ትንቢተ ሚልክያስ

የብሉይ ኪዳን ጥናት ክለሳ

የብሉይ ኪዳንን የተለያዩ መጻሕፍት ስናጠና ቆይተናል። የእያንዳንዱ መጽሐፍ ጸሐፊ ማን እንደሆነ፥ የመጽሐፉን ታሪካዊ ሥረ-መሠረት፥ ዓላማና ዐበይት ትምህርቶች ተመልክተናል። እያንዳንዱን መጽሐፍ ያጠናነው በግል ስለሆነ በመጨረሻ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት በሙሉ በአንድነት እንዴት እንደተዋሀዱ ለመረዳት ጠቃሚ የሆነውን የመጻሕፍቱን ክለሳ መመልከት አስፈላጊ ነው። የውይይት ጥያቄ፦ ሀ) በብሉይ ኪዳን የሚገኙ መጻሕፍት ስንት ናቸው? ለ) የብሉይ ኪዳንን መጻሕፍት ዋና ዋና ክፍሎች […]

የብሉይ ኪዳን ጥናት ክለሳ Read More »

አራት መቶ የጸጥታ ዓመታት

የብሉይ ኪዳን ታሪክ የሚደመደመው በመጽሐፈ ነህምያ ሲሆን፥ ትንቢታዊ መልእክቶች የሚጠቃለሉት ደግሞ በትንቢተ ሚልክያስ ነው። እግዚአብሔር ለሕዝቡ ለእስራኤላውያን የሚሰጠው መልእክት ተፈጸመ። እግዚአብሔር ኤልያስንና መሢሑን እንዲጠባበቁ ለእስራኤላውያን መልእክት ከሰጣቸው በኋላ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚያክሉት ሌላ ተጨማሪ መልእክት አልሰጣቸውም። የመጽሐፍ ቅዱስ ምሁራን ከሚልክያስ ዘመን ጀምሮ (400 ዓ.ዓ.) ኢየሱስ እስከ መጣበት (5 ዓ.ዓ.) ድረስ የነበረውን ጊዜ «400 የጸጥታ ዓመታት»

አራት መቶ የጸጥታ ዓመታት Read More »

የትንቢተ ሚልክያስ ዐበይት ትምህርቶች

1. ለቃል ኪዳኑ ሕግ መታዘዝ በማይኖርበት ጊዜ ከእግዚአብሔር ጋር የገባነውን ቃል ኪዳን አንፈጽምም። ዳሩ ግን የገባነውን ቃል ኪዳን የምንፈጽመው መታዘዛችን ከንጹሕ ልብና ከትክክለኛ ዝንባሌ ሲሆን ነው። ለእግዚአብሔር የሚቀርብ እውነተኛ አምልኮ ትክክለኛ ድርጊቶችን (ተገቢ የሆኑ ሥርዓቶች) የሚያካትት ብቻ መሆን የለበትም። ነገር ግን ለእግዚአብሔር ከሚገዛ ልብ የሚመነጭ፥ ለእግዚአብሔር ሕግ የሚታዘዝ፥ ከኃጢአት የነጻ፥ ከቤተሰብና ከጎረቤቶች ጋር ትክክለኛ በሆነ

የትንቢተ ሚልክያስ ዐበይት ትምህርቶች Read More »

የትንቢተ ሚልክያስ አስተዋጽኦ እና ዓላማ

የትንቢተ ሚልክያስ አስተዋጽኦ የውይይት ጥያቄ፥ ) ስለሚልክያስ ከመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት አንብብ። ለ) በዚህ ስፍራ ስለ ሚልክያስ የተጠቀሱትን ዐበይት እውነቶችን ዘርዝር። ሚልክያስ የተጻፈው እጅግ ልዩ በሆነ መንገድ ነበር። በመጀመሪያ አብዛኛው የመጽሐፉ ክፍል የተጻፈው ሚልክያስ እግዚአብሔርን ወክሎ እንደሚናገር ሳይሆን፥ እግዚአብሔር ራሱ ለእስራኤላውያን በቀጥታ እንደሚናገር ሆኖ ነው። በመጽሐፉ አብዛኛ ክፍል ውስጥ እግዚአብሔር ለአይሁድ የሚናገረው «እኔ» የሚለውን ተውላጠ

የትንቢተ ሚልክያስ አስተዋጽኦ እና ዓላማ Read More »

የትንቢተ ሚልክያስ ታሪካዊ ሥረ-መሠረት

ትንቢተ ሚልክያስ በዕዝራና በነህምያ ታሪክ ዘመን አካባቢ የተጻፈ ነው። ከትንቢተ ሐጌና ዘካርያስ ጥናታችን እንደሚታወሰው እነዚህ ሁለቱ፥ ነቢያት አይሁዶች ቤተ መቅደሱን እንዲሠሩ ያበረታቱ ነቢያት ነበሩ። በመጨረሻ በ516 ዓ.ዓ. የቤተ መቅደሱ ሥራ ተጠናቀቀ። አይሁድ የተሰጧቸውን የተስፋ ቃላት ፍጻሜ ይጠባበቁ ነበር። መሢሑ እንደሚመጣ ቢጠባበቁም፥ መምጣቱን በሚመለከት አንዳችም ምልክት አልታየም ነበር። ከእግዚአብሔር በረከትን በመቀበል በቁሳዊ ነገሮች እንደሚበለጽጉ አስበው ነበር፤

የትንቢተ ሚልክያስ ታሪካዊ ሥረ-መሠረት Read More »

ትንቢተ ሚልክያስ መግቢያ

የብሉይ ኪዳንን የትንቢት መጻሕፍት በምናጠናበት ጊዜ ሁሉ ሕዝቡ የወደፊቱን ነገር በተስፋና በጉጉት ይጠብቁ እንደነበር ተመልክተናል። ምንም እንኳ የእግዚአብሔር ሕዝብ በስደትና በመከራ ውስጥ ቢሆኑ ወይም አይሁድ በምድር ዙሪያ ሁሉ ተበትነው የሚኖሩ ቢሆኑም የእግዚአብሔር ቃል የወደፊቱን ነገር እንዲመለከቱ ያበረታታቸው ነበር፡፡ በብሉይ ኪዳን ውስጥ ከሚገኙ የወደፊት ተስፋዎች መካከል አይሁድ ይጠብቁት የነበረው ዋና ተስፋ የመሢሑን መምጣት ነበር። የእስራኤል ንጉሥና

ትንቢተ ሚልክያስ መግቢያ Read More »