የሕይወት እንጀራ

2ኛ የጴጥሮስ መልእክት

ጴጥሮስ ክርስቶስ ቃል እንደገባው ተመልሶ አይመጣም የሚለውን አሳብ ፉርሽ ያደርገዋል (2ኛ ጴጥ. 3፡1-18)

በመቀጠልም ጴጥሮስ በአብያተ ቤተ ክርስቲያናት እየተሰራጩ ካሉት ሐሰተኛ ትምህርቶች የአንደኛውን አስተምህሮ ሲያፈርስ እንመለከታለን። የክርስቶስን ዳግም ምጽአት የተጠራጠሩ ሰዎች የነበሩ ይመስላል። «ሰዎች ሁልጊዜም ስለ ዓለም ፍጻሜ ሲተነብዩ ኖረዋል። ይሄ እስካሁን አልተከሰተም። ክርስቶስም በቶሎ እመለሳለሁ ብሎ ነበር። ነገር ግን ይኸው ከ30 ዓመታት በኋላም ብቅ አላለም። ይህም የክርስቶስ ዳግም ምጽአት የሚባል ነገር እንደሌለ ያሳያል» ይሉ ነበር። ጴጥሮስ ይህንን […]

ጴጥሮስ ክርስቶስ ቃል እንደገባው ተመልሶ አይመጣም የሚለውን አሳብ ፉርሽ ያደርገዋል (2ኛ ጴጥ. 3፡1-18) Read More »

ጴጥሮስ አማኞች መጽሐፍ ቅዱስን ከሚያዛቡ ሐሰተኛ አስተማሪዎች እንዲጠበቁ ያስጠነቅቃል (2ኛ ጴጥ. 2፡1-22)

አማኞች በእምነታቸው እና የእግዚአብሔርን ቃል በማወቅ የማያድጉ ከሆነ በአደገኛ ሁኔታ ላይ ይወድቃሉ። ሐሰተኛ ትምህርቶች በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሊስፋፉ የሚችሉት በዚህ ጊዜ ነው። በጴጥሮስ ዘመን በአማኞች ሕይወት ውስጥ እየተከሰተ የነበረው ችግር ይህ ነበር። የ2ኛ ጴጥሮስ መልእክት ዋነኛ ትምህርት ክርስቲያኖችን ስለ ሐሰተኛ ትምህርትና አስተማሪዎች ማስጠንቀቅ ነበር። በብሉይ ኪዳን ዘመን እውነተኛ ነቢያት በተነሣ ቁጥር ሐሰተኛ ነቢያትም ይነሡ ነበር።

ጴጥሮስ አማኞች መጽሐፍ ቅዱስን ከሚያዛቡ ሐሰተኛ አስተማሪዎች እንዲጠበቁ ያስጠነቅቃል (2ኛ ጴጥ. 2፡1-22) Read More »

በእምነትና ስለ እግዚአብሔር ባል እውቀት ማደግ (2ኛ ጴጥ. 1፡1-21)

ስለሺ እግዚአብሔርን የሚወድ ወንድም ነበር። እግዚአብሔርም በቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ በሽምግልና አገልግሎት በብዙ መንገዶች ተጠቅሞበታል። ይሁንና፥ ስለሺ ሁልጊዜም ለእግዚአብሔር የሚቀና ሰው አልነበረም። ከአሥር ዓመታት አካባቢ በፊት፥ ለእግዚአብሔር የነበረው ፍቅር እየቀዘቀዘ እንዲሄድ አድርጓል። አንድ ሌሊት ከሚስቱ ጋር ብዙ ከተጨቃጨቁ በኋላ፥ ወደ ቡና ቤት ሄዶ ጠጥቶ ከሰከረ በኋላም እዚያው ከአንዲት ሴተኛ አዳሪ ጋር አብሮ አደረ። በኋላም መንፈስ ቅዱስ

በእምነትና ስለ እግዚአብሔር ባል እውቀት ማደግ (2ኛ ጴጥ. 1፡1-21) Read More »

የ2ኛ ጴጥሮስ ልዩ ባሕርያት፣ መዋቅር፣ እና አስተዋጽኦ

፩. የ2ኛ ጴጥሮስ ልዩ ባሕርያት ብዙ ምሁራን የይሁዳን መልእክት ከ2ኛ ጴጥሮስ 2፡1-22 ጋር ያነጻጽራሉ። እንዲያውም ከይሁዳ መልእክት 25 ጥቅሶች መካከል 19ኙ ከ2ኛ ጴጥሮስ ጋር ተመሳሳይ ናቸው። ይህ ማለት ጴጥሮስ የይሁዳን መልእክት ወይም ይሁዳ የ2ኛ ጴጥሮስን መልእክት ማንበቡን ወይም፥ ሁለቱም በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተሰጠው አንድ ትምህርት በማጣቀሻነት መጠቀማቸውን ሊያመለክት ይችላል። ትክክለኛው ሁኔታ የትኛው እንደነበረ ግን ማወቁ

የ2ኛ ጴጥሮስ ልዩ ባሕርያት፣ መዋቅር፣ እና አስተዋጽኦ Read More »

የ2ኛ ጴጥሮስ ዓላማ

የመጀመሪያው ዓላማ፡ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሐሰት ትምህርት መስፋፋት ጴጥሮስን አሳስቦት ነበር። ስለሆነም፥ የዚህ መልእክት ቀዳማይ ዓላማ ክርስቲያኖች በሐሰተኛ ትምህርቶች እንዳይወሰዱ ለማስጠንቀቅ ነው። ጴጥሮስ እንደሚለው፥ በመጨረሻው ዘመን ከሚከሰቱት ዐበይት ነገሮች አንዱ በፍጥነት የሚራሱ ሐሰተኛ ትምህርቶች መኖራቸው ነው። ክርስቲያኖች እውነተኛ የሆነውንና ያልሆነውን እንዴት ለይተው ሊያውቁ ይችላሉ? ለዚህ መረጃ ቀዳማዊው ምንጭ መንፈስ ቅዱስ በሰዎች ልብ ውስጥ ከማደሩ የተነሣ

የ2ኛ ጴጥሮስ ዓላማ Read More »

የ2ኛ ጴጥሮስ መግቢያ

ሸምገል ያለ ሰው ነበር። ከ30 ዓመት በፊት ነበር አንድ ክስተት ሕይወቱን የለወጠው፡፡ በአንድ ተራ ቀን ወንድሙ የእድሜ እኩያው ከሆነው ከክርስቶስ ጋር እንዲተዋወቅ ጠየቀው «መሲሁ ይሄ ነው» ሲል ነገረው። ለሚቀጥሉት ሦስት ተኩል ዓመታት ከመሢሑ ጋር በመጓዝ፥ በመነጋገር፥ ሕይወቱን በመመልከት፥ ሲሞትም እዛው በመገኘትና በትንሣኤውና በእርገቱ በመደነቅ አሳልፎአል። ይህን መልእክት በሚጽፍበት ጊዜ ብዙ ዘመናት ስላለፉ እርጅና ተጫጭኖታል። እናም

የ2ኛ ጴጥሮስ መግቢያ Read More »