የዮሐንስ ራእይ

አዲስ ሰማይና ምድር እና የክርስቶስ ዳግም ምጽአት ተስፋ (ራእይ 21፡1–22፡21)

፩. አዲስ ሰማይና ምድር (ራእይ 21፡1–22፡6) ስለ መንግሥተ ሰማይና በዚያ ሕይወት ምን እንደሚመስል የበለጠ ብናውቅ ደስ ባለን። ነገር ግን አብዛኛው ነገር ከእኛ የተሰወረ ነው። በዚህ ክፍል ውስጥ መጽሐፍ ቅዱስ መንግሥተ ሰማይ ምን እንደምትመስል በግልጽ ያሳየናል። እግዚአብሔር የተለያዩ ተምሳሌቶችን በመጠቀም የዘላለም ቤታችን ምን ያህል ውብ እንደሆነች እንድንገነዘብና ሕይወታችንን በሚገባ እያዘጋጀን እንድንኖር ያበረታታናል። ዮሐንስ የተለያዩ ምሳሌዎችን በመጠቀም […]

አዲስ ሰማይና ምድር እና የክርስቶስ ዳግም ምጽአት ተስፋ (ራእይ 21፡1–22፡21) Read More »

የክርስቶስ የሺህ ዓመት ንግሥና (ራእይ 20፡1-15)

፩. የክርስቶስ የአንድ ሺህ ዓመት ንግሥና (ራእይ 20፡1-6) ከክርስቶስ ጠላቶች መደምሰስ በኋላ የዮሐንስ ራእይ ስለ ዘላለማዊ መንግሥት አጀማመር ይነግረናል ብለን እንጠብቃለን። ነገር ግን በመጽሐፉ ውስጥ የምናገኘው ክርስቶስ ለአንድ ሺህ ዓመታት በምድር ላይ እንደሚነግሥ የሚያስረዳውን ክፍል ነው። የዮሐንስ ራእይ በተምሳሌቶች የተሞላ መጽሐፍ በመሆኑ፥ ብዙ አማኞች የሺህ ዓመቱ መንግሥት ክርስቶስ በምድር ላይ በአማኞች ልብ ውስጥ፥ በሰማይ ደግሞ

የክርስቶስ የሺህ ዓመት ንግሥና (ራእይ 20፡1-15) Read More »

የክርስቶስ ምጽአት (ራእይ 19:1-21)

፩) በሰማይ ያሉት ለባቢሎን ውድመት የሰጡት ምላሽ (ራእይ 19፡1-10) በራእይ 18 ዮሐንስ ዓለማውያን ለባቢሎን መደምሰስ የሰጡትን ምላሽ ገልጾል። ለእነርሱ ይህ የሐዘን ጊዜ ነበር። ምክንያቱም የወደዷቸው ነገሮች፥ ኃይልና ክብራቸው ሁሉ ወድሟልና ይህም ቁሳዊ ሀብት የሚያመጣው ነው። በራእይ 19፡1-10 ግን በሰማይ ለባቢሎን መደምሰስ የተሰጠው ምላሽ ተገልጾአል። ዮሐንስ በተለያዩ ሰዎች እግዚአብሔር በባቢሎን ተምሳሌትነት ለተገለጸው የዓለም ላይ ክፋት ፍርዱን

የክርስቶስ ምጽአት (ራእይ 19:1-21) Read More »

የባቢሎን ጥፋት (ራእይ 17:1-18:24)

የውይይት ጥያቄ፡- ሀ) ዘፍጥ. 11፡1-9 አንብብ። ባቢሎን በመባል በምትታወቀው ሰናዖር ላይ ምን ተከሰተ? ለ) ከመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ስለ ባቢሎን የተጻፈውን አንብብና ስለ ባቢሎን ታሪክ በተለይም ከእግዚአብሔር ሕዝብ ጋር ስላላቸው ግንኙነት ማጠቃለያ ጻፍ። ሐ) ራእይ 17-18ን አንብብ። ስለ ባቢሎን የተጻፈውን ገለጻና እግዚአብሔር ባለው መሠረት የተፈጸመውን አሳብ ዘርዝር። ራእይ 17-18 በባቢሎን ላይ ሊሆን ስላለው ነገር በሁለት

የባቢሎን ጥፋት (ራእይ 17:1-18:24) Read More »

ሰባቱ የጽዋ ፍርዶች (ራእይ 15:1-16:21)

የዘፍጥረት መጽሐፍ ትልቅ ውበትን በመግለጽ ይጀምራል። እግዚአብሔር በብርሃን፥ በእንስሳትና በሰዎች፥ እንዲሁም በአትክልት ስፍራ የተዋበች ዓለም ፈጥሯል። ከዚህም በላይ እግዚአብሔር በተደጋጋሚ የኤድን ገነት ነዋሪዎች ከሆኑት ወንድና ሴት ጋር እየተገናኘ ይወያያል። በመካከላቸውም ምንም ዓይነት መጋረጃም ሆነ ኃፍረት አልነበረም። ያ ሁሉ ውበት አዳምና ሔዋን እግዚአብሔር በሕይወታቸው ላይ የነበረውን ቁጥጥር በመቃወማቸው ከመቅጽበት ተናደ። በዚህም ጊዜ ያ ሁሉ ውበት በኃጢአት

ሰባቱ የጽዋ ፍርዶች (ራእይ 15:1-16:21) Read More »

በመንፈሳዊ ውጊያ ውስጥ የሚሳተፉ ቁልፍ ግለሰቦች (ራእይ 12:1-14:20) 

የውይይት ጥያቄ፡– ራእይ 12-14 አንብብ። ሀ) በዚህ ክፍል በቀረቡት ራእዮች ውስጥ የተገለጹትን እያንዳንዳቸውን ገጸ ባሕርያት ዘርዝር። እያንዳንዳቸው እንዴት የተለዩና ከሌሎች ጋር ግንኙነት ያላቸው መሆናቸውን ግለጽ። ለ) ይህ ክፍል ስለ እግዚአብሔር አብና ወልድ ምን ያስተምረናል? ሐ) ስለ አማኞች ምን እንማራለን? ዛሬ በምድር ላይ የሚፈጸሙትን ነገሮች ማለትም እንደ ስደት፥ ረሃብና ጦርነት የመሳሰሉትን እንዴት ልንረዳቸው ይገባል? ክርስቶስ ሊመለስ

በመንፈሳዊ ውጊያ ውስጥ የሚሳተፉ ቁልፍ ግለሰቦች (ራእይ 12:1-14:20)  Read More »

የእረፍት ጊዜ (ራእይ 10፡1-11፡14) እና የሰባተኛው መለከት ፍርድ (ዋይታ 3) ራእይ 11፡15-19

ከበደ ተወልዶ ያደገው በክርስቲያን ቤተሰብ ውስጥ ነው። ነገር ግን የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ በነበረበት ወቅት ጀርባውን ለክርስቶስ ሰጥቶ እንደ እግዚአብሔር ሕጎች ላለመመላለስ ወሰነ። የዐመፀኝነት መንፈሱን ካሳየባቸው መንገዶች መካካል አንዱ ወሲባዊ ኃጢአቶችን መፈጸም ነበር። በትምህርት ቤት ከተለያዩ ሴት ተማሪዎች ጋር ያመነዝር ነበር። ገንዘብ ሲኖረው ደግሞ ወደ ሴተኛ አዳሪዎች ጎራ ማለቱን ተያያዘው። ብዙውን ጊዜ ይህ ባህሪው

የእረፍት ጊዜ (ራእይ 10፡1-11፡14) እና የሰባተኛው መለከት ፍርድ (ዋይታ 3) ራእይ 11፡15-19 Read More »

ሰባት የመለከት ፍርዶች (ራእይ 8፡2-11፡19)

ሰባቱ የማኅተም ፍርዶች የመጨረሻውን ዘመን ባሕርያት የሚገልጹ ሲሆን፥ ሰባቱ የመለከት ፍርዶች እና ሰባቱ የጽዋ ፍርዶች ክርስቶስ ሊመለስ ሲል ስለሚሆኑት ሁኔታዎች ዝርዝር ማብራሪያ ያቀርባሉ። በራእይ 6፡9-11፥ ሰማዕት አማኞች፥ እግዚአብሔር በገደሏቸው ሰዎች ላይ ፍትሕንና በቀልን መቼ እንደሚያመጣ ሲጠይቁ እንመለከታለን። አሁን በቅዱሳን ጸሎት ምክንያት በሚገለጹት ሰባት የመለከት ፍርዶች አማካኝነት እግዚአብሔር በኃጢአተኞች ላይ ፍትሕንና በቀልን ሲገልጽ እንመለከታለን። እግዚአብሔር በፍርድ

ሰባት የመለከት ፍርዶች (ራእይ 8፡2-11፡19) Read More »

ሰባት የማኅተም ፍርዶች (ራእይ 6፡1-8፡1)

የውይይት ጥያቄ፡– ራእይ 6-9 አንብብ። ሀ) ስድስቱን የማኅተም ፍርዶች ዘርዝር። ለ) በአንድ መቶ አርባ አራት ሺህዎቹ ላይ ምን እንደሚደርስ ግለጽ። ሐ) በሰማይ የታዩትን እጅግ ብዙ ሕዝብ ግለጽ። መ) ስድስት የመለክት ፍርዶችን ዘርዝር። ሀ) እግዚአብሔር አሁንም ሆነ ወደፊት በምድር ላይ የሚከናወኑትን ነገሮች ስለ መቆጣጠሩ እነዚህ ምዕራፎች ምን ያስተምሩናል? ረ) እነዚህ ምዕራፎች ስለ መጨረሻው ዘመን ባሕርይ ምን

ሰባት የማኅተም ፍርዶች (ራእይ 6፡1-8፡1) Read More »

እግዚአብሔር በዙፋኑ ላይ ተቀምጦ የሚታይበት ራእይ (ራእይ 4:1-5:14)

የውይይት ጥያቄ፡- ሀ) በሰዎች ላይ ተስፋ መቁረጥና ስጋት ሊፈጥሩ የሚችሉትን የዓለም ክስተቶች ዘርዝር። ለ) ክርስቲያኖች ክርስቶስን በመከተላችን ምክንያት የምንሠቃይባቸውን መንገዶች ዘርዝር። ሐ) መከራን በምንቀበልበት ጊዜ የመከራውን ዓላማ ማወቃችን እንዴት እንደሚረዳን ግለጽ። በዓለም ላይ እጅግ ታላላቅ የሆኑት ሰዎች ስለ ዕቅዶቻቸው ሲነጋገሩ የመስማት ዕድል ገጥሞናል እንበል። አዲስ አበባ በሚገኘው ቤተ መንግሥት ገብተው ጠቅላይ ሚኒስቴሩ በአንተ እና በሌሎችም

እግዚአብሔር በዙፋኑ ላይ ተቀምጦ የሚታይበት ራእይ (ራእይ 4:1-5:14) Read More »