚገኙ ጥልቅ የሥነ-መለኮት ትምህርቶች መካከል አንዳንዶቹን የያዘ ነው። መጽሐፉ የይሁዳ ሕዝብ በባቢሎን መንግሥት የሚማረክበትን ምክንያትና የይሁዳ ሕዝብ ቅሬታ ደግሞ በመጨረሻ ከምርኮ እንደሚመለስ ቢናገርም፥ የመጽሐፉ ተቀዳሚ ትኩረት ግን ይህ አይደለም። የኢሳይያስ ትኩረት በእግዚአብሔር ባሕርይ ላይ ነው። የቀሩት ትምህርቶች በሙሉ ኢሳይያስ ስለ እግዚአብሔር የነበረው ግንዛቤ ውጤቶች ናቸው። እግዚአብሔር በይሁዳ ሕዝብ ላይ እንደሚፈርድ […]