የሕይወት እንጀራ

የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት

መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን መግቢያ

የውይይት ጥያቄ፥ ሀ) እግዚአብሔር መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንዲካተት ያደረገው ለምን ይመስልሃል? ለ) የመጽሐፉን አተረጓጐም በሚመለከት ምን ሰምተሃል? መጽሐፈ መክብብ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ለመረዳት እጅግ አስቸጋሪ ከሆኑት መጻሕፍት አንዱ ነው። አስቸጋሪ ከሆኑት ውስጥ ሌላው ደግም መኃልየ መኃልይ ነው፤ ታዲያ ለምንድን ነው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተካተቱት? መኃልየ መኃልይ ላይ ላዩን ቢያዩት አስቸጋሪ አይመስለኝም። በአንድ […]

መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን መግቢያ Read More »

መክብብ 7-12

በሕይወት ውስጥ ሌሎች የሚሰጡንን ቀላል መልሶች ከመቀበል ይልቅ አስቸጋሪ የሆኑ ጉዳዮችን ማሰብ እጅግ አስፈላጊ የሚሆንባቸው ጊዜያት አሉ። መጽሐፈ መክብብ አስቸጋሪ የሆኑ ጉዳዮችን ያነሣል። ጸሐፊው የሚያስተምረውን ነገር ለመረዳት በጥንቃቄ የተሞላ ጥናት ይጠይቃል። ግልጽ መልሶች ስለሌላቸው ጉዳዮች በጥልቀት ለማሰብ ፈቃደኞች ካልሆንን በስተቀር እምነታችንና መረዳታችን ሁል ጊዜ የላላ ይሆናል። የውይይት ጥያቄ፥ ሀ) ሰዎች ቀላል መልሶች የሚሰጡባቸውን፥ በጣም የተወሳሰቡና

መክብብ 7-12 Read More »

መክብብ 1-6

የውይይት ጥያቄ፡ ሀ) ብዙ ክርስቲያኖች በተለይም ወጣቶች፡- ሀብታም፥ የተማረ፥ ጥሩ ኑሮ የሚኖርና ከፍተኛ ሥልጣን ያለው ሰው ለመሆን የሚፈልጉት ለምንድን ነው? ለ) ይህ መልካም ነውን? መልስህን አብራራ። ሐ) ለእነዚህ ነገሮች ያለው አመለካከት ሚዛናዊነት ለጐደለውና ያለ እግዚአብሔር ከንቱና እርባናቢስ መሆናቸውን ላልተገነዘበው ሰው እንዴት ትመክረዋለህ?  የውይይት ጥያቄ፥ መክብብ 1-6 አንብብ። ሀ) የመጽሐፈ መክብብ ጸሐፊ «ከንቱ» የሚላቸውን ነገሮች ዘርዝር።

መክብብ 1-6 Read More »

የመጽሐፈ መክብብ ዓላማ እና ዋና ዋና ትምሕርቶች

የመጽሐፈ መክብብ ዓላማ የምናጠናው የጥበብ መጻሕፍት በመባል የሚታወቁትን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች እንደሆነ ታስታውሳለህ። መጽሐፈ መክብብ ከጥበብ መጻሕፍት አንዱ ነው። የመጀመሪያው፥ የጥበብ መጽሐፍ የሆነው መጽሐፈ ኢዮብ ጻድቅ ለምን መከራ ይቀበላል? ለሚለው ጥያቄ መልስ ለመስጠት ይሞክራል። መዝሙረ ዳዊት እግዚአብሔርን በማምለክ የሚገኘውን የጥበብ መሠረት ሲሰጠን፥ መጽሐፈ ምሳሌ ደግሞ በሕይወታችን እንዴት መኖር እንዳለብን የሚያሳዩ ተግባራዊ መልሶች በማቅረብ የጥበብን መሠረት

የመጽሐፈ መክብብ ዓላማ እና ዋና ዋና ትምሕርቶች Read More »

የመጽሐፈ መክብብ መግቢያ

የውይይት ጥያቄ፥ ሀ) የማያምኑ ሰዎች በሕይወት ውስጥ ካላቸው ዋና ዋና ዓላማዎች መካከል ጥቂቶቹ ምንድን ናቸው? እንዲህ ዓይነቱ ሰው ከፍተኛ ጥረት የሚያደርገው ምን ለማግኘት ነው? እርካታ እንደሚሰጠው አድርጎ የሚገምተው ምንድን ነው? ለ) ብዙ ክርስቲያኖችም በሕይወት ውስጥ ተመሳሳይ ዓላማ ያላቸው እንዴት ነው? ሐ) ይህ ነገር መልካም ነው ወይስ ክፉ? መልስህን አብራራ። ከእግዚአብሔር ጋር የግል ግንኙነት የሌላቸው ወይም

የመጽሐፈ መክብብ መግቢያ Read More »

ከመጽሐፈ ኢዮብ የምናገኛቸው ልዩ ትምህርቶች

1. የሰይጣን ሥራ፡- ቀደም ሲል በኦሪት ዘፍጥረት ውስጥ ሰይጣን በእባብ ተመስሉ ሔዋንን እንዳታለላትና ወደ ኃጢአት እንደመራት የሚያሳየውን የሰይጣንን ሥራ ተመልክተናል፤ ዳሩ ግን በዚያ ታሪክ ውስጥ አይሁድ ከምርኮ እስኪመለሱ ድረስ ስለ ሰይጣን የተገለጠው ነገር እጅግ አነስተኛ ነበር። በዘካርያስ መጽሐፍ ውስጥ አይሁድ ስለ ሰይጣን አካላዊ ህልውና የነበራቸው እውቀት እያደገ መምጣቱን መመልከት እንጀምራለን። በኢሳይያስ 14ና በሕዝቅኤል 28 ስለ

ከመጽሐፈ ኢዮብ የምናገኛቸው ልዩ ትምህርቶች Read More »

የመጽሐፈ ኢዮብ ዓላማ

በመከራና በክፋት መካከል ያለው ግንኙነት መጽሐፈ ኢዮብ የተጻፈው፥ በዚህ ዓለም ላይ ያለውን መከራና ሥቃይ፥ በተለይም ደግሞ ቅዱሳን ወንዶችና ሴቶች ለምን መከራ እንደሚቀበሉ ለማስረዳት ነው። የምንኖረው መከራና ሥቃይ በሞላበት ዓለም ውስጥ ነው። መከራ የሚመጣው ከየት ነው? እግዚአብሔር ሉዓላዊና ጻድቅ ከሆነ፥ በምድር ላይ መከራና ሥቃይ የሚኖረው ለምድን ነው? የውይይት ጥያቄ፥ ቅዱስ የሆነው እግዚአብሔር በምድር ላይ መከራ እንዲኖር

የመጽሐፈ ኢዮብ ዓላማ Read More »

የመጽሐፈ ኢዮብ መግቢያ

የውይይት ጥያቄ፥ ሀ) ክርስቲያን አንዳንድ ጊዜ መከራ የሚቀበልባቸውን ምክንያቶች ጥቀስ። ለ) በክርስቲያን ላይ የሚደርሰው መከራ ሁልጊዜ የኃጢአት ውጤት ነውን? መልስህን አብራራ። ሐ) አንድ ክርስቲያን በበሽታ በሚሠቃይበት ወይም የሚወደው ሰው በሞት በሚለይበት ጊዜ የምትሰጠው ምክር ወይም ማበረታቻ ምንድን ነው? የምንኖረው መከራና ሥቃይ በሞላበት ዓለም ውስጥ ነው። ትንንሽ ልጆች ራሳቸውን በሕይወት ለማቆየት የሚችሉበትን ዕድል ሙሉ በሙሉ በማጣት፥

የመጽሐፈ ኢዮብ መግቢያ Read More »

የጥበብ ሥነ-ጽሑፎች

አብዛኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል በሥነ ግጥማዊ የአጻጻፍ ስልት መጻፉን ቀደም ሲል ተመልክተናል። ይህ በተለይ በመዝሙረ ዳዊት፥ በመኃልይ መኃልየ ዘሰሎሞን፥ እንዲሁም በአንዳንድ የትንቢት መጻሕፍት ውስጥ የምናየው እውነታ ነው። የጥበብ ጽሑፎች የሥነ- ግጥምና ቅኔ ጽሑፎች ክፍል ቢሆኑም፥ «የጥበብ» ጽሑፎች ብለን ልንጠራቸው የምንችለው ልዩ ዓይነት ግጥሞች ናቸው። ከመዝሙረ ዳዊት አንዳንድ ክፍሎችና እንደዚሁም አብዛኛዎቹ የመጽሐፈ መክብብና የመጽሐፈ ምሳሌ ክፍሎች

የጥበብ ሥነ-ጽሑፎች Read More »

የግጥም መጻሕፍት መግቢያ

የውይይት ጥያቄ፡ ሀ) በራስህ ባህል ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ የአጻጻፍ ወይም የአነጋገር ዓይነቶችን ዘርዝር። ለ) ከእነዚህ የአጻጻፍ ወይም የአነጋገር ስልቶች ውስጥ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኙት ምን ያህሎቹ ናቸው? በእያንዳንዱ ባህል ውስጥ የተለያዩ የአጻጻፍ ወይም የአነጋገር ስልቶች ይገኛሉ። ለምሳሌ፥ ከጓደኞቻችን ጋር በምንነጋገርበት ጊዜ የምንጠቀምበት የተለመደ የአነጋገር ዘይቤ አለ፤ ነገር ግን ለተናገርነው ጉዳይ አትኩሮት ለመስጠት ምሳሌያዊ አነጋገሮችን የምንጠቀምበትም

የግጥም መጻሕፍት መግቢያ Read More »